Saturday, May 9, 2015

“ዜጎችን በማዋረድ የሚደሰት አገዛዝና ለመዋረድ የፈቀደ ሕዝብ እስካለ ድረስ የቁልቁለቱ ጉዞ መጨረሻ የለውም” – አርበኞች ግንቦት 7 -

የአርበኞች ግንቦት 7 በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ያተኮረ ጽሁፍ

የህወሓት አገዛዝ ፋሽስታዊ ባህርያት እያደር መረን እያጣ፤ ነውረኛ እየሆነ መጥቷል። በአሳለፍነው ሣምንት ብቻ እንኳን አስነዋሪ ይዘት ያላቸው ሁለት ፋሽስታዊ ክስተቶችን አስተውለናል።
ginbot 7
አንዱ በምርመራ ስም በታሳሪዎች ላይ የሚደረገው አሳፋሪ ሰቆቃ ነው። በገላቸው በሚያፌዙና በሚሳለቁ ተቃራኒ ፆታ መርማሪዎች ፊት ለሰዓታት ተመርማሪዎች ራቁታቸውን እንዲሆኑ የሚደረግበት እና እየተፌዘባቸው የሚደበደቡበት ሥርዓት መኖሩ የጉዳቱ ሰለባዎች ይፋ ሲያወጡ እፍረቱ ለመርማሪዎቹ ብቻ ሳይሆን ይህንን ጉድ ተሸክመን ለኖርነው ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ነው። በተለይም ደግሞ እንዲህ ዓይነት ክብረነክ ሰቆቃ በሴቶች ላይ እየተፈፀመ መሆኑን ስንሰማ አገራዊ ውርደቱ ያሸማቅቀናል። እንዲህ ዓይነቶችን በሰው ስቃይና እፍረት የሚዝናኑ ጉዶችን ተሸክመን የምኖር መሆናችን ሁላችንን ያዋርደናል። ይህንን አስነዋሪ “የምርመራ ዘዴ” ያጋለጡት የዞን 9 ብሎገሮች፣ ጋዜጠኞችና ፓለቲከኞች ክብርና ሞገስ የሚገባቸው ጀግኖች ሲሆኑ የተዋረዱት እነሱ ሳይሆኑ እኛ ኢትዮጵያዊያን መሆናችን ሊሰማንና “ውርደት በቃ” ልንል ይገባናል።
ሁለተኛው አሳፋሪ ድርጊት ደግሞ ወገኖቻችንን በግፍ ባረደው አይሲስ በተሰኘው አሸባሪ ድርጅት ላይ የህወሓት አገዛዝ የተለሳለሰ አቋም ወስዷል ብለው ራሱ ህወሓት በጠራው ሰልፍ ላይ ተቃውሞዓቸውን ባሰሙ ወጣቶች ላይ አገዛዙ የወሰደው የኃይል እርምጃና ከዚያም ወዲህ እየተደረገ ያለው ነገር ነው። አገዛዙ ለፕሮፖጋንዳው ይጠቅመኛል ብሎ በጠራው ሰልፍ ወጥተው ተቃውሞዓቸውን የገለፁ ወጣቶች በአሰቃቂ ሁኔታ ተደብድበዋል፤ በጅምላ ወደ እስር ቤቶች ተግዘዋል። የአገዛዙ ካድሬዎች ወገኖቻችንን የፈጀውን አይሲስን በመቃወም ፋንታ የራሱ የህወሓትን ውል አልባ ህግ አክብረው በመንቀሳቀስ ላይ ያሉትን ሰማያዊ ፓርቲ፣ ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞችን እና አረና ፓርቲን እየወነጀሉ መሆኑ አጅግ አሳፋሪ ነገር ነው። የአይሲስን አረመኔአዊ ድርጊት ከኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች የመብት ጥያቄ ጋር ለማገናኘት በህወሓት የደህንነት ቢሮ አማካይነት እንቅስቃሴ መጀመሩ እየተሰማ ነው። ለወጣቱ በብዛት መሰደድ በምክንያትነት የሚያቀርቡት ደላሎችን መሆኑ አላዋቂነት ሳይሆን በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ቅራኔው በኢትዮጵያዊያን መካከል እርስ በርስ እንዲሆን ያለመ መሠሪነት ነው። ከዚህም አልፎ የትግራይ ወጣቶችን ነጥሎ በመሰብሰብ “ትምክህተኞች ሊበሉህ ነውና ታጥቀህ ሳይቀድሙህ ቅደም” እያሉ መቀስቀስ በመንግሥት ደረጃ የእርስ በርስ እልቂትን ከማደራጀት ተለይቶ አይታይም። የሥርዓቱ ይሉኝታ ቢስነት የደረሰበት ዝቅጠት ገላጭ ከሆኑ ነገሮች አንዱ “እስከምርጫ መጨረሻ ድረስ ልጆቻችሁን አስረን እናቆይላችሁ” እያሉ ወላጆችን እስከመጠየቅ መድፈራቸው ነው።
arbegnoch ginbot 7
ከላይ በአጭሩ የተዘረዘሩት ኩነቶች የሚያረጋግጡት ህወሓት የተማከለ አመራር አጥተው መንገድ የጠፋቸው፤ ሆኖም ግን እጃቸው ውስጥ የገባው ስልጣንና ሀብት ላለማጣት ምንም ነገር ከማድረግ የማይመለሱ አውሬዎች ስብስብ መሆኑ ነው። እንዲህ ዓይነቱን የአውሬዎች ስብስብ የሚገዛው የህግም ሆነ የሥነ-ምግባር ገደብ የለም። ህወሓት እስር በርሳችንን አባልቶ አገራችንንና ሕዝቧን ወደ ማንወጣው አዘቅት ከመክተቱ በፊት ራሱ ህወሓትን ማስወገድ እና በምትኩት ፍትህ፣ ነፃነት፣ ዲሞክራሲና እኩልነት የሰፈነባት ኢትዮጵያን መገንባት የዚህ ትውልድ ኃላፊነት ነው። ይህ ካላደረግን አሁን በወህኒ ቤቶች የሚደረገው ዜጎችን ልብስን አስወልቆ የማዋረድ አስነዋሪ ተግባር ነገ በአደባባዮች የማይደረግ ስለመሆኑ ምንም ማረጋገጫ የለንም። ይህ ትውልድ ኃላፊነቱ ካልተወጣ ህግን አክብረው ከአገዛዙ የተለየ ሀሳብ እናራምዳለን የሚሉ ወገኖቻችን በሙሉ አደጋ ውስጥ ናቸው። በህወሓት መሠሪ ተግባራት ሳቢያ በክርስትናና እስልምና እምነት ተከታይ ኢትዮጵያዊያን መካከል ያለው መግባባት እንዲሻክር እየተደረገ ነው። ዜጎችን በማዋረድ የሚደሰት አገዛዝና ለመዋረድ የፈቀደ ሕዝብ እስካለ ድረስ የቁልቁለቱ ጉዞ መጨረሻ የለውም። ይህንን ማስቆም ያለብን እኛ ሁላንችንም ነን። በአደባባይ መደራጀት ሲከለከል በምስጢር መደራጀትን መልመድ የኛ ኃላፊነት ነው። የኢትዮጵያ አርበኞች ድል መታሰቢያ በዓልን ስናከብር ከቀደምቶቻችን ልንወርስ ከሚገቡን እሴቶች አንዱ ለክብራችን ዋጋ መክፈል ያለብን መሆኑን ጭምር ነው። የኢትዮጵያዊያን ክብር በወያኔ ሲዋረድ እያየን ዝምታን ከመረጥን ከዚህም የባሰ እንዲመጣ መፍቀዳችንን እንወቀው።
አርበኞች ግንቦት 7:የአንድነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ የዜጎችና የአገር ውርደት ይብቃ! በተባበረ ክንድ ህወሓት ይወገድ፤ በምትኩም ፍትህ፣ ነፃነት፣ ዲሞክራሲና እኩልነት የሰፈነባት ኢትዮጵያን ለመመሥረት መሠረት እንጣል፤ ይህንን ታላቅ ኃላፊነት ለመወጣት በኅብረት እንነሳ ይላል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!
- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/41195#sthash.vFHHrBcN.dpuf
የአርበኞች ግንቦት 7 በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ያተኮረ ጽሁፍ

