Monday, April 29, 2013

ESAT WAZA ENA KUMENGER ETHIOPIA


ኢህአዴግ በኖርዌይ ገንዘብ ማሰባሰብ ተሳነው


oslo


በስደት አገራቸውን ለቀው የወጡ ሰዎች ያለመሰለል መብት አላቸው። በህግም የተደነገገ ነው። ከለላ የሰጣቸውም አገር ይህንን የመከላከልና የመቃወም ግዳጅም አለበት። ከለላ ያገኙ ስደተኞችም ሆኑ ከለላ እንዲሰጣቸው ያመለከቱ ወገኖች ስለመሰለላቸው ተጨባጭ ማስረጃ ማቅረብ ከቻሉ ህጉን ጠቅሰው የመከራከር መብት አለቸው። ለመብታቸው ሲከራከሩ በመደራጀት ቢሆን ይበልጥ ውጤታማ ሊሆኑ እንደሚችሉ አውሮፓ በስደት ያሉ ቀድሞ የውጪ ጉዳይ የዲያስፖራ ኢንጌጅመንት ዳይሬክቶሬት ዲፓርትመንት ኤክስፐርት ይናገራሉ።
እኚሁ ሰው እንደሚሉት ከ1997 ዓ ም ምርጫ በኋላ በአቶ መለስ ቀጥተኛ ትዕዛዝ የተቋቋመው ይህ ዲፓርትመንት ለጠቅላይ ሚኒስትሩና ለወቅቱ የውጪጉዳይ ሚኒስትር አቶ ስዩም መስፍን ሪፖርት ያቀርብ ነበር። በጁላይ 2003 ስድስት አባላትን በመያዝ የተቋቋመው ዲፓርትመንት “ብዙሃን አድፋጭ” ዲያስፖራ ወይም “silent majority” የሚባሉትን ለመማረክና በስደት ውጪ አገር የሚኖሩትን የተቃዋሚ ድርጅት ዋና ደጋፊዎችንና አመራሮችን የሚከታተል ቻፕተሮች አሉት።
የአገዛዙ ደጋፊ ለሚባሉት ዲያስፖራዎች የቀረጥ ነጻ መብት በመስጠት፣ መሬት በማደል፣ በማህበራት በማደራጀት ቢቻል መታወቂያ በመስጠት፣ “ለአገር ግንባታ ደጋፊ ማድረግ” በሚል ሽፋን በያሉበት አገር ከኤምባሲ ጋር ግንኙነት እንዲፈጥሩ በማድረግ የተዘረጋው መዋቅር የአውሮፓውን የክትትል ስራ በግንባር ቀደምትነት እንዲመራ የመደበው የብራስልስ ኤምባሲን ነው። በቤልጂየም ኢትዮጵያ ኤምባሲ ካውንስለር በመሆን የሚያገለግሉት የቀድሞው የህወሃት ታጋይ ይህንኑ የአውሮፓ የክትትል ቻፕተር እንደሚመሩት የሚያስረዱት የቀድሞ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ሰራተኛ የቻፕተሩን ጠርናፊ “አቶ መለስ በታመሙበት ወቅት ብራስልስ ሆነው አስፈላጊውን ሁሉ ሲያደርጉ የነበሩ የስርዓቱ ታማኝ ሰው ናቸው” ሲሉ ይገልጹዋቸዋል።
በጥቅማ ጥቅም ዲያስፖራ ውስጥ ሆነው የክትትል ስራ በመስራት በያሉበት አገር ካለው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ጋር ግንኙነት በመፍጠር ስርዓቱን የሚያገለግሉ ስለመኖራቸው በውል የሚናገሩት እኚሁ ሰው “ስርዓቱን ሸሽተው ጥገኛነት የሚጠይቁ ኢትዮጵያውያን ስለ አገዛዙ የሚሰጡት መረጃ ስለሚያንገበግባቸው ዲያስፖራው ውስጥ ያለውን እንቅስቃሴ ለማኮላሸት ከፍተኛ በጀት ይመደባል። በዚሁ በጀት እጅግ ቀረቤታ ላላቸው ደጋፊዎቻቸው በሚኖሩበት አገር ተራ የጉልበት ሰራተኛ የሚያገኘው ክፍያ ተሰልቶ ይከፈላቸዋል” በማለት አገሩን፣ ቤተሰቡን፣ ንብረቱን፣ ቤተዘመዱን ጥሎ የሸሸውን ዜጋ እየተከታተሉ ሪፖርት ስለሚያቀርቡት ክፍሎች ይናገራሉ።
ሰፊ ማብራሪያ ያቀረቡት እማኝ የኢህአዴግ ደጋፊዎች የልማትና ድጋፍ ማሰባሰቢያ መድረኮችን በማመቻቸት ታማንነታቸውን እንደሚያሳዩ የሚገልጹት የቀድሞ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ባልደረባ “ይህ አሰራር የተኮረጀው ከቻይና ነው። የተለያዩ አገር አሰራሮችና የደህንነት መዋቅሮች የተጠኑ ቢሆንም የ  ቻይናው የተመረጠው ለስራውና ኢህአዴግ ለሚፈልገው አደረጃጀት አመቺ ሆኖ በመገኘቱ ነው” ሲሉ የመዋቅሩን ተፈጥሮ ያስረዳሉ።
ከሳምንት በፊት በኖርዌይ ስታቫንገር፣ ዛሬ ኤፕሪል 28/2013 ደግሞ በኦስሎ ስለተካሄደው የቁጣ ተቃውሞ አስተያየት የሰጡት እኚሁ ሰው “ኢህአዴግ ሊገለኝ ነው በማለት ሸሽተው ጥገኝነት የጠየቁ ወገኖች ከመንግስት ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት የላቸውም። ሊኖራቸውም አይችልም ማስረጃ በማሰባሰብ ጉዳዩን ወደ ህግ ማቅረብ ይቻላል” ባይ ናቸው።
“ተሰደን አገር ለቀን ወጣን። አገራችን እንዳንኖር ተደረግን። በስደት በምንኖርበት አገር ድረስ መጥተው ገንዘብ ሊጠይቁን ማሰባቸው ይገርማል። እንደዚህ ገንዘብ የተጠሙበት ምክንያት ምን ይሁን? ኢህአዴግ አገሬ እንዳልኖር አደረገኝ፣ ህይወቴ አደጋ ላይ ነው በሚል ከለላ የጠየቀ ሰው እንዴት መንግስት ደጅ ይቀርባል። ይህ እኮ ህገወጥ ነው። ወንጀል ነው። ከለላ የሰጠው አገርም ሆነ ዋናው የስደተኞች ህግ አይደግፈውም” በሚል አንድ ጥግ ይዘው የሚነጋገሩና የሚወያዩም አጋጥመውኛል።
መከላከያው አክራሪንና አልሸባብን ይደመስሳል በሚል የማይነጥፍ ገበያ አላቸው። መሬት ይሸጣሉ። ንግዱን ተቆጣጥረውታል። ኢንቨስትመንቱን በጃቸው አድርገውታል። አስመጪና ላኪነቱን የግላቸው አድርገውታል። ባዕድ ሃይል የማያደርገውን የከፋ ተግባር እንመራዋለን በሚሉት ህዝብ ላይ ይፈጽማሉ። አገሪቱን በዘርና በጎሰኝነት አስተሳሰብ መርዝ በክለው እርስ በርስ እያጫረሱ ምድሪቱን የበቀል ቡቃያ አድርገዋታል። ታዲያ እነዚህ ሰዎች በየትኛው ሞራላቸው ነው ስደት የሚለበልባቸውን ዜጎች ሰብስበው ገንዘብ የሚጠይቁት? የሁሉም ጥያቄ ነው።
በተጠቀሰው ቀን ለአባይ ግድብ የገንዘብ ማሰባሰቢያ ለማካሄድ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ አጭር የስልክ መልዕክት (የኤስ ኤም ኤስ) ጥሪና በተለያዩ አደረጃጀቶች ጥሪ ተበትኖ ነበር። ኦስሎ የሚኖሩ የስርዓቱ ሰለባዎች ራሳቸውን አደራጅተውና ግብረኃይል አቋቁመው በስብሰባው ለመገኘት ዝግጅታቸውን አስቀድመው እንዳከናወኑ በስፍራው የነበሩ ለጎልጉል ዘጋቢ አመልክተዋል።
እንደተባለው ጠዋት ረፈድ ፈድ ሲል በስቶኮልም የኢትዮጵያ ኤምባሲ ሰው ስብሰባውን ለመምራት ወዳጆቻቸውና ደጋፊዎቻቸው ያዘጋጁት መድረክ ላይ ለመቀመጥ Radisson Blue Scandinavia Hotel ሲደርሱ የጠበቃቸው ሌላ ነበር። በስብሰባው ለመገኘት የሚያስችል “የዜግነት” መብት ያላቸው ወገኖች ስብሰባውን ለመካፈል ጠየቁ። “አትገቡም” ሲባሉ ተቃውሟቸውን ከቁጣ ጋር አሰሙ። ባለስልጣኑ ማሽላ እያረረ ይስቃል እንደሚባለው ፈገግታ በማሳየት በምሬት በሚወርደው የተቃውሞ ቃል መገረፋቸውን ለመደበቅ ሞከሩ። ንዴታቸውን ለመደበቅ ሲታገሉ ጭራሹኑ ስብሰባውን ማድረግ በማይችሉበት ደረጃ ተቃውሞው ስለጨመረ ለአባይ ግድብ ብር ለማሰባሰብ የተወጠነው የኦስሎው ውጥን ስታቫንገር እንደሆነው ተኮላሸ። ፖሊስ ስብሰባው ሊካሄድ እንደማይችል አረጋገጠ።
በኖርዌይ ከሚታተሙትና ይህንኑ ጉዳይ አስመልክቶ ዜና ካሰራጩት መካከል፣ ቬጌ የሚባለው ጋዜጣ አስራ አንድ ሰዎች ህገወጥ ሰላማዊ ሰልፍ አድርገዋል በሚል መታሰራቸውን አስነበበ። በስፍራው ቁጣቸውን የገለጹ ወገኖች ሳያስፈቅዱ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ አድርገዋል በሚል ጋዜጣው የእስሩን ምክንያት ፖሊስን ጠቅሶ አስፍሯል። በስፍራው የተገኙም ሆኑ የዚህ ሪፖርት አቅራቢ እንደታዘበው ዜጎች አስቀድመው የጠየቁት በስብሰባው ላይ እንሳተፍ የሚል የዜግነት ጥያቄ ነበር። በጥያቄያቸው መሰረት ወደ ስብሰባው ቦታ ለመግባት ሳይችሉ መከልከላቸው እንደ ዜጋ የሞራልና የማንነት ጥያቄ በመሆኑ ቁጣቸው ከስርዐቱ ተፈጥሮ ጋር ተዳምሮ የነደደ ነበር።
ከፍተኛ ቁጥር የነበረው የፖሊስ ሃይል አስራ ሁለት ተሽከርካሪዎችን አሰልፎ የቁጣውን ሰልፍ “ለመቆጣጠር” እንደቻለ፣ የሰለጠኑ ውሾችና ከሆቴሉ በቅርብ ርቀት ሄሊኮፕተርም ተዘጋጅቶ እንደነበር ቬጌ አስነብቧል። የጎልጉል ሪፖርተር ባሰባሰበው መረጃ አባይ ቢገደብ የሚጠሉ ወገኖች የሉም። ቅድሚያ ሊከናወኑ የሚገባቸው ጉዳዮች እንዳሉ ግን ይስማማሉ። ቅድሚያ አፈናውና ያለ ህዝብ ውክልና በጠመንጃ ከህዝብ ጫንቃ ላይ መንሰራፋት ሊቆም ይገባዋል። የመብት ገደብም ሊቆም ግድ ነው። ይህ ሲሆን ገንዘብ ያለው በገንዘቡ፣ ገንዘብ የሌለው በጉልበቱ አድርግ የተባለውን ያደርጋል። አገርም በዜጎቿ ፍላጎትና እኩል ተሳትፎ ያለ ስጋት ትለማለች።
የታሰሩት ሰዎችን በተመለከተ ይህ ሪፖርት እስከተጠናከረበት ሰዓት ድረስ ስለመፈታታቸው የተሰማ ነገር የለም። በሳምንት ጊዜ ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ ጠንካራ ሊባል የሚችል ተቃውሞ ያጋጠመው ኢህአዴግ፣ በኖርዌይ ተመሳሳይ ፕሮግራም ለማካሄድ ባይሞክር እንደሚሻለው ገለልተኛ ነን የሚሉ ወገኖች ተናግረዋል። አቶ መለስ በህይወት በነበሩበት ወቅት በኖርዌይ የገጠማቸው ተቃውሞ የከፋ እንደነበርና የመጡበትን ጉዳይ በወጉ ሳይጨርሱ መመለሳቸውን ያስታወሱት እነዚሁ ክፍሎች “አሜሪካ በዲቪ የተጓዙ ደጋፊዎች ሊኖሩ ይችላሉ። አውሮፓ ግን በትምህርት መጥተው የቀሩ ካልሆኑ በስተቀር ኢህአዴግ በግልጽ ሊደግፉት የሚችሉትን አባላት ለመግኘት አይቻለውምና አባይን እንደጀመረው ከቻይና ተበድሮ ቢያጠናቅቀው ይመረጣል” ብለዋል። ኢህአዴግ በተለያዩ የአውሮፓ ከተሞች፣ በሳዑዲ አረቢያ፣ በዱባይ፣ በደቡብ አፍሪካ ተመሳሳይ ተቃውሞ እንደገጠመው በተለያዩ ሚዲያዎች መዘገቡ የሚታወስ ነው። (ፎቶ: VG)

