Wednesday, December 19, 2012

33 የፖለቲካ ድርጅቶች በምርጫ ስም ገንዘብ ማባከን እንዲቆም ጠየቁ


ታህሳስ ፱(ዘጠኝ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-ድርጅቶቹ ባወጡት መግለጫ በጥቅምት 15 ቀን 2005 ዓም የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ በአዳማ ኤክስኪዩቲቭ ሄቴል በዚህ አመት በሚደረገው የአካባቢ እንዲሁም የአዲስ አበባና ድሬዳዋ ከተማ ምርጫ የግዜ ሰሌዳን አስመልክቶ  የውይይት መድረክ መጥራቱን ጠቅሰዋል።
ድርጅቶቹ በመግለጫቸው ” ምርጫ ለማካሄድ ነባራዊ ሁኔታው የማይፈቅድ ስለሆነ በፖለቲካ ምህዳሩና በህዝብ ወሳኝነት ሁሪያ መወያየት አለብን ብለን ፒቲሺን ተፈራርመን ለቦርዱ ያስገባን 33 ፓርቲዎች ጉዳይ ወደ ጎን ተትቶ ቀልድ በሚመስል መልክ በጾታ ጉዳይ ልናወያያችሁ እንፈልጋለን ማለት የህዝብን የምርጫ ባለቤትነት የሚጋፋ ተግባር ሆኖ አግኝተነዋል።” ካሉ በሁዋላ፣ ቦርዱ ጾታን በተመለከተ እና አሁን ላለንበት ሁኔታ ቀላል የሆነ ጉዳይ ጠቅሶ በጠራው የፖለቲካ ፓርቲዎች የውይይት  መድረክ የማንሳተፍ መሆናችንን ፔቲሺን የፈረምን 33 የፖለቲካ ፓርቲዎች እናሳውቃለን።” ብለዋል።
33ቱ የፖለቲካ ድርጅቶች ምርቻ ቦርድ በገለልለተኛ ወገኖች እንዲቋቋም፣ ነጻና ፍትሀዊ የመገናኛ ብዙሀን እንዲኖሩ፣ የመንግስት የመገናኛ ብዙሀን ሁሉንም ድርጅቶች በእኩል እንዲያገለግሉ፣ መከላከያ፣ ፖሊስና የደህንነት ተቋማት በነነጻነት እንዲዋቀሩ፣ በተቃዋሚዎች ላይ የሚደርሰው ማዋከብ እንዲቆም የሚሉና ሌሎችንም በርካታ ጥያቄዎች መጠየቃቸው ይታወሳል።

No comments:

Post a Comment