የህወሓት አገዛዝ ፋሽስታዊ ባህርያት እያደር መረን እያጣ፤ ነውረኛ እየሆነ መጥቷል። በአሳለፍነው ሣምንት ብቻ እንኳን አስነዋሪ ይዘት ያላቸው ሁለት ፋሽስታዊ ክስተቶችን አስተውለናል።
ginbot 7
አንዱ በምርመራ ስም በታሳሪዎች ላይ የሚደረገው አሳፋሪ ሰቆቃ ነው። በገላቸው በሚያፌዙና በሚሳለቁ ተቃራኒ ፆታ መርማሪዎች ፊት ለሰዓታት ተመርማሪዎች ራቁታቸውን እንዲሆኑ የሚደረግበት እና እየተፌዘባቸው የሚደበደቡበት ሥርዓት መኖሩ የጉዳቱ ሰለባዎች ይፋ ሲያወጡ እፍረቱ ለመርማሪዎቹ ብቻ ሳይሆን ይህንን ጉድ ተሸክመን ለኖርነው ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ነው። በተለይም ደግሞ እንዲህ ዓይነት ክብረነክ ሰቆቃ በሴቶች ላይ እየተፈፀመ መሆኑን ስንሰማ አገራዊ ውርደቱ ያሸማቅቀናል። እንዲህ ዓይነቶችን በሰው ስቃይና እፍረት የሚዝናኑ ጉዶችን ተሸክመን የምኖር መሆናችን ሁላችንን ያዋርደናል። ይህንን አስነዋሪ “የምርመራ ዘዴ” ያጋለጡት የዞን 9 ብሎገሮች፣ ጋዜጠኞችና ፓለቲከኞች ክብርና ሞገስ የሚገባቸው ጀግኖች ሲሆኑ የተዋረዱት እነሱ ሳይሆኑ እኛ ኢትዮጵያዊያን መሆናችን ሊሰማንና “ውርደት በቃ” ልንል ይገባናል።
ሁለተኛው አሳፋሪ ድርጊት ደግሞ ወገኖቻችንን በግፍ ባረደው አይሲስ በተሰኘው አሸባሪ ድርጅት ላይ የህወሓት አገዛዝ የተለሳለሰ አቋም ወስዷል ብለው ራሱ ህወሓት በጠራው ሰልፍ ላይ ተቃውሞዓቸውን ባሰሙ ወጣቶች ላይ አገዛዙ የወሰደው የኃይል እርምጃና ከዚያም ወዲህ እየተደረገ ያለው ነገር ነው። አገዛዙ ለፕሮፖጋንዳው ይጠቅመኛል ብሎ በጠራው ሰልፍ ወጥተው ተቃውሞዓቸውን የገለፁ ወጣቶች በአሰቃቂ ሁኔታ ተደብድበዋል፤ በጅምላ ወደ እስር ቤቶች ተግዘዋል። የአገዛዙ ካድሬዎች ወገኖቻችንን የፈጀውን አይሲስን በመቃወም ፋንታ የራሱ የህወሓትን ውል አልባ ህግ አክብረው በመንቀሳቀስ ላይ ያሉትን ሰማያዊ ፓርቲ፣ ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞችን እና አረና ፓርቲን እየወነጀሉ መሆኑ አጅግ አሳፋሪ ነገር ነው። የአይሲስን አረመኔአዊ ድርጊት ከኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች የመብት ጥያቄ ጋር ለማገናኘት በህወሓት የደህንነት ቢሮ አማካይነት እንቅስቃሴ መጀመሩ እየተሰማ ነው። ለወጣቱ በብዛት መሰደድ በምክንያትነት የሚያቀርቡት ደላሎችን መሆኑ አላዋቂነት ሳይሆን በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ቅራኔው በኢትዮጵያዊያን መካከል እርስ በርስ እንዲሆን ያለመ መሠሪነት ነው። ከዚህም አልፎ የትግራይ ወጣቶችን ነጥሎ በመሰብሰብ “ትምክህተኞች ሊበሉህ ነውና ታጥቀህ ሳይቀድሙህ ቅደም” እያሉ መቀስቀስ በመንግሥት ደረጃ የእርስ በርስ እልቂትን ከማደራጀት ተለይቶ አይታይም። የሥርዓቱ ይሉኝታ ቢስነት የደረሰበት ዝቅጠት ገላጭ ከሆኑ ነገሮች አንዱ “እስከምርጫ መጨረሻ ድረስ ልጆቻችሁን አስረን እናቆይላችሁ” እያሉ ወላጆችን እስከመጠየቅ መድፈራቸው ነው።
arbegnoch ginbot 7
ከላይ በአጭሩ የተዘረዘሩት ኩነቶች የሚያረጋግጡት ህወሓት የተማከለ አመራር አጥተው መንገድ የጠፋቸው፤ ሆኖም ግን እጃቸው ውስጥ የገባው ስልጣንና ሀብት ላለማጣት ምንም ነገር ከማድረግ የማይመለሱ አውሬዎች ስብስብ መሆኑ ነው። እንዲህ ዓይነቱን የአውሬዎች ስብስብ የሚገዛው የህግም ሆነ የሥነ-ምግባር ገደብ የለም። ህወሓት እስር በርሳችንን አባልቶ አገራችንንና ሕዝቧን ወደ ማንወጣው አዘቅት ከመክተቱ በፊት ራሱ ህወሓትን ማስወገድ እና በምትኩት ፍትህ፣ ነፃነት፣ ዲሞክራሲና እኩልነት የሰፈነባት ኢትዮጵያን መገንባት የዚህ ትውልድ ኃላፊነት ነው። ይህ ካላደረግን አሁን በወህኒ ቤቶች የሚደረገው ዜጎችን ልብስን አስወልቆ የማዋረድ አስነዋሪ ተግባር ነገ በአደባባዮች የማይደረግ ስለመሆኑ ምንም ማረጋገጫ የለንም። ይህ ትውልድ ኃላፊነቱ ካልተወጣ ህግን አክብረው ከአገዛዙ የተለየ ሀሳብ እናራምዳለን የሚሉ ወገኖቻችን በሙሉ አደጋ ውስጥ ናቸው። በህወሓት መሠሪ ተግባራት ሳቢያ በክርስትናና እስልምና እምነት ተከታይ ኢትዮጵያዊያን መካከል ያለው መግባባት እንዲሻክር እየተደረገ ነው። ዜጎችን በማዋረድ የሚደሰት አገዛዝና ለመዋረድ የፈቀደ ሕዝብ እስካለ ድረስ የቁልቁለቱ ጉዞ መጨረሻ የለውም። ይህንን ማስቆም ያለብን እኛ ሁላንችንም ነን። በአደባባይ መደራጀት ሲከለከል በምስጢር መደራጀትን መልመድ የኛ ኃላፊነት ነው። የኢትዮጵያ አርበኞች ድል መታሰቢያ በዓልን ስናከብር ከቀደምቶቻችን ልንወርስ ከሚገቡን እሴቶች አንዱ ለክብራችን ዋጋ መክፈል ያለብን መሆኑን ጭምር ነው። የኢትዮጵያዊያን ክብር በወያኔ ሲዋረድ እያየን ዝምታን ከመረጥን ከዚህም የባሰ እንዲመጣ መፍቀዳችንን እንወቀው።
አርበኞች ግንቦት 7:የአንድነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ የዜጎችና የአገር ውርደት ይብቃ! በተባበረ ክንድ ህወሓት ይወገድ፤ በምትኩም ፍትህ፣ ነፃነት፣ ዲሞክራሲና እኩልነት የሰፈነባት ኢትዮጵያን ለመመሥረት መሠረት እንጣል፤ ይህንን ታላቅ ኃላፊነት ለመወጣት በኅብረት እንነሳ ይላል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!
- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/41195#sthash.vFHHrBcN.dpuf

Thursday, March 12, 2015

Somalia’s Shebab militants attack in central town of Baidoa

Somali women sell tea on the side of the road in Baidoa on June 22, 2014, while Ethiopian soldiers in the African Union Mission in Somalia conduct a night patrol (AFP Photo/)
Somali women sell tea on the side of the road in Baidoa on June 22, 2014, while Ethiopian soldiers in the African Union Mission in Somalia conduct a night patrol (AFP Photo/)

Mogadishu (AFP) – Somalia’s Al-Qaeda-affiliated Shebab militants on Thursday attacked a fortified area in the central town of Baidoa, home to a key regional government headquarters, United Nations compound and airport, security officials said.

Officials said five gunmen opened fire at the gate of the high-security zone but were held off by Ethiopian troops. A source said an Ethiopian soldier was killed, while three of the attackers blew themselves up, another was shot dead and the fifth was shot and wounded, ending the attack.
“They are Shebab disguised in Somali military uniforms. That’s how they managed to enter,” a Somali police official in Baidoa, Mohamed Dahir, told AFP by telephone.
In a statement, the militants confirmed they carried out the attack and insisted it was a “success” — with the objective being to “disrupt a security meeting” between local authorities and Ethiopian troops, who are part of the African Union’s AMISOM force fighting the Islamists.
A United Nations source confirmed the attack, but said the compound where aid agencies are located did not appear to be the target of the militants.
Baidoa, situated 220 kilometres (140 miles) northwest of the capital Mogadishu, was captured by Ethiopian forces in February 2012, ending three years of Shebab rule and dealing the group a major blow.
In November the city became the capital of Somalia’s newly created South West State and the seat of its president Sharif Hassan Sheikh Adan, a former parliamentary speaker and key ally of the country’s internationally-backed government.
According to a security source, Adan’s office appeared to be the main target of the attack. However, militants failed to penetrate the building and the regional leader was safe, the source said.
Shebab rebels continue to stage frequent attacks as part of their fight to overthrow the country’s government and counter claims that they are close to defeat due to the loss of territory, regular drone strikes against their leaders and defections.
In the capital Mogadishu they have targeted hotels, the international airport, the presidential palace, a UN compound and restaurants.
On Wednesday evening one person was killed in a suspected Shebab car bomb attack against a popular hotel in Mogadishu, an attack that came several weeks after the Islamists carried out a suicide raid against another hotel in the city, killing at least 25 people.
The group have also carried out a string of revenge attacks in neighbouring countries — including the September 2013 attack on the Westgate shopping mall in the Kenyan capital Nairobi which left at least 67 dead.
Somalia has been unstable since the collapse of Siad Barre’s hardline regime in 1991, and the country’s new government is being supported by a 22,000-strong African Union force that includes troops from Burundi, Djibouti, Ethiopia, Kenya and Uganda.
- See more at: http://www.zehabesha.com/somalias-shebab-militants-attack-in-central-town-of-baidoa/#sthash.14ovXJkm.dpuf