The Agenda of Nile Dam Fundraising Event prepared by TPLF, In Oslo Norway has failed again.

On April 28,2013  The Agenda of Nile Dam Fundraising Event prepared by TPLF, In Oslo Norway  has failed again.


Oslo Norway April 28,2013

It was almost intolerable and angry to know and saw TPLF's own agenda to bring back again the  propaganda of Fundraising event for the so called development for Ethiopians in Norway when their is total ignorance of  hearing  the voice of the people for Justice.What comes first ? Human rights of the people in one country or construction of Dam under injustice  ? 


It is really a big Ignorance of TPLF's to come repeatedly in Norway and announce a fundraising event for angry Ethiopians who are tired of  being victim of TPLF's, hearing news of injustice all the times, who have family prisoned in Homeland , who loses a freedom of religion, who is being victimised because of Ethnicity, and with all Human right violation in Ethiopia.
TPLF's came in Norway to collect a fund raising money from this Ethiopians.

They have planned to raise money again in Oslo after they failed to do it in Stavanger Norway on 20 of April 2013.  It is obviously known that they are not after the money but their own propaganda of making up story how they have supporters and the same all 11%  economy growth talk, they dare to do it again In Oslo  but could't make it at all, it was even worse of humiliation to run away cheesed by the people, they changed the place of where the fundraising event will take place what they  first announced ,because they were afraid what they will face again for sure but then their tactic of changing place was known immediately by the organized group of Ethiopians. So the people have got in to the place before anything has begun , It was more than three hundred people  demonstrated  against TPLF'S agenda , All the people who has been in the place was angry and impatient to see them and were shouting TPLF is thief,killer, we need justice,and so many slogans written to free prisoners of conscience, Free Oromo student prisoners and picture of  innocent prisoners who are suffering in Ethiopia,and also demand of freedom of religion.
The united demonstration of Ethiopians in Norway could not give a breath to TPLF representatives to forward  one step a head, so that the Norwegian police are forced to stop the program and it was not able for the representatives to make it even look like close to what they have planned to do so.
Finally the voice of the people for justices was  louder, for their is so much injustice going on in Homeland.

The video says it all.

Sunday, April 28, 2013

ሰበር ዜና! ጀግኖች ኢትዮጵያዊያን ዛሬም በኦስሎው፣ ታሪክ ሰሩ!


ወያኔ በልማት ስም ገንዘብ ለመቃረምና ደጋፊ ለመመልመል አቅዶ ከሳምንት በፊት በስታቫንገር አንዲሁም በዛሬው እለት ደግሞ በኦስሎ ስብሰባ ለመጥራት ታቅዶ የነበረ ቢሆንም ሳይሳካላቸው የውርደት ካባቸውን ለብሰው መሄድ እጣፋንታቸው እንዲሆን የግድ ሆኗል፡፡ እንደሚታወቀው ባለፈው ሳምነንት ማለትም እንደ ኢሮፓ አቆጣጠር ሚያዝያ 20፣ 2013 በነበረው ስብሰባ ላይ ኢትዮጵያዊያን ከየተለያዩ ቦታዎች በመሰባሰብ የወያኔ አምባሳደር በስዊድን የሆኑትንና የዲያስፖራ ተወካዩን ከስብሰባ በማባረር ከፍለውበት የነበረውን አዳራሽ ተረክቦ ኢትዮጵያዊያን የራሳቸውን አጀንዳ እና ለተፈናቀሉት ወገኖቻችን እርዳታ የሚሆን ገቢ እንዲሰበሰብና ይህን አምባገነንና ዘረኛ ቡድን መታገል የሚቻለው በ አንድነት መሆኑን ሁሉም የሚስማሙበትና እጅ ለእጅ ተያይዘን መታገል እንዳለብን አስምረው፣ ከ አንድ ሳምንት በሗላ ለሚደረገው የወያኔ ገቢ ማሰባሰቢያ ይህንኑ ድል መደገም ያለበት መሆኑን በመስማማት ነበር የተለያዩት፡፡
ይህንንም ተከትሎ የስታቫንገሩን የወያኔ ፕሮግራም ለማክሸፍ ከፍተኛው ሚና የተጫዎተውን ግብረ-ሓይል በማጠናከር ሳምንቱን ሁሉ ውጤታማ ሥራ ለማድረግ የሙስሊም ወንድሞቻችንን፤ ኦሮሞና ሶማሌ ኢትዮጵያዊያንን በማስተባበር ሌት ከቀን  ሲሰራ ሰነንብቷል፡፡ የጀግኖች ኢትዮጵያዊያንን ከፍተኛ ዝግጅትና ቅስቀሳ ሲከታተሉ የነበሩ የወያኔ ቅጥረኞችና አገላጋዮች ስብሰባ ሊደረግ ታቅዶበት የነበረውን አዳራሽ የስብሰባው ሰዓት ሊደርስ አንድ ሰዓት ተኩል ሲቀረው የመሰብሰቢያው አዳራሽ በፀጥታው፣ በጥራቱና በደህንነቱ በታወቀው ራድሰን ብሉ ሆቴል እንደሚካሄድ አስታውቀው፣ ስብሰባውን ለመሳተፍ ግን ህጋዊ መታወቂያ እንደሚያስፈልግ ተገልፆ የሞባይል አጭር መልዕክት ተላለፈ፡፡ ጀግኖች ኢትዮጵያዊያን ስብሰባው ይካሄድበታል ተብሎ ከታሰበበት አዳራሽ አካባቢ ከአስር ሰዓት ጀምሮ ወደዚያ የሚያልፈውን የወያኔ ቅጥረኛ ለመቃኘት ወረውት የነበረ ቢሆንም ዘግይቶ የመጣውን አጭር የሞባይል መልዕክት ማለትም የስብሰባ ቦታ መቀየር በመረዳት፣ ወደዚያው ተመመ፡፡
ብዙዎቹ ኢትዮጵያዊያን ከመድረሳቸው በፊት በገቡት የወያኔ ተወካዮች በመበሳጨቱ ወደ ሆቴሉ ለመግባት በነበረው ግብግብ፣ ምንም ዓይነት ሰው እንዳይገባ ተከለከለ፡፡ ይህንንም ተከትሎ የኢትዮጵያዊያንን ቁጣ ለማስቆም ከ15 መኪና በላይ የፖለስ ሃይል የተጨመረ ቢሆንም የጀግኖች ኢትዮጵያዊአንን ቁጣና እልህ መቋቋም አልቻሉም ነበር፡፡ አካባቢው የግልና ተቃውሞውም ህገወጥ እንደሆነ በማስረዳት  ከአካባቢው ገለል ለማድረግ ቢሞክሩም አልተቻለም፡፡ ኢትዮጵያዊያኑ በሆቴሉ የታደሙት የወያኔ ቅጥረኞት ወጥተው ካልሄዱ አካባቢውን ለቀን አንሄድም፤ ይውጡ እንለቃለን፤ ይውጡ እንለቃለን፤ ይውጡ እንለቃለን፤ ይውጡ እንለቃለንበማለት አብዘተው ጮሁ፡፡ ይህንንም ተከትሎ ሁለት ሴቶች እህቶቻችንና ዘጠኝ ወንድሞቻችን ለሰዓታት ታስረው የተፈቱ ሲሆን፤ ፖሊስም የተቃውሞውን ሓይለኝነት በማየት የወያኔ ተወካዮችንና የስብሰባው አስተባባሪዎች በጓሮ በር ማለትም በመኪና ማቆሚያ በኩል ከህዝብ ሰውረው ከሆቴሉ ሸኝተዋቸዋል፡፡
ከዚያም ኢትዮጵያዊያን አያ ሆሆ ማታ ነው ድሌ፤ አያ ሆሆ ማታ ነው ድሌ፤ አያ ሆሆ ማታ ነው ድሌ እያሉ በመዝለል ደስታቸውን ገልጸዋል፡፡ የሚከተሉትን የፎቶ ትዕይንት ይመልከቱ፡፡
DSC_0010DSC_0012DSC_0015DSC_0922DSC_0931DSC_0938Arrestationarrestation 2.

