Tuesday, December 25, 2012

ከቀጣዩ የኢህአዴግ ጉባዔ ምርጫ አዳዲስ አመራሮች አይጠበቁም ተባለ


ታህሳስ ፲፭(አስራ አምስትቀን ፳፻፭ /

ኢሳት ዜና:-የኢህአዴግ ጉባዔ በየካቲት ወር በመቀሌ ከተማ የግንባሩን አመራር ይመርጣል ተብሎ የሚጠበቅ ቢሆንምምርጫው ግን ብዙም አዳዲሰ ለውጦች እንደማይኖሩት ለድርጅቱ ቅርበት ያላቸው ሰዎች ገለጡ

በግንባሩ ሕገደንብ መሰረት ከሁለት እስከ ሁለት ዓመት ተኩል ባለው ጊዜ ውስጥ የሚካሄደው ይኸው ጉባዔ በየካቲት ወር2005 ሲካሄድ ግንባሩን ለቀጣይ ሁለት ዓመት የሚያገለግሉ አመራሮችን ይመርጣል፡፡

በዚሁ መሰረት የግንባሩ አባል ድርጅቶች እስከቀጣዩ ወር የራሳቸውን ጉባዔ በማካሄድ ለኢህአዴግ ሥራ አስፈጻሚነትየሚያገለግሉ እያንዳንዳቸው ዘጠኝ አባላትን የሚመርጡ ሲሆን እነዚህ በጠቅላላው 36 አባላት የግንባሩ ሥራ አስፈጻሚበመሆን ከመካከላቸው የግንባሩን ሊቀመንበር፣ምክትል ሊቀመንበር ምርጫ በጉባዔው ላይ ያከናወናሉ፡፡

ይህ ጉባዔ ከአቶ መለስ ሞት በኃላ በቅርቡ የተሾሙትን የግንባሩን ሊቀመንበር አቶ ኃይለማርም ደሳለኝ እና ምክትላቸውንአቶ ደመቀ መኮንን ያነሳል ተብሎ እንደማይገመት ታውቋል፡፡

በሕመም ምክንያት ረዥም የሕክምና ክትትል ላይ የሚገኙት የአህዴድ ሊቀመንበር አቶ አለማየሁ አቶምሳ በምክትላቸውአቶ ሙክታር ከድር ይተካሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

አቶ አለማየሁ ቀደም ሲልም መልቀቂያ ከማቅረባቸው ጋር ተያይዞ በቅርቡ በተካሄደው የሶስት ምክትል /ሚኒስትሮችሹመት ውስጥ ኦህዴድን መወከል የሚገባቸው እሳቸው የነበሩ ቢሆንም ምክትላቸው አቶ ሙክታር እንዲሾሙ ኦህዴድበወከላቸው መሰረት አቶ ኃይለማርያም ካቢኔ ውስጥ መካተታቸው ይታወሳል፡፡
በተያያዘ ዜና በቅርቡ የተካሄደው ሹመት ብዙም ያላስደሰታቸው የህወሃት አባላት የቀድሞ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር የነበሩትንአቶ ቴዎድሮስ አድሃኖምን ወደ ውጪ ጉዳይ ሚኒስትርነት እንዲዛወሩ ያደረጉት ከሁለት ዓመት በኃላ የጠ/ሚኒስትርነትንቦታ እንዲይዙ ታቅዶ ሊሆን ይችላል የሚሉ አስተያየቶች አሉ።

የአቶ መለስ ሞት ከማንም በላይ ህወሃቶችን ያደናገጠና ሁኔታውንም ተከትሎ የተሰጡ ሹመቶች ነባር የሚባሉ ከፍተኛየህወሃት አመራሮችን ጭምር እንዳላረካ የሚጠቅሱት የቅርብ ሰዎች፣  ትልቁ የህወሃቶች ስጋት ከእጃቸው የወጣውንስልጣን መቼ መልሰው እንደሚያገኙት እርግጠኛ መሆን አለመቻላቸውና ብዙዎቹ አመራሮች ከፍተኛ ሃብት ከማፍራታቸውጋር ተያይዞ ስጋት ላይ በመውደቃቸው ነው ተብሎአል፡፡

ይህ ጉዳይ በህወሃቶች በሚስጢር ተመክሮበት አቶ ቴዎድሮስ ከጠ/ሚኒስትር ኃይለማርም ጋር   በቅርበት መስራትበሚያስችላቸው ቦታ በማስጠጋት 2007 . አገራዊ ምርጫን ተከትሎ በሚደረገው የጠ/ሚኒስትር ሹመት ብቁማድረግ የሚለው ዕቅዳቸው በፓርቲያቸው ተቀባይነት አግኝቶ መተግበሩን አስረድተዋል፡፡

እንደ ህወሃቶች ዕቅድ ከሆነ አቶ ኃይለማርያም ከሁለት ዓመት ስልጣን በኃላ መሰናበታቸው ግድ ይሆናል፡፡ ይሁን እንጅ ይህ የተባለው ዕቅድ መኖርና አለመኖሩን ከገለልተኛ ወገን ማረጋገጥ አልተቻለም።

ኢህአዴግ ባስቀመጠው የመተካካት ዕቅድ መሰረት የብአዴን ጎምቱ የተባሉ አመራሮች በአዲስ መተካትሚኖርባቸው ቢሆንም እስካሁን ባለው መረጃ መሰረት እንደ እነአቶ በረከት ስምኦን የመሳሰሉ ነባር አመራሮች ከፓርቲውስራ አስፈጻሚ ስለመነሳታቸው ጉዳይ ምንም ዓይነት ፍንጭ አለመኖሩን ጠቁሟል።

No comments:

Post a Comment