“ውድ ኮሚቴዎቻችን ለውሳኔ 1 ወር ብቻ መቀጠራቸው የጓሮ ውሳኔ ለመሰጠቱ ማሳያ ነው” – ድምፃችን ይሰማ -

“ውድ ኮሚቴዎቻችን ለውሳኔ 1 ወር ብቻ መቀጠራቸው የጓሮ ውሳኔ ለመሰጠቱ ማሳያ ነው!!!
ፍ/ቤቱ ፖለቲካዊውን ውሳኔ ባለመቀበል በነጻ ሊያሰናብታቸው ይገባል!!!” 
ድምፃችን ይሰማ
ሐሙስ መጋቢት 3/2007
ከህግ የበላይነት ይልቅ የደህንነትና የመንግስት ባለስልጣናት ፍላጎት ተፈፃሚ በሚሆንበት መንግስታዊ ስርዓት ውስጥ ፍትህን ማድበሰበስና ማስተጓጎል የተለመደ ሆኗል፡፡ መንግስት ይህንን ለማድረግ የተገፋፋበት ምክንያት ደግሞ ‹‹በሽብርተኝነት ተጠርጥረዋል›› የተባሉት ንፁሃን ለእስር የሚበቁት ተጠርጥረዋል በሚባሉበት ወንጀል ሊያስጠይቃቸው የሚችል አንዳችም ህጋዊ ማስረጃ ሳይኖር በመሆኑ ነው፡፡
yisema dimstachin
ህዝበ ሙስሊሙ የመረጣቸው እንደራሴዎቹ በግፍ በታሰሩበት ማግስት በማዕከላዊ ከደረሰባቸው አካላዊ በደል ባልተናነሰ በፍትህ ችሎቱ ውስጥ በሚሰሩ ተውኔቶች የሥነ-ልቦና በደል ደርሶባቸዋል፡፡ በደሉ መደበኛ ክስ ተመስርቶባቸው ችሎት ፊት የቀረቡ ዕለት ከተነበበው የክስ መዝገብ ይጀምራል፡፡ በሀገሪቷ ከፍተኛ የሆነ ቅጣት በሚያስከትለው የሽብር ክስ የተከሰሱ ሲሆን ክሱ የተዋቀረበት የሀሰት ትብታብ እርስ በእርሱ እንኳ ተደጋግፎ መቆም የማይችል፣ ብሎም የቅጥፈትን ትክክለኛ ገጽታ ለተመልካች ሁሉ ማሳየት የሚችል ነበር፡፡ ከሁለት ዓመታት በላይ የዘለቀው የፍርድ ሂደትም ከአንድ ምንጭ በተቀዱት አቃቤ ህግ፣ ዳኛና ምስክሮች ቁርኝት የኮሚቴዎቻችንን የሞራል ልዕልና ለመስበር፣ አካላቸውን በማሰቃየት ያልተሳካውን የነፃነት ስሜታቸውን ለመቅበር፣ ተስፋቸውን ለማጨለም ተደራራቢ ትንኮሳዎች በሚደረጉበት የዕለታዊ ስነ ልቦናዊ ቅጣት ማዕከል በሆነው ፍርድ ቤት ውስጥ የሚደረግ ቅርፁ እንጂ ይዘቱ ያልተለየ ቅጥ ያጣ ተውኔት ሆኖ ቆይቷል፡፡
ፍርድ ቤቱ ፍትህ የምትንገላታበት የተውኔት መድረክ ከመሆንም ባሻገር የኢትዮጵያዊው ሙስሊም ሰላማዊ ትግል አሁንም በህገ ወጥነት፣ ህዝቡም በሽብርተኝነት የሚፈረጅበት፣ ለሚደርሱ በደሎች ሁሉ የህግ ሽፋን የሚፈለግበት አውድማ ነው፡፡ የህዝበ ሙስሊሙ እንደራሴዎች የፍርድ ሂደት መጠናቀቁን ተከትሎ ለመጨረሻ ብይን የአንድ ወር ቀጠሮ የተሰጠበት የመጨረሻው ችሎት በራሱም ለዚህ እውነታ ሌላ ተጨማሪ ማሳያ ነው፡፡ ከሁለት ዓመታት በላይ የዘለቀውና ከ5 ሺህ በላይ የፅሁፍ፣ የምስል፣ የድምፅና፣ የቪዲዮ ማስረጃዎች የቀረቡበት የፍርድ ሂደት የመጨረሻ መከላከያ ከተሰማበት ቀን ጀምሮ ሂደቱን ሙሉ ገምግሞ እና ከህግ፣ አዋጅና ደንቦች አንፃር መርምሮ ብይን ለመስጠት የአንድ ወር ቀጠሮ መስጠት ስላቅ ብቻ ሳይሆን ከችሎቱ መጋረጃ ጀርባ ባሉት የመንግስት አካላት ውሳኔው ቀድሞ ማለቁን አመላካች ነው፡፡
በዚህ ዓይነት በርካታ ተከሳሾች ባሉበት ሰፊ፣ ውስብስብና ረጅም የክስ ሂደት ውስጥ ቀርቶ የአንድ ግለሰብ ተራ ክስ እንኳ ሂደቱን መርምሮ ብይን ለመስጠት የሚሰጠው ቀጠሮ ከወር ከፍ ያለ ነው፡፡ ሆኖም ግን በኮሚቴዎቻችን የፍርድ ሂደት ውሳኔው የሚተላለፈው የቀረቡትን መረጃዎች መርምሮ፣ ከጭብጡ ጋር ያላቸውን ተያያዥነት አስልቶ፣ የተቀዱትን የአቃቤ ህግ ምስክርና የኮሚቴዎችን መከላከያዎች በሚገባ አድምጦ፣ በጠበቆችና በአቃቤ-ህጉ መካከል የተደረጉ ክርክሮችን አመዛዝኖ ሳይሆን የኢትዮጵያ ሙስሊሞችን የመብት ጥያቄ ለማፈንና የበደሉን ግፊት ለመጨመር በሚረዱ የፖለቲካ ውሳኔዎች በመሆኑ ከተለምዶው የፍርድ ቤት ሥርዓት ያነሰ እጅግ አጭር ጊዜ በመስጠት መንግስት በፍትህ ስርዓቱ ቁልቁል ጉዞ ላይ ፍጥነት ጨምሮበታል፡፡ ታዲያ ይህ ለአንድ አገር ውድቀት አይደለምን?
ዛሬም ሕዝበ ሙስሊሙ በጀግኖች መሪዎቹ ላይ የሚሰጥን የሐሰት ፖለቲካዊ ብይን በጭራሽ አይቀበልም! በጽኑም ይታገለዋል!!!
ትግላችን እስከድል ደጃፎች በአላህ ፈቃድ ይቀጥላል!
ድምጻችን ይሰማ!
አላሁ አክበር!
http://www.zehabesha.com/amharic/archives/39667

Wednesday, February 25, 2015

“መረጃ አውጡ፣ የደበቃችሁትን ሁሉ ተናገሩ”


የተቃዋሚ ፓርቲዎች አመራሮች በጨለማ ቤት መታሰራቸውን አስታወቁ

dark



በሽብርተኝነት ተጠርጥረው ማዕከላዊ ፌደራል ወንጀል ምርመራ የሚገኙት የሦስት ተቃዋሚ ፓርቲዎች የቀጠና/ዞን አመራሮች ለ16 ተከታታይ ቀናት በጨለማ ክፍል መታሰራቸውን ለፍርድ ቤት አስታወቁ፡፡
የካቲት 17 ቀን 2007 ዓ.ም በፌደራሉ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት የቀረቡት የሰማያዊ (የፓርቲው የጎንደር አደራጅ አቶ አግባው ሰጠኝ)፣ የአንድነት እና መኢአድ የዞን አመራሮች “መረጃ አውጡ፣ የደበቃችሁትን ሁሉ ተናገሩ” እያሉ እንደሚደበድቧቸውና በጨለማ ክፍል እንዳሰሯቸው ተናግረዋል፡፡ ፖሊስ አሁንም መረጃየን ሰብስቤ አልጨረስኩም በሚል ተጨማሪ 8 ቀናት ጠይቆ ተፈቅዶለታል፡፡
ተጠርጣዎቹ በማዕከላዊ እየደረሰባቸው የሚገኘውን ሰቆቃ አስመልክተው ለፍርድ ቤት አቤት ማለታቸውን ተከትሎ ፍርድ ቤቱ ፖሊስ የቀረበበትን አቤቱታ እንዲያስተካክል ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡
ተጠርጣሪዎቹ በጎንደርና ጎጃም አካባቢዎች የዛሬ አራት ወር ገደማ በፖሊስ ታስረው ወደ አዲስ አበባ ማዕከላዊ ፌደራል ወንጀል ምርመራ እንዲዛወሩ የተደረጉ ሲሆን፣ ጠበቃቸው በተደረገባቸው ክልከላ ምክንያት ተጠርጣሪዎቹን ካገኟቸው 2 ወር እንደሞላቸው ተናግረዋል፡፡ ከተጠርጣሪዎቹ መካከል አቶ አግባው ሰጠኝ እየተፈጸመበት ያለውን የመብት ጥሰት በመቃወም የርሃብ አድማ ላይ መሆኑ የታወቀ ሲሆን አድማውን ከጀመረ ሁለተኛ ቀኑ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡
ፍርድ ቤቱ በሰጠው የጊዜ ቀጠሮ መሰረት አመራሮቹ የካቲት 25 ቀን 2007 ዓ.ም ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ (ነገረ ኢትዮጵያ ፌስቡክ ገጽ)
http://www.goolgule.com/opposition-party-leaders-under-severe-interrogation-and-torture/

ሳይገባቸው ቻይና በነገራቸው የሚያውቁትን የሚረሱ ማን ያስተምራቸው!


ፕ/ር መስፍን ወልደ-ማርያም

haile china



የጎረቤት ኬንያ ዳኛ ለኬንያ መንግሥት አስፈጻሚው ክፍል ልኩን ነገረው፤ ሕገ መንግሥቱን በመርፌ አስተኝተህ ሕገ መንግሥቱን የሚጻረር ሕግ ለማውጣት አትችልም፤ ስለዚህም የሰነዘርኸውን የጉልበት ሕግ አንሣ፤ አለው፤ ዳኛ አይጥፋ! ሌላ ቢቀር ከጎረቤት ዳኝነትን እንስማ፡፡
ኢትዮጵያ ውስጥ ዳኛ ቢኖር ስንት ጋዜጠኛ፣ ስንት የሃይማኖትና ስንት የፖሊቲካ መሪዎች ከየወህኒ ቤቱ ይወጡ ነበር! ሁላችንም እንደልባችን ሳንፈራ፣ ሳንፈራራ በሙሉ ነጻነት ችግሮቻችንን የወያኔን ጭቆና ጨምሮ ለመወያየትና መፍትሔዎችን ለመለዋወጥ የምንችልበት መድረክ፣ ጋዜጣ፣ መጽሔት፣ ራድዮና ቴሌቪዥን በኢትዮጵያ ውስጥ ይኖረን ነበር፤ ስንት ሰው ሥራ ያገኝ ነበር፡፡
ከሁሉም በላይ በየመንገዱ ጠመንጃ የያዘ ሊያስፈራራን የሚሞክር ሆድአደር እያየን፣ እንደዚሁም በየጫካው ያሉትን እያሰብን ሰላማችንን ከምናጣ አበባውን ትተን፣ ሩዙን ትተን፣ የተወደደልንን ጤፋችንን እያመረትን አዲስ ኑሮ ብንጀምር የተሻለ ነበር፡፡
ግን አንድ እንቅፋት አለብን፤ እነዚህ ከየኪዮስኩ እውቀት ገዝተን አዋቂዎች ሆነናል የሚሉት እንትኖች መጀመሪያ ችግሩ እንዲገባቸው፣ ሁለተኛ መፍትሔው እንዲገባቸው፣ ሦስተኛ ጉልበትና እውቀት አንድ አለመሆናቸውን ብቻ ሳይሆን በጉልበት እውቀት የማይገኝ መሆኑን ማሳመን በረዶ እየወረደ የስሜን ተራራን መውጣት ነው፤ በረዶ ሳይኖር ወጥቼዋለሁ!
እነዚህን የጉልበት አዋቂዎች — ስለሽማግሌዎችና አሮጊቶች ሳያስቡ፣ ስለመብራት ኃይል ሳያስቡ፣ ስለውሀ ሳያስቡ ሁሉም በጉልበት ፎቅ ይውጣ የሚሉ! ይባስ ብለው ለእስረኛውም ፎቅ እየሠሩለት ውጣ! ሊሉት ነው!
እነዚህ የጉልበት አዋቂዎች የአበሻ ኑሮ፣ ቡናው፣ ሙቀጫው፣ ምጣዱ፣ በርበሬው፣ ቁሌቱ፣ ቄጤማው፣ ዶሮና በግ ማረዱ፣ ኧረ ስንቱ! ሳይገባቸው ቻይና በነገራቸው የሚያውቁትን የሚረሱ ማን ያስተምራቸው! እናውቃለን ስለሚሉ እንዴትስ ይማራሉ? በእውነት ለመማር ቢፈልጉስ ስንት ዓመት ሊያስፈልጋቸው ነው!
እግዚአብሔር እነሱንም እኛንም በምሕረቱ ይጎብኘን! የሚያስተምር ጎረቤት አያሳጣን! (ምንጭ: ከፕ/ር መስፍን ፌስቡክ ገጽ)
http://www.goolgule.com/forgetting-what-they-have-learned-and-taught-by-the-chinese/

Thursday, February 19, 2015

20ኛው የዞን9 ጦማርያን እና ጋዜጠኞች የ”ፍርድ ቤት” ውሎ- በገዛ ፍቃዴ ለቅቄያለሁ ያሉት ዳኛ ደግመው ተሰይመዋል!