ሰበር ዜና በአባይ ስም ዶላር ለመሰብሰብ በሲውዲን የወያኔ አምባሳደር ወደ ኖርዌይ ተጉዛ ለ ሁለተኛ ጊዜ በ ኦስሎ ውርደት ተከናንባ ተመልሳለች፥፥


ኣብረሃ ደስታ በአሸባሪነት ሊታሰር ነው



ወደ ማታ ኣከባቢ በማላውቀው ስልክ ተደወለልኝ። ከተወሰነ ሰጣገባ በኋላ “ኣንተ ኣሸባሪ ነህ። በኣሸባሪነት እንደምንትያዝ ኣትጠራጠር” ኣለኝ።አብርሃ-ደስታ
“ኣዎ ኣሸባሪ ነኝ። ያሸበርኳቹ ያህል ነው የሚሰማኝ። ምክንያቱም ባላሸብራቹ ኑሮ የኔን ፌስቡክ ለማስዘጋት ባልተረባረባቹ ነበር” መለስኩለት።
ስልኩን ጀሮየ ላይ ጥርቅም ኣድርጎ ዘጋው።
“ለካ እንዲህ ለነፃነት የሚቆሙ፣ የፈለጉትን የሚፅፉ፣ ስለ ፍትሕ የሚዘምሩ ግለሰዎች ናቸው ‘ኣሸባሪ’ ተብለው በኣምባገነን ገዢዎች የሚሰየሙት” ስል ኣሰላሰልኩ። “ኣሸባሪ” የሚለውን ስም ወድጀዋለሁ። “ኣሸባሪ” መሆን ደስ ይላል። ጥያቄው መሆን ያለበት ‘የሚሸበረው ኣካል ማነው?’ (ሰለማዊ ህዝብ ወይስ ገዢው መደብ) ነው። ምናልባት እኔ “ኣሸባሪ” ከተባልኩ በኔ የተሸበረው ገዢው ፓርቲ ብቻ ነው።
ግን ገዢው መደብ የሚያሸብሩ ሰዎች ሌላ ስም ሊሰጣቸው ይገባል እላለሁ። ምክንያቱም መሪዎቻችን ስልጣናቸውን ያለ ኣግባብ ተጠቅመው ሰለማዊ ህዝብ ሲያሸብሩ ምን ብለን ልንሰይማቸው ነው? መንግስትን የሚቃወም “ኣሸባሪ” ከተባለ፣ ህዝብን በጭቆና የሚያሸብር ባለስልጣንስ ????
ከጭቆና በላይ ሽብር የለም። ምክንያቱም ጭቆና ማስፈራራት፣ ግድያ ……… ምናምን (ሰው ፈርቶና ተሸብሮ ሳይቃወም እንዲገዛ ለማድረግ የሚደረጉ ጥረቶች የሽብር ተግባራት ናቸው)። “ሽብር” ማለት’ኮ ኣንድ ኣካል ራሱ የሚፈልገውን ተግባር በሌሎች ሃይል በመጠቀም ወይ በማስፈራራት ለመጫን ሲሞክር ነው። ሌሎችን እያስፈራራ ያለው ማነው??? እኔ ወይስ ገዢው ፓርቲ? ኣሸባሪ ማነው? ማነው ሰለማዊ ዜጎችን በማፈን እያሸበረ ያለው?
ይሄንን ሳስብ ከቆየሁ በኋላ ትንሽ ቀለል ኣለኝ። ‘መንግስትን መቃወም ትክክል ነው’ ማለት ነው ብዬ በራሴ ተፅናናሁ። ምክንያቱም መቃወም ኮ የሚያስፈልግ የምንቃወምበት ምክንያት ሲኖረን ነው። ይሄው ምክንያት ኣገኘን። የሚቃወም ሰው ማፈን ዓፈናን በመቃወም መንግስትን ለመቃወም በቂ ምክንያት ነው።
ዛሬ ጠዋት ኣንዳንድ መረጃዎች ደረሱኝ። ባለፈው ቅዳሜና እሁድ (ለህወሓት ጉባኤ ድጋፍ ለማሰባሰብ ሰልፍ በተጠራ ግዜ) ስለ ሰልፉ ኣስፈላጊነትና የትእምት ንብረትነት ፅፌ ነበር። ከዚህ በመነሳት የተወሰኑ የፖሊስ መኮነኖችና የደህንነት ተጠሪዎች በጉዳዩ ተወያይተው እኔን ለማሰር ሓሳብ ኣንስተው ምክንያት በሚያፈላልጉበት ግዜ ሳይስማሙ ቀርተዋል።
የማክሶኞ ኣጀንዳ ባብዛኛው ‘የመለስ ታሪክ’ መተረክ ነበር (ከጉባኤው ኣጀንዳ ዉጭ)። ሰኞ በፃፍኳቸው ነጥቦች (ስለ ጉባኤው ኣሰራርና የድርጅት ሥራ ተግባራት፣ ስለ ፍትሕ ጉድለት፣ ስለ ህወሓት ምስጢር ባጠቃላይ) ትናንት ሮብ ኣጀንዳ ሁነው ውለዋል። “ሚስጢር እየወጣ ነው። የጉባኤው ምስጢር መጠበቅ ኣለበት” ተብሎ ከመድረክ ከባድ ማስጠንቀቅያ ተሰጥተዋል። ከቤትም “ምስጢራችን ከሌሎች ከምንሰማው በራሳችን የሚድያ ሰዎች ቢነገር ኣይሻልም ወይ?” የሚል ኣስተያየት ስለተሰጠ ሬድዮ ፋና ኣንዳንድ ነጥቦች (በተለይ ስለተቀነሱ የህወሓት ኣመራር ኣባላት ስም ዝርዝር) ማሰራጨቱ ሰምቻለሁ።
ሌላው ሳይታሰብ (በህወሓት ጉባኤ ታሪክ ለመጀመርያ ግዜ) ኣጀንዳ የሆነው የትእምት ጉዳይ ነው። “ትእምት ላይ ያነጣጠረ ዘመቻ ተከፍቶብናል” የሚል ሓሳብ ኣንስተው ድርጅቱ ጥሩ እየሰራ እንደሆነ ተሳታፊዎችን ለመጀንጀን ሞክረዋል። ትእምት ሌላ የብረታ ብረት ፋብሪካ እንደሚከፍትና በመሰቦ ሲሚንቶ በኩል ደግሞ የፕላስቲክ ፋብሪካ (በ ስድስት ቢልዮን ብር ካፒታል) እንደሚገነባ ተነግረዋል።
ትናንት ማታ ዛሬ ለሚመረጡ 45 የማእከላዊ ኮሚቴ ኣባላት 50 እጩዎች መርጠዋል። ኣርከበ ዕቁባይ፣ ስዩም መስፍንና ብርሃነ ገብረክርስቶስ ጨምሮ ዘጠኝ ሰዎች ከማእከላዊ ኮሚቴ ኣባልነት ተቀንሰዋል። ኣብዛኞቹ (የተቀነሱት) ከነኣርከበ ዕቁባይ ቡድን ናቸው። ጉባኤው ዛሬ ይጠናቀቃል።
ባጠቃላይ ግን በፌስቡክ የሚነገሩ ወሬዎች በህወሓት ጉባኤ ከፍተኛ ጫና ፈጥረዋል። በርስበርሳቸው ኣለመተማመንና መወቃቀስ ተያይዘውታል። የኔ ፌስቡክ ለማስዘጋት ከተቋቋመ ግብረ ሃይል የተወሰኑ የማእከላዊ ኮሚቴ ኣባላት በኣስተባባሪነት ተሳትፈዋል። ከተወሰነ ኣከባቢ ወይ ወረዳ በመጡ ሰዎች (You may guess) የኔን ፌስቡክ እንዲዘጋ ለማድረግ “የራሱ ስም ኣይደለም” በማለት (ጉባኤው በሰላም እንዲጠናቀቅ) ወደ Facebook Admin ሪፖርት እንዲያደርጉ መመርያ ተሰጥተዋል።
ኣዎ ኣሸባሪ መባል ደስ ይላል። ህወሓቶች እንዲህ በጣም ፈሪዎች መሆናቸው ኣላውቅም ነበር። በፌስቡክ እንዲህ ይሸበራሉ ብዬ ኣላሰብኩም ። ኣሁን ግን ራሳቸው ኣጋለጡ።
የህዝቦች ነፃነት ይቅደም።