ለሶስት መቶ ቀናት በእስር ላይ የቆዬት ጦማርያን ለ20ኛ ጊዜ “ፍርድ ቤት” ቀርበዋል፡፡
ትላንትና የካቲት 12 ቀን ገዥው ህወሃት 41ደኛ ልደቱን ባከበረበት በተመሳሳይ ቀን በነሶልያን ሽመልስ የክስ መዝግብ “ፍርድ ቤት” የቀረቡት ጦማርያን እና ጋዜጠኞች የእምነት ክህደት ቃላቸውን ሰጥተዋል፡፡Zone 9 bloggers
“የፍርድ ሂደቱ” ጠዋት ሊጀመር ተቀጥሮ የነበረ ቢሆንም ያለቅጥ ዘግይተው የተሰየሙት ዳኞች ተከሳሾቹ ለከሰአት ስምንት ሰአት ለሚጀምረው ችሎት አንዲገኙ ለከሰአት ተቀጥረው ነበር፡፡ ከሰአት ስምንት ሰአት ላይ ችሎቱ ከመጀመሩ በፌት ባሉት ሰአታት ልደታ ፍርድ ቤት ጊዜያቸውን ያሳለፉት ጦማርያን ከሰአት በኋላ “ፍርድ ቤት” ቀርበዋል፡፡ ችሎቱ ላይ ባለፈው ቀጠሮ አቤቱታ ቀርቦባቸው አቤቱታውን “ፍርድ ቤቱ” ባይቀበለውም በገዛ ፍቃዴ ከችሎቱ ለቅቄያለሁ ያሉት ዳኛ ሸለመ በቀለ መልሰው ችሎቱን ሰብስበዋል ፡፡ ከችሎቱ ለመነሳታቸውም ሆነ ላለመነሳታቸው የተሰጠ ማብራሪያ ሳይኖር ከሁለተኛ ተከሳሽ ከጦማሪ በፍቃዱ ሃይሉ ጀምሮ እያንዳንዳቸው ተከሳሾች በስም እየተጠሩ የተጠረጠሩበትን ወንጀልመፈጸም እና አለመፈጸማቸውን ቃል አንዲሰጡ የተጠየቁት ጦማርያን እና ጋዜጠኞች ሲመልሱ
በፍቃዱ ሃይሉ – እኔ ክሱን ከአምስት ጊዜ በላይ በተደጋጋሚ አንብቤዋለሁ ምንም የሚገባ ነገር አላገኘሁበትም ሲል ዳኛው አቋርጠውት አሁን ምንም አይነት ዝርዝር ውስጥ አልገባም በማለታቸው “የሽብር ወንጀል ለመፈጸም አላሰብኩም አልፈጸምኩት አልፈጽምም ሽብር ተፈጽሞብኛል” ሲል መልሷል፡፡ ከበፍቃዱ በማስከተል ቃሉን የሰጠው ጦማሪ ናትናኤል “ህግ የሚከበርበት አገር ቢሆን ኖሮ ዛሬ እዚህ ቦታ መቆም የነበረባቸው አሳሪዎቼ ናቸው ፣ ምንም ወንጀል አልፈጸምኩም “ያለ ሲሆን ጦማሪ አጥናፍ “ወንጀል አልፈጸምኩም” ፣ ጦማሪት ማህሌት “ምንም አይነት ወንጀል አልፈጸምኩም” ብላ ቃሏን ስትሰጥ ጦማሪ አቤል በበኩሉ “ክሱ ግልጽ አይደለም” ሲል ዳኛው ምንም አይነት ተጨማሪ ነገር ሳያስፈልግ ቀጥታ ቃል እንዲሰጥ ማሰጠንቀቂያ ሰጥተዋል፡፡ በመሆኑም አቤል “የህብረተሰቡን ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥል ምንም አይነት የሽብር ተግባር አልፈጸምኩም አላሴርኩም” ሲል በቀጥታ ክሱ ላይ የተጠቀሰውን አንቀጽ ጠቅሶ ቃሉን ሰጥቷል፡፡ ጦማሪ ዘላለም በበኩሉ የተከሰሰበት ወንጀል አንዲብራራለት የጠየቀ ሲሆነ “ፍርድ ቤቱ” ወደኋላ አንመለስም የሚል ማስፈራሩያ በማሰማት በቀጥታ ቃሉን እንዲሰጥ ሲነገረው “የተከሰስኩበት ክስ ግልጽ ባልሆነበት ሁኔታ የእምነት ክህደት ቃሌን መስጠት አልችልም” በማለት በመናገሩ ቃሉን ሳይሰጥ ቀርቷል ፡፡ በህጉ መሰረትም ጥፋተኛ አይደለሁም አንዳለ ተቆጥሮ ተመዝግቧል፡፡
ጋዜጠኛ ኤዶም ካሳዬ -” ምንም ወንጀል አልፈጸምኩም እኔ ነጻ ሰው ነኝ ” ስትል ጋዜጠኛ አስማመው “ወንጀል አልፈጸምኩም” ጋዜጠኛ ተስፋለም ደግሞ “እኔ ጋዜጠኛ ነኝ ጋዜጠኝነት ወንጀል አይደለም እኔ ምንም ወንጀል አልፈጸምኩም” ብሏል፡።
የእምነት ክህደት ቃል መስጠቱነ ተከትሎ አቃቤ ህግ ምስክሮቸን ለመስማት ተለዋጭ ቀጠሮ ይሰጠኝ ብሎ በጠየቀው መሰረት ከአርባ ቀን በኋላ ለመጋቢት 21-23 ለሶስት ቀናት የሰውና የሰነድ ማስረጃ ለማቅረብ ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡ የተከሳሾች ጠበቆች በበኩላቸው አለ የተባለው የሲዲ ማስረጃ ግልባጭ ስላልተሰጠን አንዲሰጠን ብለው የጠየቁ ሲሆን “ፍርድ ቤቱ” እንዲሰጣቸው ትእዛዝ ሰጥቷል፡፡
የተከሳሾች አያያዝ
ባለፈው ችሎት ወቅት ጦማሪ አቤል ዋበላ ያቀረበውን አቤቱታ ተከትሎ ማረሚያ ቤቱ መልስ አንዲሰጥ መጠየቁ የሚታወስ ሲሆን የጦማሪው ጠበቃ ተከሳሹ ከማረሚያ ቤት አስተዳደሩ ጋር በመነጋገር ችግሩን ስለፈቱት አቤቱታውን መቅረቱን ለ”ፍርድ ቤቱ” ተናግረዋል፡፡ ጦማሪ አቤልም በበኩሉ ተጨማሪ የመብት ጥሰት አስካልደረሰብኝ ድረስ ባለፈውን አቤቱታዬን ትቼዋለሁ ያለ ሲሆን ባለፈው ተቀምቶ የነበረው የጆሮ ማዳመጫ መሳሪያም ተመልሶለታል ፡፡ ነገር ግን የሴት ተከሳሾች አያያዝ አንደአዲስ አስቸጋሪ እንደሆነ የሚያያቸው ሰው ገደብ እንዳልተነሳ እና አሁንም በጥቂት ሰዎች ብቻ አንደሚጠየቁ ለፍርድ ቤቱ አቤቱታ በማቅረባቸው የእነሱን አያያዝ አስመልክቶ ማረሚያ ቤቱ መልስ አንዲሰጥ ለመጋቢት 18 ጠዋት ቀጠሮ ተሰጥቶ ችሎቱ ተጠናቋል ፡፡
የዞን9 ማስታወሻ
ሶስት መቶ ቀን እስር እና ከሃያ ቀጠሮ በኋላ የተጀመረው ይህ መደበኛ “የፍርድ ሂደት” እንደተለመደው መጓተቱ ሳያንስ በአንድ ወር በላይ የሚፈጅ ቀጠሮ መሰጠቱ ለክሱ ፓለቲካዊነት አንዱ መገለጫ እንደሆነ እናምናለን፡፡ ሶስት ወር በፈጀ ምርመራ ሂደት ውስጥ ተገኙ የተባሉትን ማስረጃዎች ለማቅረብ የ40 ቀን መዘጋጃ ጊዜ አንደማያስፈልግ ለማንም ሰው በግልጽ የሚታይ ሃቅ ነው ፡፡ በመሆኑም ባለፈው የቀረበው አቤቱታ ላይ አንደተገለጸው ዳኛውም ሆነ የፍትህ ስርአቱ አላግባብ መታሰራችን እና መከሰሳችን ሳያንስ አንድን “የፍርድ ሂደት” በማራዘም አፋጣኝ ፍትህ የማግኘት መብት መቀለጃ እየሆነ አንደሆነ እያሳዬን ነው፡፡ የዞን9 ነዋሪያንና አንባቢዎችም ይህ ፍትህ ስርአቱ ስም የሚደረግ ቀልድ አንደማይጠፋቸው አናምናለን ፡፡
የዞን9 ጦማርያን እና ወዳጅ ጋዜጠኞች በመልካም ጤንነት በጠንካራ ስነልቦና እና በራስ መተማመን ስርአቱን ፌትለፌት እየተገዳደሩ ያሉ ኩሩ ልበ ሙሉ ወጣት ዜጎች ናቸው ፡፡ የተለየ ሃሳብን በሚያራምዱ ጥቂት ወጣቶች የተሸበረውን መንግሰት የምናፍርበት ያህል በጓደኞቻችን አንኮራለን ፡፡
የዞን9 ኩራት ጦማሪ በፍቃዱ ሃይሉ በድጋሚ መልካም ልደት
ስለሚያገባን እንጦምራለን ፡፡
ዞን9
http://ecadforum.com/Amharic/archives/14450/

የ2007ቱን ሀገራዊ ምርጫ ሂደት እና ከምርጫዉ ዉጭ ያሉ አዋጭ አማራጮችን በተመለከተ የአርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ የአቋም መግለጫ


  • Share
    አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ በሰላማዊ፣ ተዓማኒና ፍትሀዊ በሆነ ምርጫ የማይፈልጋቸውን መሪዎች መሻር፤ የሚፈልጋቸውን ደግሞ መሾም የሚያስችሉትን መሠረቶች ለመጣል የሚታገል ንቅናቄ ነው። እንደሚታወቀው የሕዝብ እውነተኛ ፍላጎት የሚገለጽበት እውነተኛ ምርጫ እንዲኖር ገለልተኛና ቀልጣፋ የፍትህ ሥርዓት፣ የጦርና የፓሊስ ሠራዊት ሊኖሩ ይገባል። ነፃ የሚዲያ ተቋማትና በነፃነት የሚንቀሳቀሱ የሲቪክ ማኅበራት መኖርም መታለፍ የሌለባቸው አቢይ ጉዳዮች ናቸው። አማራጭ ፓሊሲዎችን ማቅረብ የሚችሉ በነፃነት የሚንቀሳቀሱ የፓለቲካ ፓርቲዎች ከሌሉም አማራጮች የሉምና ምርጫ ትርጉም የለውም። ይህ ሁሉ ቢሟላ እንኳን ምርጫውን የሚያስፈጽመው አካል ገለልተኛ፣ ሀቀኛና ተዓማኒ ካልሆነ የሚደረገው ምርጫ የመራጩን ሕዝብ ፍላጎት የሚያንፀባርቅ ሊሆን አይችልም።
g 7ከላይ የተዘረዘሩትን የምርጫ እሴቶች ሙሉ በሙሉ ባይሆንም እንኳን የተወሰኑትን በመጠኑም ቢሆን ያካተተ ምርጫ እንዲኖር መጣርና በሂደት የምርጫውን አፈፃፀም ማሻሻል ይቻል ይሆናል በሚል እምነት የዲሞክራሲ ኃይሎች በህወሓት የሴራ ምርጫዎች ሲሳተፉ ቆይተዋል። ሆኖም በህወሓትና በእውነተኛ ምርጫ መካከል  ያለው ተቃርኖ እያደር እየሰፋ ሲሄድ እንጂ ሲጠብ አልታየም።  በህወሓት ሙሉ ቁጥጥር ስር በሚካሄድ ምርጫ ኢትዮጵያን የሚጠቅም ለውጥ ሊመጣ ይችላል የሚለው እምነት ለአርበኞች ግንቦት 7 ፈጽሞ የተሟጠጠው ከምርጫ 97 ማግስት ጀምሮ  ነው። በግንቦት 7 ቀን 1997 ዓም የኢትዮጵያ ሕዝብ በታላቅ የለውጥ ተስፋ የሰጠው ድምጽ በህወሓት የተዘረፈው ከላይ የተዘረዘሩት ተቋማት ያልነበሩ በመሆናቸው፤ ስለዚህም ከምርጫ በፊት ተቋማቱን መገንባት፤ ተቋማቱን ለመገንባት ደግሞ ህወሓትን ከስልጣን ማስወገድ ይገባል ብሎ በማመኑ ነው አርበኞች ግንቦት 7 በሁለገብ የትግል ስልት በመንቀሳቀስ ላይ የሚገኘው።
ያም ሆኖ ግን በምርጫ ላይ ያላቸው ተስፋ ፈጽሞ ያልተሟጠጠ ፓርቲዎችን በማክበርና ሥራቸውንም አስቸጋሪ ላለማድረግ ሲባል ከምርጫ 97 ወዲህ የነበሩ ብሄራዊም ሆነ ክልላዊ ምርጫዎችን አስመልክቶ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከምርጫ ዉጭ ያሉ ሌሎች አማራጮችን ብቻ እንዲመለከት አርበኞች ግንቦት 7 ጥሪ አድርጎ አያውቅም ነበር። አሁን ግን የአገራችን ኢትዮጵያ የፓለቲካ ሁኔታዎች  ይህንን የቆየ አቋም በሚያስቀይር መንገድ፤ የአገራችንን የወደፊት ዕድል ብቻ ሳይሆን ባጠቃላይ ያካባቢውን ሰላም በሚጎዳ መልኩ ተቀይሯል። የሰሞኑ የወያኔ እርምጃዎች ትንሽ ተስፋ ያደርግ የነበረውን የዴሞክራሲ ወገንተኛ ተስፋም እምሽክ አድርጎ በልቶታል:: እየተቃረበ ያለው ዓይነት የፌዝ ምርጫ ወያኔ እንደ እንጄራ የራበውን የተቀባይነት እጦት ለአጭር ጊዜ ያስታግስለት ይሆናል እንጂ የሀገሪቱን እያደር እየተወሳሰበ የመጣ ችግር ለጊዜውም እንኳን የሚያስታግስ አይሆንም፤ ይልቁንም ጊዜው በገፋ ቁጥር ችግሩ መቋጠሪያ የጠፋው እየሆነ ይሄዳል::
የሁኔታውን አሳሳቢነት ከግምት ውስጥ በማስገባት የአርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ለዲሞክራሲ ንቅናቄ አመራር የወቅቱን የአገራችን የፓለቲካ ሁኔታ በጥንቃቄ መርምሮ የሚከተሉት ግንዛቤዎች ላይ ደርሷል።
  1. ህወሓት ብዙዎች እትዮጵያዊያን የተሰውላቸውን አንድነት ፓርቲንና መኢአድን በመበተን የድርጅቶቹን ስምና ንብረት ለአገልጋዮቹ መስጠቱ፤ ከዚህ በፊት ሲያደርግ እንደነበረው የመራጭን ድምጽ መስረቅ ሳይበቃው የምርጫ ተወዳዳሪንም መዝረፍ መጀመሩን አመላካች ነው። ይህ ተግባር ህወሓት የምርጫ ውጤትን ብቻ ሳይሆን ተወዳዳሪዎችንም እሱ ራሱ ለመምረጥ መወሰኑን ያሳያል፤ ከዚህ በተጨማሪ የሴራ ምርጫውን ከጅምሩ ጀምሮ አስቀድሞ እስከተወሰነለት መዳረሻው ድረስ ለምንም ዓይነት ያልተጠበቀ አጋጣሚ (በምርጫው ወቅት የሚደረጉትን ክርክር ተብዬዎች ጨምሮ) እድል ላለመስጠት ወስኖ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን በግልጽ ያሳያል፤
  2. ይህ እኩይ ውሳኔ በምርጫ ቦርድ ፊርማና አንደበት ቢነገርም ምንጩ የህወሓት ፓሊት ቢሮ  መሆኑን የሚከተሉት ተግባራት ይጠቁማሉ፤
2.1.         በምርጫ ቦርድ በኩል እንዲገለጽ የተወሰነው እርምጃ ለማስመሰል ያክልም ቢሆን የህጋዊነት ሽፋን እንዲኖረው አለመደረጉ ውሳኔው ፍጹም እብሪተኛ በሆነ አካል መወሰኑን ያመለክታል። እንዲህ                   ዓይነቱ እብሪተኛ አካል ደግሞ የህወሓት ፓሊት ቢሮ ነው። ውሳኔውን ለማስፈፀም የነበረው ጥድፊያም ይህንኑ ያጠናክራል።
2.2.        ለማስመሰያ ያክል እንኳን ምንም አይነት የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ሳይኖር ፓሊስ የአንድነትና የመኢአድ ቢሮዎችን መውረሩ፤ ህወሓት አንድነትንና መኢአድን አጥፍቶ የድርጅቶቹን ስሞችና ንብረቶች                   ለሚፈልጋቸው ሰዎች ሰጥቶ በአስቸኳይ ለምርጫ ድራማው በፊት መስመር ሊያሰልፋቸው መወሰኑን አመላካች ነው። እንዲህ ዓይነት ከባድ ውሳኔ የሚሰጠው ደግሞ የህወሓት ፓሊት ቢሮ ብቻ                    ነው።
2.3.        ወደ ፈቃድ መንጠቅ ከመደረሱ በፊትም በሰማያዊ ፓርቲ፣ በአንድነትና በመኢአድ አባላት የደረሰው አረመኔያዊ ድብደባ፤ ንቁ የፓለቲካ ተሳትፎ የሚያደርጉ ዜጎች ላይ የሚደርሰው እስር፣ መሰወርና                 እና ባልታወቁ ሰዎች ተገድሎ መገኘት መብዛት እነዚህን አገራዊ ፓርቲዎች የመበተን የፓለቲካ ውሳኔ መሰጠቱን አመላካቾች ናቸው።
  1. ለጊዜው የፈቃድ ነጠቃና የንብረት ዘረፋ የተፈፀመው በአንድነትና በመኢአድ ላይ ቢሆንም በሰማያዊ ፓርቲ ላይ በየእለቱ እየጠነከረ የመጣው የአፈና እርምጃም በተመሳሳይ ፓርቲውን ወደማገድ አለዚያም ፈጽሞ መንቀሳቀስ ወደማይችልበት ደረጃ ሊያደርሰው ይችላል የሚል እምነት አሳድሯል። ሌሎች ፓርቲዎችም ከዚህ ህወሓት ካሰመረው የውሸት ጫወታ መስመር የመውጣት ዝንባሌ ቢያሳዩ ተመሳሳይ እርምጃ አይቀርላቸውም።
  2. የህወሓት የወቅቱ የጥፋት ዒላማ ያነጣጠረው አንፃራዊ በሆነ መንገድ የተሻለ መዋቅርና ማኅበራዊ መሠረት ባላቸው እና በአገራዊ አጀንዳዎቻቸው በሚታወቁ ፓርቲዎች ላይ መሆኑ፤ የወቅቱ የጥፋት ዘመቻ የኢትዮጵያ አንድነትን የማዳከምና ከፋፍሎ የመግዛት የህወሓት ትልቁ አጀንዳ አካል መሆኑን ያሳያል።
  3. እራሱን በዘር ያደራጀዉና ኢትዮጰያ ዉስጥ ያለዉ ፖለቲካዊና ማኅበራዊ አደረጃጀት ከዚሁ እሱ ከተደራጀበት የዘር አደረጃጀት ዉጭ እንዲሆን በፍጹም የማይፈቅደዉ የወያኔ አገዛዝ፤ መጣፊያው ሲያጥረውና ወደ ማይቀረው ውድቀቱ ሲያመራ፤ እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል እንዳለችው አህያ አገራችን ኢትዮጵያን በቀላሉ ወደማትወጣዉ የዘዉግ ግጭት ዉስጥ አስገብቶ ዘመናት ያስቆጠረዉ አንድነቷ እንዲፈረስ በትጋት እየሠራ መሆኑን ያሳያል።
  4. ከመለስ ዜናዊ ሞት ወዲህ ህወሓት ከሁሉን ጠቅላይ (totalitarian) አገዛዝ ወደ ፋሽስታዊ ቡድንነት ያሽቆለቆለ መሆኑን አርበኞች ግንቦት 7 ተገንዝቧል። ህወሓት ዘረኛ፣ ጠቅላይና ፈላጭ ቆራጭ ጨቌኝ በመሆኑ ፋሽስት ብለነዋል።  ሆኖም በታሪክ የሚታወቁ ፋሺስታዊ አገዛዞች ከፍተኛ ብሄራዊ ስሜት የነበራቸው ሲሆን የህወሓት ፋሽስታዊ አገዛዝ ግን ብሔራው ስሜት አልባ መሆኑ ልዩ እና የበለጠ አደገኛ ያደርገዋል። ይህ ፋሽስታዊ ቡድን የህወሓት መሪዎችንና ጥቂት ሌሎች አጫፋሪዎቻቸውን የያዘ ለጊዜው አስተባባሪ መሪ የሌለው ሆኖም ግን የጦር ሠራዊትን፣ የስለላ መዋቅሩንና ፓሊስን ተቆጣጥሮ በአሁኑ ሰዓት ኢትዮጵያን እየገዛ ያለው ይህ አስኳል የለሽ ፋሽስታዊ ቡድን መሆኑ እጅግ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን አርበኞች ግንቦት 7 ተገንዝቧል። ይህ ፋሽስታዊ ቡድን ተደላድሎ መሪ እንዲፈጥር ከተፈቀደለት አገራችንን የከፋ መከራ ውስጥ ሊከታት እንደሚችል ግንዛቤ ተወስዷል።