ESAT Weekly News 28 April 2013


Friday, April 26, 2013

አዋሽ ወንዝ በጥቂት ወራት ውስጥ የሚሊዮኖችን ህይወት ለአደጋ አጋልጦ ከጥቅም ውጭ ሊሆን ይችላል ተባለ



ኢሳት ዜና:-ብሉበርግ ትናንት ይዞት በወጣው አስደንጋጭ ዘገባ በስምጥ ሸለቆ ውስጥ የሚገኘው የበሰቃ ሀይቅ በመስኖ ስራዎች እና በተፈጥሮ እንቅስቃሴ ምክንያት ጨዋማነቱ በ15 እጥፍ በመጨመሩ በሰኔ ወር ዝናብ ከዘነበና  ሀይቁ ወደ አዋሽ ወንዝ መፍሰስ ከጀመረ ፣ ወንዙን ለመጨረሻ ጊዜ ከጥቅም ውጭ ያደርገዋል ሲል ጠቅሷል።.
ስራ ጋር በተያያዘ በተፈጠረ የአፈር መሸርሸርና በመሬት የውስጥ እንቅስቃሴ ምክንያት ጨዋማነቱ ከመጠን በላይ እየጨመረ በመሄዱ የሚሊዮኖችን ህይወት ለአደጋ አጋልጧል።
በውሀ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር የከርሰ ምድር ውሀዎች ዋና ሀላፊ የሆኑት አቶ ተስፋ ታደሰ ፣ “ሀይቁ በራሱ ጊዜ ወደ አዋሽ መፍሰስ ከጀመረ የአዋሽ ወንዝ ለዘላለሙ ከጥቅም ውጭ ይሆናል።” ብለዋል።
የላይሻው አዋሽ ወንዝ የውሀ ጥናት ባለሙያ የሆኑት አቶ  እንደሻው ታደሰ  ደግሞ የሰኔ ዝናብ ከመዝነቡ በፊት ሀይቁ ወደ አዋሽ ወንዝ እንዳይፈስ ወሳኝ ጥረት መደረግ አለበት ሲሉ አሳስበዋል። ባለሙያው እንደሚሉት ከአዲስ አበባ በስተምስራቅ የሚገኘው ሀይቅ ወደ ወንዙ ከፈሰሰ ከተሞችን ከማጥለቅለቅ አልፎ የአካባቢውን አርብቶ አደሮች ሊያፈናቅላቸው ይችላል።
ብሉበርግ እንደሚለው መንግስት ላለፉት 14 አመታት የውሀ ፓምፖችን በመጠቀምና ቦዮችን በመስራት በሰቃን ለመቆጣጠር ጥረት ቢያደርግም አልተሰካላትም።
በአለማያ ዩኒቨርስቲ የሲቪል ኢንጂነርግ ረዳት ፕሮፌሰር የሆኑት መገርሳ  ዲንቃ እንደተናገሩት በአካባቢው የሚደረገው የመስኖ ስራ  ችግሩን አባብሶታል። ፕሮፌሰሩ የመሬት እንቅስቃሴው ለሀይቁ መስፋፋት ተጨማሪ አስተዋጽኦ አድርጎ ሊሆን እንደሚችልም ገልጸዋል።
የመንግስት ባለስልጣናት ከዚህ ቀደም በላይኛው አዋሽ ላይ ሲካሄድ የነበረው የመስኖ እንቅስቃሴ ችግሩን እንዳባባሰው ለማመን ተገደዋል።
በመተሀራ አካባቢ ያለውን የላይኛው የአዋሽ አግሮ እንዱስተሪ ኢንተርፕራይዝ፣ የሼክ ሙሀመድ አላሙዲ ንብረት የሆነው ሆራይዞን ፕላንቴሽን በቅርቡ መግዛቱ ይታወሳል። የሆራይዞን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ጀማል አህመድ እንዳሉት በላይኛው አዋሽ ላይ የሚካሄደው የመስኖ ስራ ምንም አይነት የአካባቢ ተጽኖ አላመጣም፤ ይሁን እንጅ ድርጅታቸው ችግሩን ለማጥናት ከመንግስት ጋር ለመተባበር ዝግጁ ነው ብለዋል።
የበሰቃ ሀይቅ ወደ አዋሽ ወንዝ ከፈሰሰ 23 ሚሊዮን ዶላር የወጣበት የሼክ ሙሀመድ አላሙዲ ድርጅት፣ ከህንድ አገር በተገኘ የ640 ሚሊዮን ዶላር ብድር የማስፋፍያ ስራ የሚሰራለት የተንዳሆ ስኳር ፋብሪካ፣ 30 ሺ ነዋሪዎች የሚኖሩባቸው  መተሀራ እና አዲስ ከተማ እንዲሁም የመተሀራና የተንዳሆ የስኳር ፋብሪካዎች ሙሉ በሙሉ ከጥቅም ውጭ ይሆናሉ።ው በመካከለኛው አዋሽ አካባቢ ያለው የአምቢባራ ቢዝነዝ ግሩፕ ንብረት የሆነው የጥጥ እርሻ እና በአጣቃላይ ድምራቸው 5 ቢሊዮን ዶላር ካፒታል ያላቸው ፕሮጀክቶች በሙሉ ከጥቅም ውጭ ይሆናሉ።
“ሰኔ ላይ ዝናብ ከዘነበ ሁሉም ነገር ተፈጸመ” ሲሉ የውሀ ባለሙያው  አቶ እንዳሻው አስጠንቅቀዋል።
የበሰቃ ሀይቅ ጨዋማነት እየተፋጠነ የመጣው የክልሉ መንግስት በ467 ሚሊዮን ብር ወጪ ለመስኖ ስራ የሚያገለግለውን የፈንታሌ ቦይ መገንባት ከጀመረ ጊዜ ጀምሮ መሆኑን ደግሞ በኢትዮጵያ ውሀ ስራዎች፣ ዲዛይን እና ሱፐር ቪይዢን ኢንተርፕራይዝ ስራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ እንግዳ ዘመድኩን ተናግረዋል።
ውሀ በፓምፕ ለማስወጣት የተደረገው ጥረት አልተሳካም፣ የሚሉት የመንግስቱ ባለስልጣን አቶ ተስፋየ ደግሞ አዋሽ ወንዝ በራሱ 4 በመቶ ጨውነት ያለው በመሆኑ ከዚህ መጠን ካለፈ ውሀውን ከጥቅም ውጭ ያደርገዋል ብለዋል።
ፕሮፌሰር መገርሳ ደግሞ ” የሀይቁ ጨውነት በምንም ይጨምር በምንም፣  በሰቃ ሀይቅ ወደ አዋሽ ወንዝ መፍሰሱ እና የመተሀራ ስኳር ፋብሪካን በሚቀጥሉት ጥቂት አመታት ውስጥ ማውደሙ አይቀሬ ነው።  ተንዳሆን ጨምሮ በታችኛው የውሀ ክፍል የሚካሄዱ ፕሮጀክቶችም በሙሉ በሙሉ ይወድማሉ” ብለዋል ፕሮፌሰሩ። ረዳት ፕሮፌሰር መገርሳ የአዋሽን ውሀ ለመጠጥነት በሚጠቀሙት የአፋር ተወላጆች ላይ የከፋ አደጋ እንደሚከሰትም ገልጸዋል።
ምንም እንኳ የመንግስት ባለስልጣናትና ባለሙያዎች በጋራ የበሰቃን ሀይቅ እያጠኑ ቢሆንም ፣ አቶ ተስፋየ እንደሚሉት ለጊዜው መንግስት ስለሚወስደው እርምጃ አቅጣጫው ጠፍቶበታል።
በአካባቢ ጥበቃ ዙሪያ መረጃዎችን በማሰባሰብ ችግሩን ለማሳወቅ ጥረት ሲያደረግ የነበረው የፎቶ ጋዜጠኛው ቢኒያም መንገሻ ፣ ሀይቁ የፈጠረውን አደጋ ለመንግስት ለማቅረብ ተደጋጋሚ ሙከራ ቢደርግም በመንግስት በኩል የተሰጠው ትኩረት አናሳ መሆን ችግሩን እንዳባባሰው ተናግሯል
3 ኪሎ ሜትር ስፋት ብቻ የነበረው የበሰቃ ሀይቅ በአለፉት አርባ አመታት ውስጥ ወደ 45 ኪሎሜትር ከፍ ማለቱን በዘገባው ተመልክቷል። ሟቹ ጠቅላይ ሚኒሰትር አቶ መለስ ዜናዊ አፍረካ የአካባቢ ጠበቃ እየተባሉ ሲወደሱ እንደነበር ይታወሳል።

የህዳሴ ግድብ ኃይል ጣቢያ በ1 ቢሊየን ዶላር የቻይና ብድር ሊሠራ ነው


ከታላቁ የኢትዮጵ ህዳሴ ግድብ የሚመነጨውን ኃይል የሚያስተላልፍና የሚያከፋፍል ጣቢያ ለመገንባት የሚያስችል የኮንትራት ስምምንት ተፈረመ። የማስተላለፊያና የማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታው 1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ይጠይቃል።
የኮንትራት ስምምነቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ምህረት ደበበና የቻይናው ኤሌክትሪክ ፓወር ኢኩዊፕመንት ና ቴክኖሎጂ ኩባንያ ተወካይ ሚስተር ዥያ ዥኪያንግ ፈርመዋል።
አቶ ምህረት በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት ለፕሮጀክቱ ማስፈጸሚያ ከሚውለው ገንዘብ 85 በመቶ ከቻይና መንግሥት በብድር የሚገኝ ሲሆን፣ ቀሪው በኢትጵያ መንግሥት ይሸፈናል።
የጣቢያው ግንባታ በቀጣዮቹ 30 ቀናት ውስጥ ይጀመራል ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፣ሥራው በ24 ወራት ጊዜ ውስጥ ሙሉ በሙሉ ይጠናቀቃል ተብሎ እንደሚጠበቅም ተናግረዋል።
የፕሮጀክቱ ጥናትና ዲዛይን ሥራ ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች መካሄዱን ገልጸው፣ በግንባታው ላይ የሁለቱም አገሮች ባለሙያዎች በጋራ እንደሚሳተፉ አስረድተዋል።
የኃይል ማስተላለፊያ መሥመሩ ባለ 500 እና 400 ኪሎ ቮልት የመሸከም አቅም ያለው ሲሆን፣ አጠቃላይ ርዝመቱ 700 ኪሎ ሜትር ይሸፍናል።
አቶ ምህረት እንዳሉት መሥመሩ ወደፊት በዓለም አቀፍ ደረጃ በኃይል ማስተላለፍ መስክ ለሚደረገው ግንኙነት ከፍተኛ ጠቀሜታም ይኖረዋል። ከግድቡ የሚመነጨውን ኃይል ከዋናው ብሄራዊ ሃይል ማዕከልር ለማገናኘት ከደዴሳ -ሆለታ፣ሰበታ ሁለት እንዲሁም ከሆለታ ወደ ሰበታ ከዚያም አቃቂ ወዳለው የኃይል ማከፋፊያ ጣቢያ እንዲገባ ይደረጋል።
ሚስተር ዥኪያንግ እንዳሉት ኩባንያቸው ፕሮጀክቱን በተያዘለት ጊዜ ውስጥ አጠናቅቆ እንደሚያስረክብ ገልጸዋል።
በፊርማው ሥነ ሥርዓት ላይ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን የቦርድ ሰብሳቢ ዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል፣የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር አቶ ዓለማየሁ ተገኑና ሌሎችም ከፍተኛ የመንግስት ባለሥልጣናት መገኘታቸውን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዘግቧል።
***************
Source: Ethiopian News Agency – April 26, 2013. Originally titled “የህዳሴ ግድብ የሚመነጨውን ኃይል የማስተላለፊያና የማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ለማከናወን ስምምነት ተፈረመ”.

የኢሚግሬሽንና ዜግነት ጉዳይ ዋና መምሪያ በሙስና መጨማለቁን አንድ ጥናት አመለከተ


መጋቢት ፲፱ (አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-በብሔራዊ የመረጃ ደህንነት አገልግሎት የኢሚግሬሽንና ዜግነት ጉዳይ ዋና መምሪያ የመንገደኞች የይለፍ ማረጋገጫ
አሰጣጥ እና የአገልግሎት ክፍያ ገንዘብ ገቢ አሰባሰብ የአሰራር ሥርዓት በሙስናና ብልሹ አሰራር የተጨማለቀ
መሆኑን ከፌዴራል የስነምግባርና የጸረ ሙስና ኮምሽን የተገኘ አንድ ጥናት አመለከተ፡፡
በመምሪያው በይለፍ ማረጋገጫ አሰራር ስርዓት ላይ ለሙስናና ብልሹ አሰራር የሚያጋልጡ ተብለው በጥናቱ ከቀረቡት
ሁኔታዎች ውስጥ የመረጃ አያያዝና ዘመናዊ ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ደካማ መሆን፤የሙስናና ብልሹ አሰራር
መንሰራፋት፣የሰለጠነ የሰው ኃይል አለመመደብ፣ግልጽ የስራ መመሪያና ማኑዋል ያለመኖር የሚሉት ተጠቅሰዋል፡፡
ለሠራተኞች የሚያገለግል የሥነምግባር መመሪያ ባለመኖሩ ጠንካራና አስተማሪ የሆነ አስተዳደራዊና የዲሲፕሊን እርምጃ ለመውሰድ ባለመቻሉ  ደላሎች፣ የካውንተር ሠራተኞችና ኃላፊዎች ተባባሪና የጥቅም ተጋሪ በመሆን መንገደኞች በፎርጅድ ፓስፖርትና ቪዛ ከአገር እንዲወጡ ያደርጋሉ። ቪዛ በሕገወጥ መንገድ ከተለያዩ ኤምባሲዎች እንዲወጡና ቪዛ ከሌሎች አገሮች እንዲመጣ በማድረግ መሸጥ፣ ቪዛ የሚሰጡ አገሮች  ለተጓዦች የሰጡትን የቪዛ ሊስትና ቁጥር ለኢሚግሬሽን በሚልኩበት ጊዜ ቦሌ አንዳንድ የመ/ቤቱ ሠራተኞች ዝርዝሩን የመሰረዝና የመፋቅ፣ ከዚያም በማመሳሰል ቪዛውን ፓስፖርት ላይ በመምታት ገንዘብ እንደሚያጋብሱ ተመልክቷል።
እንዲሁም ደላሎችና የካውንተር ሠራተኞች በምን ሰዓት ማን እንዳለ በተለምዶ በመለየት መንገደኛውን በመላክና በሕገወጥ መንገድ እንዲያልፍ በማድረግ፣ ቪዛ በማያስፈልገው የኬንያን በመሳሰሉ ፓስፖርቶች በመጠቀም  መንገደኛው በቦሌ በኩል ካለፈ በኋላ ኬንያ ሲደርስ የሌሎችን አገሮች ቪዛ በመለጠፍ ትራንዚት ነን እንዲሉ በማድረግ፣ ከተለያዩ አገሮች የተባረሩ ተጓዦችን ኤርፖርት ከያዙና አስፈላጊውን መረጃ ከሰነዳቸው ላይ ከወሰዱ በሁዋላ ምርመራ መከናወን ሲገባው በጥቅማጥቅምና በቸልተኝነት እንዲበተኑ በማድረግ ገንዘብ እየተዘረፈ መሆኑ ተመልክቷል።
መ/ቤቱ ለመንግሥት ከፍተኛ ገቢ ከሚሰበስቡት ተቋማት መካከል አንዱ ቢሆንም  የፋይናንስ አስተዳደርና
ሌሎች ጉዳዮች ላይ ተገቢውን ክትትልና ቁጥጥር ለማከናወን የሚችል የውስጥ ኦዲት የሥራ ክፍል የለውም፡፡ በዚህም የተነሳ ይላል ጥናቱ ወቅታዊና ድንገተኛ ኦዲት በአግባቡ ለማድረግ ባለመቻሉ የሚሰበሰበው ገቢ በትክክል ለመንግስት ገቢ መደረጉን ለማረጋገጥ አልተቻለም።  በሚፈጠሩ ችግሮች ላይ ወቅታዊ የማስተካከያ እርምጃ አለመውሰድ፣በፌዴራል ዋናው ኦዲተር መ/ቤት ዓመታዊ ኦዲት ሪፖርት መሠረት የማሻሻያ ሥራ አለማከናወን የአሰራር ስርዓቱ ለሙስናና ብልሹ አሰራር የተጋለጠ እንዲሆን አድርጎታል፡፡
በመ/ቤቱ በሁለቱም የሥራ ክፍሎች ተመድበው የሚሰሩ አብዛኛዎቹ ሠራተኞች ብቃታቸውና ክህሎታቸው አነስተኛ
መሆኑም ተመልክቷል።
ለሰራተኞች የስራ ላይ ሥልጠና የሚሰጥ ቢሆንም እንኳን የፎርጀሪና ማጭበርበር መንገዶች እንደ ወቅታዊ ቴክኖሎጂ ደረጃ የሚሻሻሉና የሚለወጡ በመሆኑ በብቃት ለመከላከል የሚያስችል የአሰራር ሥርዓት አለመዘርጋቱን በጥናቱ ተጠቅሷል፡፡
የአሰራር ሥርዓት ችግሩን ለመፍታት በሥራ ክፍሎች አሰራር ሥርዓት ላይ በባለሙያ እጥረት ምክንያት እያጋጠመ
ያለውን ችግር ለመቅረፍ ብቃትና ክህሎት ያለውን ባለሙያ ለማስመደብ ወይም ለመቅጠር በቅድሚያ ለሥራ መደቦች
የሚያስፈልገውን የትምህርት ዝግጅትና የሥራ ልምድ እንዲወጣለት በማድረግ ማሟላት፣ ከዚህም በተጨማሪ አዲስ
ሠራተኞች ሥራ ከመጀመራቸው በፊት ስለአሰራሩ በቂ ስልጠና የሚያገኙበት ሁኔታ ማመቻቸትና በሥራ ላይ እያሉ
የማጠናከሪያ ሥልጠና እንዲሰጥ ማድረግ በጥናቱ የተጠቆመ የመፍትሄ ሀሳቦች ናቸው፡፡
የ ተለያዩ የሥራ ክፍሎችን የሚመሩ የሥራ ኃላፊዎች ሥራውን የሚመሩት በግልፅ መመሪያ ሳይሆን በልምድ፣ በቃል ትዕዛዝ እና በማስታወሻ መሆኑ፣ ይህ ዓይነቱ አሰራር ደግሞ ግለሰቦች እንደፈለጉት ሥራውን የሚመሩበት በመሆኑ በተፈለገው ጊዜ የሚሰራበት በማይመች ጊዜ እንዲቆም የሚታዘዝበት አሰራር ዘይቤ እንዲከተልና ለግለሰብ አመለካከት የተጋለጠ መሆኑም በጥናቱ ተጠቅሷል፡፡
የይለፍ ማረጋገጫ አሰጣጥ አሰራር ሂደት በባህሪው በየቀኑ በርካታ ተገልጋዮችና መንገደኞች የሚስተናገዱበት የሥራ ክፍል ቢሆንም በአሰራር ሥርዓቱ ላይ የመንገደኛው የሀሳብ መስጫ አስተያየት ማቅረቢያ ቅፅም ሆነ ሳጥን አለመኖር፣ የቅሬታ ማስተናገጃ ክፍልም ሆነ ኦፊሰር አለመደራጀት፣ ተገልጋዩ በአቅራቢው ችግሩን የሚፈታበት ሥርዓት ያልተዘረጋ ስለሆነ ችግር ሲያጋጥመው ከቦሌ ወደ ዋናው መ/ቤት እንዲመጣ ማድረግና ማጉላላት ስላለ ለሙስናና ብልሹ አሰራር በቀላሉ የተጋለጠ ሆኗል
ከአሰራር ጋር በተያያዙ የተጠቀሱት ሌሎች ችግሮች ከአገልግሎት የሚሰበሰብ ገንዘብ በየእለቱ ወደ ባንክ ገቢ
አለማድረግ፣ ከመጠን በላይ በካዝና ገንዘብ ማሳደር፣ የዕለት ገንዘብ ሰብሳቢዎች በየዕለቱ የሚሰበስቡትን ገንዘብ
አግባብ ያለው ወቅታዊ ቁጥጥርና ክትትል እየተደረገበት ለባንክ ገቢ አለመሆን፣ የሂሳብ ምዝገባ በየቀኑ
ስለማይመዘገብ አግባብ ያለውን ክትትልና ቁጥጥር ማድረግ አለመቻልና የገቢ ሒሳብ ምዝገባ ሳይከናወን ለረጅም ወራት
ማከማቸት፣ የገቢ ሒሳብ እንቅስቃሴ መዝገብ በኮምፒውተር በየጊዜው ስለማይመዘገብ ሒሳቡን በወቅቱ አለመዝጋት፣
የገንዘብ መቀበያ ደረሰኞች አያያዝና አጠቃቀም ብክነት ያለበት መሆን እንዲሁም የሚሰበሰበው
ገንዘብና ወደ ባንክ ገቢ የሚሆነው ገንዘብ ከደረሰኞች ጋር በወቅቱና በዕለቱ ማመዛዘኛ /balance/
አለመሰራት የሚሉት ይገኙበታል፡፡
ከመረጃ አያያዝ ጋር በተገናኘ ከተጠቀሱት ችግሮች መካከል ደግሞ ውዝፍ ሥራዎች በመብዛታቸው ምክንያት
ሥራዎችን በዘመቻ በመስራት የሥራ ጫና መኖር፣ ፋይሎች በዓመታትና በየወሩ ተለይተው በቀላሉ የሚገኙና የተደራጁ አለመሆኑ ምክንያት ለክትትልና ለቁጥጥር አለመመቸት፣ ከክልል ኬላዎች ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች ጋር የተቀናጀ ግንኙነት ባለመኖሩ የሰበሰቡትን ገንዘብ በወቅቱ በባንክ በኩል ፈሰስ አድርገው ማስረጃውን እንዲልኩ አለማድረግና የገቢ ደረሰኝ በወቅቱ አለመስራት፣ ፋይሊንግ ሲስተሙ በዘመናዊ መልክ የተደራጀ አለመሆን፣ ከገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ማዕከላዊ ሒሳብ መምሪያ ጋር ተናቦ ሪፖርቶችን በወቅቱ አለማዘጋጀት፣ ገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር፣ ብሔራዊ ባንክና በመሥሪያ ቤቱ መካከል ልዩነት መኖር ፣ የሚሉት ተካተዋል።
ብሔራዊ የመረጃ ደህንነት አገልግሎት የኢሚግሬሽንና ዜግነት ጉዳይ ዋና መምሪያ ፓስፖርት ለማውጣትም ሆነ
ለማሳደስ ዜጎች እስከ አራት ወራት የሚደርስ ቀጠሮና መጉላላት የሚደርስባቸው ሲሆን ቀልጣፋ አገልግሎት ለማግኘት
በነፍስወከፍ እስከ አምስት ሺ ብር ጉቦ በመጠየቅ ላይ መሆናቸውን በቅርቡ መዘገባችን ይታወሳል፡፡
መ/ቤቱ በቂ የትምህርት ዝግጅት በሌላቸው በቀድሞ የህወሀት / ኢህአዴግ ታጋዮች ከላይ እስከታች የተሞላ መሆኑም ይታወቃል፡፡