ከላይ በአጭሩ ከተራ ቁጥ 1 እስከ 6 የተዘረዘሩትን በማገናዘብ በግንቦት 2007 ሊደረግ የታቀደውን አምስተኛው ዙር ሀገር አቀፍ የሴራ ምርጫን በተመለከተ የአርበኞች ግንቦት 7 አመራር ውሳኔዎችን አስተላልፎ ከዚህ የሚከተሉት ጥሪዎችን ለኢትዮጵያ ሕዝብ አቅርቧል።
  1. በምርጫ 2007 መሳተፍ ለዲሞክራሲያዊ ለውጥ ሁኔታዎችን ከማመቻቸት ይልቅ ፋሽስታዊውን ቡድን የሚያጠናክርና የኢትዮጵያን ሕዝብ የወደፊት ዕድል የሚገድል በመሆኑ፣ ለፍትህ፣ ለነፃነት፤ ለዲሞክራሲና ለአገር አንድነት ግድ ያላቸው ወገኖች ሁሉ ከአሁኑ ከዚህ የይስሙላ ምርጫ ዉጭ ዓይኖቻቸውንና ሙሉ ጉልበታቸዉን በሌሎች የኢትዮጵያን ሕዝብ ነፃነት በሚያፋጥኑ አማራጮች ላይ እንዲያሳርፉ ጥሪ ያደርጋል። አርበኞች ግንቦት 7 የኢትዮጵያ ሕዝብ ከዚህ ዓይን ያወጣ የሴራ ምርጫ ይልቅ መብቱን፤ ነፃነቱንና እኩልነቱን በሚያፋጥኑለት በሕዝባዊ እምቢተኝነትና በሕዝባዊ አመፅ የትግል አመራጮች ላይ እንዲሳትፍ ለመላው ያገሪቱ ሕዝብ ጥሪ ያስተላልፋል።  ህወሓት ማኅበረሰባችንን ለመከፋፈልና ለማባላት የሚያደርገውን እኩይ ሴራ በጋራ እንድናከሽፈው ወገናዊ ጥሪ ያስተላልፋል፤ “አንከፋፈልም፤ ተከፋፍለንም አንጠቃም“ እንበል ይላል::
  2. ህወሓትን ማስወገድ የሚቻለው በሕዝባዊ እምቢተኝነትና በሕዝባዊ አመጽ በመሆኑ፤  ከሁለቱ አንዱንም አለመያዝ ሌላ ሰው ታግሎ ነፃነቴን ያቀዳጀኝ እንደማለት የሚቆጠር በመሆኑ፤ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ በአፋጣኝ ከእነዚህ ሁለት የትግል ዘርፎች ዉስጥ የተሻለ አስተዋጽኦ አበረክታለሁ በሚለው የትግል ዘርፍ ውስጥ ተሳትፎ  እንዲያደርግ ጥሪ ያቀርባል።
  3. አርበኞች ግንቦት 7፣ በሁለቱም የትግል ዘርፎች ድርጅታዊ መዋቅሩን እያሰፋና ከሌሎች ድርጅቶች ጋር በመተባበር በሕዝባዊ እምቢተኝነትና በሕዝባዊ አመጽ ህወሓትን ከስልጣን ለማስወገድ አቅዶ በመንቀሳቀስ ላይ የሚገኝ በመሆኑ ኢትዮጵያዊያን በስፋት እንዲቀላቀሉት፤ በኅብረት እንድንቆም እና የህወሓትን ውድቀትና የኢትዮጵያን ትንሳኤ እንድናፋጥን ጥሪ ያደርጋል::
  4. ያለንን አቅም በሙሉ ህወሓትን በማስወገድ ላይ ካዋልነው አንድ ጠንክር ያለ ሕዝባዊ አመጽ አገዛዙን ሊያፍረክርክው የሚችል በመሆኑ፤ በአንድ ወይም በሌላ መንገድ ከምርጫ ጋር ለተያያዙ ሥራዎች ሊውል ታስቦ የነበረው የሰው ኃይል፣ ጊዜ፣ ገንዘብና እውቀት ለሕዝባዊ አብዮት መቀስቀሻነት እንዲውል ጥሪ ያደርጋል።
  5. በውጭ አገራት የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችንም በ2007 ምርጫ ላይ ጊዜና ንብረት ከማባከን ይልቅ በአንድ ልብ በኢትዮጵያ ውስጥ ለሕዝባዊ አብዮት መቀስቀስ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ ጥሪ ያደርጋል።   ከሁሉም ዴሞክራሲያዊ ኃይሎች የተውጣጣ አካል የዚህን ጥሪ ተፈፃሚነት እንዲከታተል ቢደረግ ይበልጥ ውጤታማ ይሆናል ብሎ ያምናል።

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/39133

Sunday, February 8, 2015

ልደቱ አያሌው በቀጣዩ “ምርጫ” አልወዳደርም አሉ – “ካለፉት ምርጫዎች የተለየ ምንም ነገር አይመጣም” ሲሉ ምርጫውን አጣጣሉት

lidetu ayalew
“ቴአትረ ቦለቲካ” የሚል መፅሃፍ ሊያወጡ ነው
በመጪው ግንቦት በሚካሄደው አገራዊ ምርጫ ካለፈው ምርጫ የተለየ ውጤት ቨመጣል ብለው እንደማይጠብቁ የተናገሩት የቀድሞው የኢዴፓ ፕሬዚዳንት አቶ ልደቱ አያሌው፤ በምርጫውም እንደማይወዳደሩ አስታወቁ፡፡ በ “ቴአትረ ቦፖለቲካ ፣ አሉባልታና የአገራችን ፖለቲካ ገመና” በሚል ርዕስ የፃፉት አዲስ መፅሀፍ በቅርቡ በገበያ ላይ እንደሚውልም ተናግረዋል፡፡
“የኢህአዴግን አካሄድና የተቃዋሚው ጎራ ያለበትን ሁኔታ ሳየው በግንቦቱ ምርጫ ካለፈው የተለየ ነገር ይመጣል ብዬ አላስብም” ያሉት አቶ ልደቱ፤ ኢህአዴግ ምርጫውን ሙሉ በሙሉ በራሱ ቁጥጥር ስር አድርጎ እንደቀጠለ ነው፣ ተቃዋሚው ጎራም ካለፉት ስህተቶቹና ድክመቶቹ ተምሮ ራሱን ለማሻሻል ያደረገው ብዙ ነገር የለም ሲሉ ምክንያታቸውን ገልፀዋል፡፡ “ድፍረት አይሁንብኝ እንጂ ተቃዋሚው ጎራ በፓርላማ ያለችውን አንድ መቀመጫ አስጠብቆ ይቀጥላል ወይ የሚለው በራሱ ለኔ ጥያቄ ነው” ሲሉም ጥርጣሬያቸውን አስቀምጠዋል፡፡
በተቃዋሚ ፓርቲ ዙሪያ የተደረጉ የትብብር ሙከራዎች ትግሉን የጎዱ እንጂ የጠቀሙ አይደሉም ሲሉ የሚሞግቱት አቶ ልደቱ፤ ፓርቲዎች በእንተባበር ጥያቄዎች ባይዳከሙ ኖሮ በአሁኑ ወቅት ሁለት ወይም ሶስት ጠንካራ ፓርቲዎች ይኖሩን ነበር ብለዋል፡፡
“ቴአትረ ቦለቲካ፡ አሉባልታና የአገራችን ፖለቲካ ገመና” የተሰኘ ሶስተኛ መፅሃፋቸው በቅርቡ እንደሚወጣ የጠቆሙት አቶ ልደቱ፤ መፅሃፉ በኢትዮጵያ ፖለቲካ አሉባልታዎች ዙሪያ እንደሚያጠነጥን ተናግረዋል፡፡ አሉባልታ የተቃውሞ ጎራውን ትግል ክፉኛ እንደጎዳውም ከአዲስ አድማስ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ገልጸዋል፡፡
- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/38800#sthash.dwCFcPry.dpuf