ESAT Abay bond Protest in Norway April 2013


Wednesday, April 24, 2013

የከሸፈዉን ቦንድ ሽያጭ የተሳካ ገቢ ማሰባሰቢያ በኖርዌይ ስታቫንገር አድረኩ አለ


በኖርዌይ ስታቫንገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የሚውል75 ሺ የኖርዌይ ክሮነር /ሩብ ሚሊዮን ብር/  ቦንድ መግዛታቸውን በስቶክሆልም የኢፌዲሪ ቆ/ጀ/ፅ/ቤት አስታወቀ ፅህፈትቤቱ እንደገለፀው በኖርዌይ ስታቫንገር የሚኖሩ  ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያ በተለያየ ሽፋን የተሰባሰቡ ፀረሰላምና ፀረ ልማት ሃይሎች ያቀነባበሩት የተቃውሞ ሰልፍ ሳይገድባቸው ለህዳሴው ግድብ ግንባታ የሚውል ቦንድ በመግዛትለአገራቸው ልማት ያላቸውን ቁርጠኝነት በተግባር አስመስክረዋል ብሏል፡፡

http://www.ertagov.com/amharic/index.php/component/k2/item/586

ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያም አልሞቱም



(EMF) የቀድሞው የኢትዮጵያ መንግስት ፕሬዘዳንት የነበሩት ኮ/ል መንግስቱ ኃይለማርያም እንደሞቱ ተደርጎ በኢትዮጵያ እና ከኢትዮጵያ ውጪ ብእሚገኙ ሚዲያዎች ሲወራ ሰንብቷል። ኢ.ኤም.ኤፍ. ከኮ/ል መንግስቱ የቅርብ ቤተሰብ እንዳረጋገጠው ከሆነ፤ ወሬው ከወሬ ያላለፈ የውሸት ዜና ነው ብለዋል። ከዚህ በፊት ከኮሎኔል መንግስቱ ጋር ባደረግነው ቃለ ምልልስ፤ “ወያኔ እንኳንስ በህይወት እያለሁ፤ ሞቼ አስከረኔንም አያገኘውም።” የሚል ምላሽ መስጠታቸው ይታወሳል። እስካሁን የዜና ምንጭ ተብሎ የሚጠቀሰው የዙምባብዌ ቴሌቪዥን ነው። ሆኖም ቴሌቪዥኑ ይን በተመለከተ ምንም ነገር አላለም። ነገር ግን ቴሌቪዥኑን ጠቅሶ ሌላ ድረ ገፅ ባለፈው ኤፕሪል ፉል April Fool እለት ህዝቡን ለማሞኘት ይህን ዜና ሰርቶት ነበር። የሚገርመው ነገር April fool ካለፈ 3 ሳምንታት ተቆጥረዋል።
First, his death reported on April fool, now the news spreading again. Col. Mengistu is not dead!
First, his death reported on April fool, now the news spreading again. Col. Mengistu is not dead!
ጊዜው ቢዘገይም  ይህንን ዜና ይዘው ወሬውን የሚያባዙት ሰዎች በራሳቸው ተሞኝተዋል ማለት ነው። 3 ሳምንታት ቢቆጠሩም… እነዚህን የሞኝ ወሬ ሳያረጋግጡ የሚነዙትን ሰዎች April Fool እንበላቸው (ከፈገግታ ጋር)።
ማጠቃለያችን የሚሆነው… “ኮሎኔል መንግስቱ አልሞቱም።” የሚለው ርእሳችን ነው።





PM Hailemariam Asked About Reeyot Alemu In France24 Interview


New York (TADIAS) – In a wide-ranging interview with France24 this week, Prime Minster Hailemariam Desalegn energetically fielded a number of questions in his role as the current chairman of the African Union about the continent’s troubled spots, including the situation in Mali, the elections in Kenya, the prospect of peace in Somalia, and the border issue with Eritrea. But when the topic changed to domestic matters and the imprisoned Ethiopian journalist Reeyot Alemu, winner of the 2013 UNESCO World Press Freedom Prize, so did the tone of the Prime Minister.


“For us our due process of law is according to the international standard and practice and we will continue on this way whether whoever says it,” he said. “What matters is the peace, security and democracy in the country, rather than what somebody says.”
Reeyot, who is now 32-year-old, was arrested in June 2011 inside a high-school class room where she worked as an English teacher. She was wanted for her opposing views in her part-time job as a columnist for the Amharic weekly Feteh. She is currently serving a five year sentence in Kality prison. UNESCO said last week that she was recommended for the prestigious award by an independent international jury of media professionals in recognition of her “exceptional courage, resistance and commitment to freedom of expression.”
“The whole important thing in this issue is that rule of law is one of the pillars of democratic process in the country,” the PM told the French television station, without mentioning Reeyot by name. “So we have responsibility also not only to have, you know, any kind of issues in the country, but to secure our people from any kind of terrorist actions.”
Hailemariam added: “In this regard, I think what’s important is that we are following all the international standard including the UN charter for human rights and democracy, which we have signed and ratified in my country. So I think it is according to the international, universal declarations that we are operating in the country.”
“Do you think there is room for improvement?” the reporter for France24 asked. “Do you agree that things could be better in this regard that there should be more vibrant press and a more vibrant opposition to make Ethiopia a real and full democracy?”
“I think there is no doubt about it,” the PM said. “Not only in Ethiopia, even in much more civilized democratic nations like France you have always something to improve. So how can we say there is no need of improvement in a fledgling democracy and a democracy of only fifteen years of age.”
The PM argued that establishing a culture of democracy takes time. “Therefore, we have a fledgling democracy, we have to learn lots of things, there are a number of rooms for improvement, including, the press, media and all kind of things,” he said. “We are learning from the international practices and my government is open to learn and improve things at home.”
The UNESCO Guillermo Cano World Press Freedom Prize is awarded annually during the celebration of World Press Freedom Day on May 3rd, which will take place this year in Costa Rica. The UNESCO jury highlighted Reeyot critical writing published in several independent Ethiopian newspapers on various political and social issues focusing on poverty and gender equality.
We urge Prime Minister Hailemariam Desalegn to do the right thing for Ethiopia and exercise his authority under the constitution to pardon Reeyot Alemu.

Tuesday, April 23, 2013

“ማፈናቀሉ የሚካሄደው በመንግሥት ትዕዛዝ ነው፤ ወደ ክስ እናመራለን”


“ማፈናቀሉ የሚካሄደው በመንግሥት ትዕዛዝ ነው፤ ወደ ክስ እናመራለን”


“በቤኒሻንጉል የህወሃት ታጋዮች ሰፋፊ እርሻ አላቸው”



በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ከ2000 ሺህ በላይ ትግሬዎች ባለይዞታ መሆናቸውንና ማንም ሳይነካቸው በሰላም እንደሚኖሩ፣ በቶጎ ወረዳ ከስልሳ በላይ ነባር የህወሃት ታጋዮች ሰፋፊ የእርሻ መሬት ወስደው በባለሃብት ደረጃ እንደሚገኙ የመኢአድ የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል አስታወቁ። ከሌሎች ብሔረሰቦች ተለይቶ የዘር ማጥፋት ወንጀል እየተፈጸመበት ያለውን የአማራ ብሔረሰብ በድጋሚ ለማስወጣት መታቀዱንም በመረጃ ማረጋገጣቸውን ተናግረዋል።
በቦታው በመገኘት አስፈላጊውን መረጃ እንደሰበሰቡ ለአሜሪካ ሬዲዮ የገለጹት የመኢአድ ስራ አስፈጻሚ በክልሉ ከሚኖሩት የተለያዩ ብሔረሰቦች ተለይቶ የአማራ ብሔረሰብ እንዲፈናቀልና እንዲሰቃይ የሚደረገው በማዕከላዊ መንግስት ትዕዛዝ እንደሆነም አመልክተዋል።
Justice Gavelመኢአድ ያሰራጨውን መግለጫ ተከትሎ በተዘጋጀ ጋዜጣዊ መግለጫ ማብራሪያ የሰጡት አቶ ሃይሉ ሻወል፣ ድርጊቱ በበታች የቀበሌና ወረዳ አመራር አካላት ተፈጽሟል መባሉን ተቃውመዋል።”ሰዎቹ እንዲወጡ ሲታዘዝ ያ ሁሉ ወታደር ከየት መጣ?” በማለት የጠየቁት አቶ ሃይሉ ሻወል፣ በርካታ የወያኔ ሰዎች በቦታው እያሉ አማራው ተለይቶ እንዲፈናቀል የበታች ባለስልጣናት በራሳቸው ውሳኔ ይህን ሊያደርጉ እንደማይችሉ ተናግረዋል። በማያያዝም በርካታ ተጨባጭ ማስረጃ ስለተሰባሰበ ጉዳዩን ወደ ዓለምአቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ለመውሰድ በዝግጅት ላይ እንደሚገኙ አመልክተዋል።
ባላቸው የተለያየ መስመር ፍርድ ቤቱ የሚቀበላቸውን ማስረጃዎች በማጣራት አስፈላጊ መረጃዎችን እንዳሰባሰቡ የገለጹት ኢንጂነር ሃይሉ ሻወል፣ “የሰውና የቪዲዮ መረጃ አለን። የመንግስት ወታደሮች ህዝብ ሲደበድቡ፣ መኪና ተገልብጦ ሰዎች ሜዳ ላይ ሲሰቃዩ፣ በግድ ሲፈናቀሉ … የሚያሳይ ተጨባጭ ማስረጃ አሰባስበናል። ወደ ክስ እናመራለን” በማለት መናገራቸውን የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ (ቪኦኤ) አመልክቷል።
የመኢአድ የስራ አስፈጻሚ አባል በበኩላቸው የመንግስት ባለስልጣኖችና ካድሬዎች በኩምሩክ ሕዝብ በመሰብሰብ ማነጋገራቸውን ይጠቅሳሉ። እሳቸው እንዳሉት ህዝቡ “ለምን በዘራችን ሳቢያ ይህ ሁሉ ስቃይ ይደርስንባል?” በማለት ጠይቆ ነበር። የሰበሰቧቸው ባለስልጣናት “ክልሉ የናንተ አይደለም ውጡ” ሲሉ  እንደመለሱላቸው የጠቀሱት የስራ አስፈጻሚ አባል፣ በሌላ በኩል የተፈጸመው ህገ ወጥ የዘር ማጥፋት ተግባር የመንግስት እጅ ያለበት እንዳይመስል ለክልሉ ነዋሪዎች “አማራን አታስጠጉ፣ ከአማራ ጋር አትብሉ፣ ከአማራ ጋር አትጠጡ፣ ቤት አታከራዩ፣ ይህን ማድረግ ወንጀል ነው” በማለት መንገራቸውንና በዚሁ መነሻ ህዝቡ በክልሉ ያሉ አማሮች አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ ጥያቄ እንዲያቀርቡ መመሪያ መሰጠቱን አመልክተዋል። ይህ የሚሆነውም ጥያቄው ከህዝብ የመጣ እንደሆነ ለማሳየት እንደሆነም አስታውቀዋል።
ahmed
የቤኒሻንጉል ፕሬዚዳንት አህመድ ናስር
በዘር፣ በሐይማኖትና በአመለካከት አንድን ማህበረሰብ በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት መሞከር፣ ማሸማቀቅ፣ ሴቶችን መድፈር በዘር ማጥፋት እንደሚያስጠይቅ ያመለከቱት የመኢአድ የስራ አስፈጻሚ አባል፣ “ይህ ሁሉ ተፈጽሟል” በማለት ድርጅታቸው በዓለም አቀፉ ወንጀለኞች ፍርድ ቤት ክስ ለመመስረት ከድምዳሜ መድረሱን ገልጸዋል።
የቤኒሻንጉል ክልል ፕሬዚዳንት ለሪፖርተር በሰጡት መግለጫ ስህተት መሰራቱን ማመናቸውና ድርጊቱን የፈጸሙት ኪራይ ሰብሳቢ የወረዳና የበታች አመራሮች እንደሆኑ ማስታወቃቸው አይዘነጋም። በተመሳሳይ ለስራ ፈረንሳይ አገር በነበሩበት ወቅት ለጀርመን ሬዲዮ ጉዳዩን አስመልክቶ መግለጫ የሰጡት የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ዲኤታ ብርሃነ ገ/ክርስቶስ ፕሬዚዳንቱ ተፈጸመ ስላሉት ስህተት “የማውቀው ነገር የለም። አልሰማሁም። እኔ የማውቀው ደን ጨፍጭፈው በሃይል መሬት የያዙ መፈናቀላቸውን ነው” ብለዋል። ዶ/ር ያዕቆብ ሃይለማርያም ቀደም ባሉት ሳምንታት ከቤኒሻንጉል የተፈናቀሉትን ዜጎች አስመልክተው በሰጡት አስተያየት ወንጀሉ የዘር ማጥፋት ስለሆነ ክስ መመስረት እንደሚቻል አመልክተው ነበር።
መኢአድ በበደኖ፣ በአርባ ጉጉ፣ አረካ ቀደም ሲል የተፈጸሙትን የዘር ማጥፋት ወንጀሎች አያይዞ ለክስ እንደሚጠቀምበት አመልክቷል። በጥያቄና መልሱ ወቅት ከነበሩት ጋዜጠኞች መካከል “የተፈናቀሉት ተመልሰዋል። ለምን አትተውትም” በማለት ጥያቄ ያቀረቡ ጋዜጠኞች እንደነበሩ የቪኦኤው የአዲስ አበባ ዘጋቢ ጠቆም አድርጎ አልፏል።

ESAT Daily News April 22 2013


ግብጽ የውሃ ጦርነት ለማድረግ ሃይል እያደራጀች ናት።



በአሜሪካ ከፍተኛ እገዛ የሚደረግለት የግብጽ ጦር ሃይል የናይል ወንዝን ለመቆጣጠር ሲባል መጠሪያው የዉሃ ጦርነት ሊባል የሚችል ጸብ አጫሪ ተግባር ለመፈጸም በዝግጅት ላይ ይገኛል። የምዕራብ የደህንነት ምንጮች እንደተናገሩት ከሆነ የጦር ክፍሉ የሃገሪቱን ፕሬዝዳንት ሞሃመድ ሞርሲን ማንኛውንም የናይል ወንዝ ፍሰት የሚያስተጓጉል ተግባር ለመቀልበስ ጦሩ የሚደራጅበትን ፈቃድ ጠይቋል።
 አካላቱ የሚሉት የጦር ሃይሉ ከኢትዮጵያ ጋር ከፍተኛ ጸብ ሊፈጠር እንደሚችል እና ያም የግብጽን እና የሱዳንን የውሃ ፍጆታ አደጋ ላይ የሚጥል ክስተት ይሆናል ያለው ሜንልነው።
”ለግብጽ የጦር ሃይል እና መንግስት ይህ ምናልባትም የዛሬው ትልቁ እና አንገብጋቢ የጸጥታ ጉዳይ ነው” ብለዋል ምንጮቹ።
ምንጮቹም አክለው ሞርሲ ከሱዳን ጋር የጦር ሃይል ውህደት በማድረግ ኢትዮጵያ በናይል ወንዝ ላይ የምታደርገውን የግድብ ግንባታ ለማስቆም በዝግጅት ላይ ይገኛሉ ሲሉም ለኢትዮጵያ የአደጋ ማስጠንቀቂያ ሊባል የሚችል ሃሳብ ሰንዝረዋል። የህዳሴ ግድቡ ወደ 84 ቢሊዮን ኪዩቢክ ዉሃ በማስቀረት ለኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጫ በቂ የሆነ ክምችት ለማድረግ ታስቦበት እየተገነባ ያለ ፕሮጀክት መሆኑ ይታወቃል።
”የጦር ሃይሉ በቅርቡ የአየር ጥቃት ለማድረግ ትእዛዝ የሚደረግበትን መንገድ እና የግድቡን ግንባታ ለማስቆም ወይም የኢትዮጵያዋን ልዕልት በቀላሉ ለማውደም እየተዘጋጀ ይገኛል” ይላል ይህ ምንጭ።
የዉሃውን ስልሳ በመቶ የምትጠቀመው ግብጽ የቀድሞውን ያለፈ ”መብት” ለማስጠበቅ የሙጥኝ ማለቷ የማያለሰልስ አቋም እየሆነ መጥቷል።
በማስቀጠልም ምንጮቹ የሞርሲ መንግስት ለአዲስ አበባ ጠንካራ ማስጠንቀቂያ ይሰጣል ተብሎ እንደሚጠበቅ ግምታቸውን አስታውቀዋል። ይህም ይሆናል ተብሎ የሚታሰበው በመጪው የግንቦት ወር መገባደጃ አከባቢ በግብጽ-ሱዳን-ኢትዮጵያ ሶስትዮሽ የቴክኒካል ቀጣይ ስብሰባ ነው ተብሏልም።
ናይል በአስር ሃገራት የጋራ ሃብትነት ይታወቃል።
”ኢትዮጵያ ለግድቡ ተግባር የሚጠቅማትን  ወይም የሚሆናትን ዉሃ ብቻ ማጠራቀሟን ማረጋገጥ የሚቻልባቸው እርምጃዎች መወሰዳቸው ግድ ነው ይህም ከግብጽ ፈቃድ እና መስመር ጋር የተስማማ መሆን አለበት” ሲሉ የተደመጡት ደግሞ የዛሬ አራት ቀን በግብጽ የመንግስት ዜና አውታር አል አህራም ዴይሊ ንግግር ያደረጉት የሃገሪቱ ባለስልጣን ናቸው።
የዜና ምንጮች ይህን ያሉት የግብጽ የጦር ሃይል  ከዩናይትድ ስቴትስ አዲስ ኤፍ-አስራ ስድስት ብሎክ ሃምሳ ሁለት የተባለ ለብዙ ተግባራት የሚውል የጦር አውሮፕላን መረከቧን እንደ ዋቢ መረጃ በመጥቀስ ነው። በማስቀጠል እንዳሉትም  በአ.አ 2013 ወደ ሃያ የሚሆን ቁጥር ያላቸው መሰል የጦር አውሮፕላኖች የሚቀበለው የግብጽ የአየር ሃይል በሰጠው መረጃ የቅርብ ጊዜው ኤፍ አስራ ስድስት ቫሪያንት ተቀጥያ የነዳጅ መያዣዎች ያሉት በመሆኑ በኢትዮጵያዋ ልዕልት ላይ ጥቃት ለመሰንዘር ያስችለናል ሲል አስታውቋል።
የህዳሴው ግድብ በየዓመቱ ከአስራ ስምንት እስከ ሃያ ሚሊዮን ኪዩቢክ ዉሃ እንድናጣ ያደርገናል ስትል ግብጽ አስታውቃለች። ምንጮቹ እንደሚሉትም ግብጽ ለዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ በተደጋጋሚ የኢትዮጵያን ግድብ ፕሮጀክት አደገኛነት ማሳሰቧን ገልጸዋል።
”በዚህ ጉዳይ ላይ የአሜሪካ ድርሻ በጣም ወሳኝ ነው ምክንያቱም በኢትዮጵያ ሊደረግ የሚችለው ጥቃት ላይ ምርቷ የሆነው የጦር አውሮፕላን ግልጋሎት ላይ ሊውል ታቅዷል እና ነው” ያለው ይህ ምንጭ ነው።
ይህ ዜና የተገዛ በመሆኑ ማሰራጨት የሚፈልግ ከዝግጅት ክፍላችን ፈቃድ መውሰድ አለበት።
wolaita.com

ጠቅላይ ሚንስትር ኃይለ ማርያም ብራስልስ ላይ እንዳሉት መንግሥታቸዉ ከዓለም አቀፉ ድርጅት ሸላሚዎች ጋር አይግባባም፥ እንዲያዉም ይቃረናል።ከዋሽግተን ዲሲ የደረሰንን ዘገባ ከተከታተላችሁት፥ የዩናይትድ ስቴትስ ዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር አርብ ማታ ይፋ ያደረገዉ ዓመታዊ ዘገባ ከጠቅላይ ሚንስትር ኃይለ ማርያም መግለጫ ጋር መቃረኑን አስተዉላችኋል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሕዝብ ግንኙነት ምክትል ኀላፊ፥—
ከተቃዋሚ ፓርቲ ባለሥልጣናት አንዱ፥ —
የፖለቲካ ተንታኝ፥ —-
ጠቅላይ ሚንስትር ኃይለ ማይርያም ደሳለኝ፥—
የዩናይትድ ስቴትስ ዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር ሹም፥—
አይግባቡም።አይደማመጡም፥ ይቃረናሉም።እንዴት? ለምን?
——
የተለያዩ መገናኛ ዘዴዎች እንደዘገቡት፥ኢትዮጵያዉያን ሥደተኞች ለበርካታ አመታት እንደሚያደርጉ፥ እንደኖሩበት፥ከኖርዌ እስከ ዋሽግተን፥ ከአዳራሽ እስከ አደባባይ እንደተሰለፉ ያለፈዉ ሳምንት-ይሕን ሳምንት ተካ።ጥያቄዉ አንድም ብዙም ነዉ።መፈክሩ ግን ይቀነቀናል።ጥያቄዉ ይዥጎደጎዳል።ቅዳሜ፥-ስታቫንገር-ኖርዌ ተደገመ።
ቅዳሜ፥ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ምናልባት አዲስ አበባ ይሆኑ ይሆናል።ከአራት ቀን በፊት ሮብ ግን ሽትራስቡርግ-ፈረንሳይ ነበሩ።ጠቅላይ ሚንስትሩ ከአዉሮጳ ሕብረት ምክር ቤት ፕሬዝዳት ከማርቲን ሹልስ ጋር ባደረጉት ዉይይት ከተነሱ ጉዳዮች የኢትዮጵያ መንግሥት የሠብአዊ መብት፥ የፕሬስ ነፃነት፥ የፍትሕ አያያዝ ዋናዎቹ ነበሩ።
ርዕሠ-መንበሩን ፓሪስ ፈረንሳይ ያደረገዉ የተባበሩት መንግሥታት የትምሕርት፥ የሳይንስ እና የባሕል ድርጅት (UNESCO) የኢትዮጵያ መንግሥት በአሸባሪነት ወንጀል በይግባኝ አምስት ዓመት እስራት ያስፈረደባትን አምደኛ፥ ፀሐፊና መምሕርት ርዕዮት ዓለሙን መሸለሙን ያስታወቀዉ ጠቅላይ ሚንስትር ኃይለ-ማርያም እዚያዉ ምሥራቅ ፈረንሳይ እያሉ ነበሩ።ርዕዮት የተሸለመችበት ምክንያት፥-
ሽልማቱ እንዲሰጣት ከወሰኑት ዳኞች አንዱ፥-
በማግስቱ ሐሙስ ጠቅላይ ሚንስትር ኃይለ ማርያም ብራስልስ ላይ እንዳሉት መንግሥታቸዉ ከዓለም አቀፉ ድርጅት ሸላሚዎች ጋር አይግባባም፥ እንዲያዉም ይቃረናል።ከዋሽግተን ዲሲ የደረሰንን ዘገባ ከተከታተላችሁት፥ የዩናይትድ ስቴትስ ዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር አርብ ማታ ይፋ ያደረገዉ ዓመታዊ ዘገባ ከጠቅላይ ሚንስትር ሐይለ ማርያም መግለጫ ጋር መቃረኑን አስተዉላችኋል።እንቀጥል፥ አዲስ አበባ።
ጠቅላይ ሚንስትር ኃይለ ማርያም ከብራስልስ፥ በፓሪስ አድርገዉ አዲስ አበባ በገቡ በሳልስቱ፥ ከአዲስ አበባ ከመነሳታቸዉ በፊት የተጀመረዉ አካባቢያዊ ምርጫ ተጠናቀቀ።ዕሁድ።በምርጫዉ ዝግጅት እና ሒደት ገዢዉ ፓርቲ እና ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ-ባንድ ጎራ፥ ተቃዋሚዎቹ፥ በሌላ ጎራ ቆመዉ ይወዛገባሉ።እንዲያዉም ይቃረናሉ።
አቶ ይስማ ጅሩ ምርጫ ቦርድ ምክትል የሕዝብ ግንኙነት ኀላፊ ናቸዉ።አቶ አስራት ጣሴ ሠላሳ ሰወስት ተቃዋሚ ፓርቲዎችን የሚያስተባብረዉ ጊዚያዊ ኮሚቴ ሰብሳቢ ናቸዉ።ሠላሳ-ሰወስቱም ፓርቲዎች በምርጫዉ አልተሳተፉም።የምርጫ ዝግጅት ሒደቱንም ያወግዙታል።
አቶ ወድማገኘሁ ደነቀ፥-የመላዉ ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳትና የሰላሳ ሠወስቱ ፓርቲዎች አስተባባሪ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ናቸዉ።
የምርጫ ቦርድ ምክትል የሕዝብ ግንኙነት ምክትል ኀላፊ ግን ሌላ ነዉ-የሚሉት።
የሲዳማ አርነት ንቅናቄ (ሲአን) ጉዳይ ከተነሳ፥ የሰላሳ ሰወስቱ ፓርቲ ሰብሳቢ ያሉት አለ።
አቶ አስራት «ትክክል» ያሉት የሰላሳ ሰወስቱ ተቃዋሚ ፓርቲዎች አቋም በምርጫዉ ላለመሳተፍ መወሰናቸዉን ነበር።የዉሳኔያቸዉ ሰበብ ምክንያት «የዲሞክራሲ እጦት» ቢባል-የሚጠቃለል፥ ግን በአስራ-ስምንት ነጥቦች የተዘረዘሩ ቅድመ-ሁኔታዎች እንዲሟሉ ጠይቀዉ «ከገዢዉ ፓርቲና ከምርጫ ቦርድ መልስ በማጣታችን ነዉ» ባዮች ናቸዉ።አቶ ወንድማገኝ፥-
አንድ ሐገር፥ እንዲያዉም አንድ ከተማ ነዉ ያሉት፥እኩል ስለሚመለከታቸዉ አንድ ጉዳይ ነዉ የሚያወሩት ሥለ ምርጫ። ግን አይግባቡም።እንዲያዉም ይቃረናሉ።ይተዋወቁስ ይሆን?
ያለመግባባት፥ የመቃረን፥ ምናልባትም እየተዋወቁ የማይተዋወቁ የመምሰላቸዉ ሰበብ በርግጥ ብዙ ነዉ።ባለፈዉ ሳምንት ዕሁድ ተጀምሮ ትናንት ዕሁድ የተጠናቀቀዉ የአካባቢ ምርጫ በተገቢዉ መንገድ ተካሒዶ ቢሆን ኖር ግን ፍራንክፈርት-ጀርመን የሚኖሩት ኢትዮጵያዊዉ የፖለቲካ ተንታኝ ዶክተር ለማ ይፍራሸዋ እንደሚሉት በኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመመሥረት ለሚደረገዉ ተስፋ ወሳኝ በሆነ ነበር።
የገዢዉ ፓርቲ ተፅዕኖ፥ ወይም የተቃዋሚዎቹ ድክመት፥ ይባል ወይም ሌላ ባሁኑ ምርጫ መሆን የነበረበት አለመሆኑ፥ የሚታሰብ የሚፈለገዉን የዲሞክራሲ ተስፋ ጨርሶ ባያስቀረዉ እንኳ አርቆታል። እንደገና ዶክተር ለማ።
በ1997ቱ ብሔራዊ ምርጫ የፈነጠቀዉ ተስፋ በዉጤት ዉዝግብ፥ ባሳዛኝ ግጭት ተጨናጉላል።ያኔ ከእንግዲሕስ ብለን ነበር።በሁለተኛዉ ዓመት በተደረገዉ አካባቢያዊ ምርጫ እንዲሕ እንደዘንድሮዉ አብዛኞቹ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ባለመሳተፋቸዉ በገዢዉ ፓርቲና በተባባሪዎቹ ድል ተጠናቅቋል።ያኔም ጠይቀን ነበር።የ2002ቱ ብሔራዊ ምርጫ ተቃዋሚዎች ተሳትፈዉም፥ በገዢዉ ፓርቲ የዘጠና ዘጠኝ ነጥብ ስድስት በመቶ ድል አብቅቷል።ያንኑ ጥያቄ አሰልሰን ጠይቀን ነበር።በዘንድሮዉም ምርጫ አዲስ ነገር የለም።አዲስ ጥያቄም የለንም።በ2007 ግን ሌላ ምርጫ አለ።አሮጌዉን ጥያቄ እንድገመዉ።ከእንግዲሕስ?
Pakistani journalists demonstrate against the attacks on the offices of the private Geo news channel and english daily The News International, in Islamabad on Friday, 16 March 2007. Windows were smashed in the lobby as police officers tried to interrupt transmission of violent scenes near the Supreme Court, where suspended chief justice Iftikhar Chaudhry stood before a panel of judges over allegations of misuse of office. EPA/NADEEM KHAWER +++(c) dpa - Report+++የፕረስ ነጳነት
የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሕዝብ ግኙነት ሐላፊ አቶ ይስማ ጅሩ መለሱ፥-እያሉ።የአንድነት ለዲሚክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) የሕዝብ ግንኙነት ሐላፊ አቶ ዳንኤል ተፈራ የሩቅም ቢሆን ተስፋ አላቸዉ፥-የሰላሳ ሰወስቱ ተቃዋሚ ፓርቲዎች አስተባባሪ አቶ አስራት ጣሴ ግን መጪዉን ምርጫ በቀቢፀ ተስፋ ነዉ የሚያዩት፥-።
ዶክተር ለማ፥ ይመክራሉ፥-ሰሚ ጆሮ ይገኝ ይሆን?
ነጋሽ መሐመድ
ተክሌ የኋ