Saturday, January 3, 2015

“እንደ ኢህአዴግ ያለ አሸባሪ የለም” አብርሃ ደስታ

"በሐሰት ፕሮፖጋንዳ ሰው ማሳበድ ይፈልጋሉ" ኦኬሎ አኳይ

abraha and okello


ከቂሊንጦ እስር ቤት ከሚገኙት መካከል የነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር ያነጋገራቸው አብርሃ ደስታና የቀድሞው የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት ኦኬሎ አኳይ፣ ስለ እስራቸው ሁኔታ እንዲህ ይላሉ:: በቅድሚያ አብርሃ ደስታ:-
“እዚህ እስር ቤት ውስጥ በሽብር ስም የገባ ሰው በፈጠራ ወንጀል እንደገባ ነው የሚታመነው፡፡ ስለዚህ የሽበር ክስ ተመስርቶባቸው የታሰሩትን ሰዎች ማንም ወንጀለኛ አድርጎ አይመለከታቸውም፡፡ በእርግጥም አሸባሪ የለም፤ የፈጠራ ክስ ነው ያሳሰራቸው፡፡ አሸባሪ አለ ከተባለም እንደ ኢህአዴግ ያለ አሸባሪ የለም፡፡
“ነጻ መውጣት ያለበት ቡድን አለ፣ እሱም ኢህአዴግ ራሱ ነው፡፡ እኔ አልታሰርኩም፡፡ የታሰሩት ኢህአዴጎች ናቸው፡፡ እስር የአዕምሮ ነው፡፡ እኔ አዕምሮየ አልታሰረም፡፡ ነጻ ሰው ነኝ፤ ውስጤ በጣም ነጻነት አለው፡፡ የታሰሩት ኢህአዴጎች ናቸው፡፡
“እኔ እስር ቤት እንድገኝ ያደረገኝ ወንጀል አይደለም፡፡ መቃወሜና ይህን ተቃውሞየን በጽሑፍም በፊት ለፊትም መግለጼ ነው፡፡ ይህን ደግሞ ብዙ ኢትዮጵያውያን ያውቁልኛል፡፡ ሌላው ቢቀር ጥቂት የህወሓት ሰዎችም ያለ መረጃ እንደታሰርኩኝ በማመን እስሩን እየተቃወሙ ይመስለኛል፡፡ አንድ ቀን ወደ ህሊናቸው ከተመለሱ ስህተታቸው በህዝብ ፊት ያዋርዳቸዋል፡፡”
“በሐሰት ፕሮፖጋንዳ ሰው ማሳበድ ይፈልጋሉ” ኦኬሎ አኳይ፣ የቀድሞው የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት
“የሆነ ያልሆነውን የሚያወራው በዙሪያዬ ቢሰበሰብም እኔ በጣም ሰላም ይሰማኛል፡፡ ካድሬዎች አብረውን እስር ቤት አሉ፡፡ ወሬ ነው የሚለቃቅሙት፡፡ ይህን ወሬ ሲለቃቅሙ ይቆዩና የሆነ ያልሆነውን እያወሩ፣ የሐሰት ፕሮፖጋንዳ እየነዙ ሊያሳብዱህ ይሞክራሉ፡፡ እስር ቤትም ችግር ፈጣሪዎች ራሳቸው ኢህአዴጎች ናቸው፡፡ እኔማ ሰላማዊ ሰው ነኝ፡፡ ጉዳዩንም ፍርድ ቤት ይጨርሰው፡፡ ፍትህ አገኛለሁ ብዬ ባላስብም ፍርድ ቤት የሚወስነውን እጠብቃለሁ፡፡
“እየመጡ የሚጠይቁኝ ዘመዶች አሉኝ፡፡ ቤተሰቦቼ ደህና መሆናቸውን መረጃ አገኛለሁ፡፡ ስለዚህ ምንም የምረበሽበት ነገር የለም፡፡ በህግ የምከራከርባቸው ብዙ ነጥቦች አሉ፡፡ ቢሆንም ከውሳኔ በፊት ምንም ባልናገር ጥሩ ነው፡፡ እዚህ ድረስ እየመጡ ለሚጠይቁኝ ሁሉ ክብር አለኝ፡፡” (በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር)
http://www.goolgule.com/eprdf-is-the-most-notorious-terrorist/

ወ/ሮ ገነት ዘውዴ እውን ነገሩ እንዲያ ነውን?


(ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው)

genet zewdie


ወ/ሮ ገነት ዘውዴ (ዮዲት ጉዲት) ይቅርታ መሳደቤ አይደለም ሰው የሚያውቃቸው በዚህ ስም በመሆኑና የሚኮሩበትም በመሆኑ እንጅ፡፡ እናም ወ/ሮ ገነት በቅርቡ በሸገር የኤፍ ኤም ሬዲዮ (ነጋሪተ- ወግ) “የሸገር እንግዳ” በተባለው ዝግጅት እንግዳ ሆነው አዘጋጇ ጋዜጠኛ ወ/ሮ መዓዛ ሦስት ቅዳሜ አዋይተዋቸው ነበር፡፡ በዚያ ጨዋታቸው ወ/ሮ ገነት ከተናገሩት ብዙው ነገር ከንክኖኝ ከጊዜ አንጻር ባይሆን በጥቂቶቹ ላይ ጥቂት ነገር ለማለት አስቤ እየጫጫርኩ እያለሁ እንዲያውም በወ/ሮዋ በሐሰት ስማቸው ከጠፋ ወገኖችና ጉዳዩ በቀጥታ ከሚመለከታቸው አንደኛው በጥሩ ምሁራዊ ተዋስኦ የተዋዛ ምላሽ ሰጥተው አሻሩልኝ፡፡ ይሁንና ወ/ሮዋ የተናገሩት አጉል ነገር በርካታ በመሆኑ ሁሉንም ለመዳሰስ ከጊዜና ከቦታ አንጻር የማይቻል በመሆኑ ዶክተሩ ለሁሉም አጉል ነገር መልስ ሳይሰጡ ቀሩ፡፡ እኔም እንማማርባቸው ዘንድ ይጠቅማሉ ብየ ባሰብኳቸው በዚያ በወይዘሮዋ ወግ በተነሡ ሁለት ዐበይት አጉል ጉዳዮች ላይ አተኩሬ የተቻለኝን ያህል ለማለት ፈለኩ፡፡ እነኝህ ወ/ሮዋ የተናገሩት ሁለት ዐበይት አጉል ነገሮችም አንደኛው ወይዘሮዋ “የግራ ዘመም የፖለቲካ (የእምነተ-አሥተዳደር) አስተሳሰብ አራማጅ በመሆኔ” እያሉ የተናገሯቸው ነገሮች ሲሆኑ ሁለተኛው ደግሞ ሀገራችንን የሴቶች ሲዖል አድርገው ያቀረቡት ነገር ነው፡፡
ወ/ሮ ገነት ግራ ዘመም የፖለቲካ (የእምነተ አሥተዳደር) እምነትን ወይም አሥተዳደርን (left political belief) የተረዱት በተሳሳተ አረዳድ ነው፡፡ ለወ/ሮ ገነት ግራ ዘመም ፖለቲከኛነት (እምነተ-አሥተዳደሬነት) ማለት ነባሩን አስተሳሰብ ሙሉ ለሙሉ መቃረን መቃወም ማለት ነው፡፡ ነገር ግን ግራ ዘመም እምነተ አስተዳደር ማለት የራስን መጣል መተው መቃረን ማለት ሳይሆን የሶሻሊዝምን (የኅብረተሰባዊነትን) የፖለቲካ (የእምነተ-አሥተዳደር) ርዕዮተዓለም (Ideology) መከተል ወይም መቀበል ማለት ነው፡፡ ይህ ችግር የወ/ሮ ገነት ችግር ብቻ አይደለም በዚያ ዘመን የነበረው ትውልድ ሁሉ ሊባል በሚችል ደረጃ የነበረውን የፖለቲካ ማዕበል ይንጠው የነበረውም እንጅ፡፡
በስለው ከማይበስሉት ከጥቂቶቹ በስተቀር ብዙዎቹ ዛሬ ላይ ሰክነው ሲያስቡት በዚያ ጊዜ የነበራቸው አስተሳሰብ የተሳሳተ እንደነበረ ከመረዳታቸው የተነሣ ያ ዘመን የእብደት ዘመን እንደነበር ሐፍረት እየተሰማቸው ይናገራሉ፡፡ ይህ የጸጸት ስሜት ከግለሰቦችም አልፎ በዚያ የስሕተት ማዕበል ይናጡ የነበሩ ሀገራትም ተጋርተውታል፡፡ የግራ ዘመም ፖለቲከኞች (እምነተ-አስተዳደራዊያን) በነበራቸው የተሳሳተ ግንዛቤ የተነሣ ያራምዱት የነበረው የግራ ዘመም አስተሳሰብ የዜሮ (የባዶ) ብዜት ማለት ነበር፡፡ የነበረውን ነገር አጥፍቶ ከዜሮ የመጀመር የድንቁርና ሥራ ማለት ነው፡፡ በተለይም እንደኛ ጥንታዊና ለሌሎችም የተረፈ ሥልጣኔ ባለቤት በነበረች ወይም በሆነች ሀገር ላይ የነበረውን ብዙ የተለፋበትን የተደከመበትን መሥዋዕትነት የተከፈለበትን ነገር ሁሉ በዜሮ አጣፍቶ ከዜሮ መጀመር ምን ያህል እብደትና ድንቁርና እንደሆነ ቢያንስ አሁን ላይ የማይረዳ ሰው ይኖራል ብየ አላስብም፡፡ አሀ! ለካ እነ ወ/ሮ ገነት አሉ እሽ ከእነሱ ውጭ በሚል ይስተካከልልኝ፡፡
አንድ ሀገርና ማኅበረሰብ ታሪካዊና ጥንታዊ ከሆነ በረጅም ጊዜ ቆይታውና ሒደት ማንነቱን ባሕሉን ሃይማኖቱን አየር ንብረቱን ሳይቀር መሠረት በማድረግ የሚያፈራው በርካታ የተለያዩ ዓይነት እሴቶች ይኖሩታል እነዚህ በሒደት በሞክሮ ማየት (trial and error) የሚጠቅመውን በመያዝ የማይጠቅመውን በመተው ሒደት የሚያዳብራቸው ብዙ ዓይነት አስተሳሰቦች መኖራቸው የማይቀር ነው፡፡ ታዲያ አንድ ትውልድ ድንገት ተነሥቶ ከባዕድ በተጫነው አስተሳሰብ ሳቢያ የነበረውን ሁሉ እንዳለ ጠቅልሎ ልጣል በሚልበት ሰዓት ሊደርስ የሚችለው ኪሳራ እጅግ ከግምት በላይ ነው፡፡ ከስልሳዎቹ እስከ ሰማኒያዎቹ አጋማሽ (1950-1975ዓ.ም.) የነበረው ተማሪውና ተራማጅ ነኝ ይል የነበረው ትውልድ (የደርግ የኢሐፓና ከእነሱ የወጡት የወያኔ ሌሎችም የዚያን ዘመን ፖለቲካ ተዋንያን) በምዕራቡ የሶሻሊዝምና ኮሚኒዝም ርዕዮተ ዓለም ራሳቸውን አጥምቀው የሀገራችንን እሴቶች ከባሕል እስከ ሃይማኖት ከታሪክ እስከ ትምህርት ከወግ እስከ ሥርዓት የነበረውን ሀብታችንን ዋጋ አሳጥተና ጥለው ለገዛ ማንነታቸው ታሪካቸው ቅርሶቻቸው ጠላቶች ሆነው እንደ አዲስ ሀገርና ኅብረተሰብ ከዜሮ ነበር እንድንጀምር ይሟሟቱ የነበሩት፡፡ የእነሱ ጥረትና ፍልስፍና ግን የት እንዳደረሰን ሁሉም በግልጽ የሚያየውና የሚረዳው መረጃ የማያስፈልገው ኪሳራ ነው፡፡
ያ ሁሉ አለፈና ምን አለፈና ይሄው ዛሬስ የሚያዳክረን እሱው አይደል? እሽ ከእኛ ውጭ ባለው ዓለም ግን ዛሬ ሌላው ቀርቶ የዚያ ርዕዮተ ዓለም (Ideology) ቃፊር የነበረችው ሩሲያ እንኳን ተለውጣ ተጸጽታ ያኔ የሰበረቻትን ያደቀቀቻትን አንቅራ ተፍታት የነበረችውን የሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንን ከጣለችባት አንሥታ ክብር በመስጠት ከዚያ ሁሉ ቀውስ በኋላ ዛሬ ላይ የሩሲያ መንግሥት መሪዎች ያለ ፓትርያርኩ ቡራኬ የሚከውኑት መንግሥታዊ በዓላትና ታላላቅ ክንውኖች የሌለበት ሁኔታ ሊታይ ግድ ብሏል፡፡ መሪዎቿም ቤተክርስቲያን ሳሚዎች የሆኑበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡
እንግዲህ ወቅታዊ የዓለም አቀፍ ሁኔታ እንዲህ በሆነበት ሁኔታ ነው “ሞኝና ወረቀት ያሲያዙትን አይለቅም” እንዲሉ የኛዋ ግራ ዘመም ፖለቲከኛ ወ/ሮ ገነት ያኔ ያውም በተሳሳተ ግንዛቤ የጨበጡትን ሙጭጭ አድርገው ይዘው ከስንት ዐሥርት ዓመታት በኋላም በዕድሜ በልምድ በተሞክሮ ብዛት በትምህርትም ሳይለወጡ አሁንም “ግራ ዘመም ስለሆንኩ እንደዚህ ዘንደዚህ ዓይነቱን አልፈልገውም ደሞ የምን ምንትስ ነው እንደ ዛ የድሮው ደጅ አዝማች ቀኝ አዝማች!” እያሉ በዚያ ዘመን ቅኝት ማውራታቸው በጣም ነበር የደነቀኝ፡፡
አንዴ አንድ መድረክ ላይ ዶክተር ዳኛቸው (የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፍልስፍና መምህርና ወያኔ በሀገራችን ላይ ያደረሰባትንና የጋረጠባትን ማኅበራዊ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ቀውስ በተቻለው መጠን ባጋጠመው መድረክ ሁሉ እያጋለጠና እየሞገተ ያለ ምሁር) በኢሕአፓ ዘመን በነበረው ትውልድ ትግል ዙሪያ ላይ የተጻፈን መጽሐፍ በገመገመልን ወቅት ለዚያ ዘመን ትውልድ ያለኝ ግምት ወይም አቋም ከዶክተር ዳኛቸው ጋርም አጨቃጭቆጫል፡፡ ዶክተር ዳኛቸው እንደማንኛውም የዚያ ዘመን ሰው ሁሉ በተለይም እንደ የትግሉ አጋርነቱ ያን ትውልድ እያወደሰ እያሞካሸ መቸም ሊደገም የማይችል ትውልድ እያለ ነበር አቅርቦቱን (ፕረዘንቴሽኑን) ያቀረበው፡፡ በውይይቱ ላይ ሐሳብ አስተያየት እንዲሰጡ ዕድል ከተሰጣቸው ሰዎች አንዱ ነበርኩና ሐሳቤን ስሰጥ “እኔ የዚያ ዘመን ትውልድ ጀግና ምናምን በሚባለው ጉዳይ አልስማማም ስላልነበርኩበት ግን አይደለም ለኔ ጀግና ማለት ሞትን የሚጋፈጥ ሞትን የማይፈራ ማለት ሳይሆን የሚሞትለት ዓላማ ከሀገሩ ከማንነቱ አንጻር ሲታይ ባለው ጠቀሜታ የሚወሰን ነው ለኔ ያትውልድ ስሩን ከሀገሩ ከገዛ ከማንነቱ ነቅሎ አውሮፓ ላይ የተከለ ለገዛ ማንነቱ ሥልጣኔው ጠላት የሆነ ርዕዮተዓለሙም ኢትዮጵያዊ ያልነበረ ነውና በፍጹም ጀግና አልነበረም አባጭ የሚለው ስም ግን ይስማማዋል፡፡ ይሄው የጣለው የተከለብን ጠንቅም እስከዛሬ አልለቀቀንም ወደፊትም ገና ብዙ ያዳክረናል” አልኩ፡፡ አለዛ እኮ እነዮዲት ጉዲትን፣ እነ ግራኝ አሕመድን፣ በድፍረት መግደል ማጥፋት ማውደም የሚችሉበትን ዕድል ለራሳቸው የፈጠሩትን፣ ክፉ የጭካኔ እርኩስ መንፈስ ተጠናውቶት ያለምንም ምክንያት እየተነሣ በድፍረት የሚገለውን ሁሉ እኮ ጀግና ልንል ነው!
ይህ አስተያየቴ ለዶክተር ዳኛቸው በጣም አልተመቸውም ነበር “ያ ትውልድ ጀግና ካልተባለ ማን ሊባል ነው?” አለ “አንተን ደስ እንዲልህ ፈሪ ነው ልበል? ርዕዮተዓለሙ ኢትዮጵያዊ አይደለም ትላለህ መሬት ላራሹ ኢትዮጵያዊ አይደለም? የብሔር ጥያቄ ኢትዮጵያዊ አይደለም?” ሲል ጠየቀኝ መልስ ለመስጠት ዕድሉ እንዲሰጠኝ ጠየኩ አወያዩ አልፈቀደም እናንተ በግል ተወያዩ ያለንን ሰዓት በቀሪ ሐሳቦችና ጥያቄዎች ላይ እናተኩር በማለቱ ቀረ፡፡
በእርግጥ ወ/ሮ ገነት ዛሬ የዚያ ርዕዮተዓለም አፍላቂዎች በተውበት ዘመን የወደቀውን የነጭ ውራጅ አስተሳሰብ በተንጋደደ አረዳድ ጨብጠው ይዘው ዛሬም ማውራታቸው ወ/ሮዋ ለአሁኑ ትውልድ አርአያ የመሆን አቅም ኖሯቸው ይህ ትውልድም ተመሳሳይ ችግር እንዳይፈጥር በመፍራት አይደለም በዚህ ጉዳይ ላይ ትኩረት መስጠቴ፡፡ ነገር ግን የዚያን ዘመን እብደት እንዲገነዘብ እንዲታዘብ እንጅ፡፡ ወ/ሮ ገነት ግራ ዘመም ስለሆንኩ እያሉ በመንቀፍ ሊከተሉት እንደማይሹ ከገለጹት ነባር ባሕል ወግ ሥርዓት አንዱ ለጋብቻ ሽምግልና መላኩን ነው፡፡ ከዓመታት በፊት ይሄንን ጉዳይ አንድ እንደሳቸው ግራ ዘመም ወይም ተራማጅ ነኝ ባይ በሬዲዮ (በነጋሪተ ወግ) በሚተላለፍ ዝግጅት ላይ እየተቸ እንዲቀርም እየመከረ አሳች ሐሳቡን በጽሑፍ አስተላልፎ ስለነበርና ይህ ጉዳይ ዝም ተብሎ የሚታለፍ ስላልሆነብኝ በዚያው ዝግጅት ላይ ሰጥቸው የነበረው ምላሽ ይሄንን ይመስል ነበር፡፡
“ሌላው አቶ ተራማጅ ስለጋብቻ ሽማግሌ የመላክም ባሕል ኋላ ቀር ነው በማለት አጣጥለው ነቅፈዋል፡፡ ኋላቀሩ ባሕሉ ወይስ እርስዎ የሚለውን በአጭሩ እንይ አቶ ተራማጅ ምክንያት አድርገው ያቀረቡት በጣም አስቂኝ ነገር ነው የሆነብኝ፡፡ ምክንያትዎ ምን ነበር? 1ኛው ሽማግሌዎቹ ሄደው የሚያወሩት ነገር አብዛኛው ውሸት ስለሆነ የሚል ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ተጋቢዎቹ መጀመሪያ ተዋውቀው ተፈቃቅደው የጨረሱት ጉዳይ ነው፡፡ የሚለው ደግሞ ሌላኛ ውምክንያታቸው ነው፡፡
አቶ ተራማጅ ታዲያ በምን ሒሳብ ነው መፍትሔው ባሕሉን ማጥፋት ሊሆን የሚችለው? በትዳር ውስጥ የሚማግጡ ሰዎች አሉና ተብሎ ትዳር ይጥፋ ወይም ይቅር ይባላል እንዴ? ይሄስ ከበሰለ ጭንቅላት የፈለቀ በሳል የመፍትሔ ሐሳብ ነው? ነው ወይስ በትዳር ላይ የሚማግጡ ሰዎች እንዳይኖሩ የሚያስችሉ የማኅበራዊ ግንኙነትና አስተዳደር ሥራዎችን መሥራት? የትኛው ነው የበሰለ እና ማስተዋል የታከለበት የመፍት ሔሐሳብ? እንደዚሁም ሁሉ በሽምግልና የሚዋሹ ሰዎች አሉ ተብሎ ሽምግልና ይቅር አይባልም በሽምግልና ውሸት እንዲቀር መሥራት እንጂ፡፡ በዚህ ላይ አሁን ያለው ሽምግልና የሚላክበት ሁኔታ እና ሽምግልናን የፈጠረው የቀደመው ባሕላችን ሁኔታ ይለያያል፡፡ አንዱ ይሄ ነው ለሁለተኛው ምክንያትዎ ደግሞ እንደው እርስዎ ሲያስቡት አይደለም ልጅን ያህል ነገርና መርፌም እንኳ ቢሆን ሳይጠይቁ እና ሳያስፈቅዱ ከሰው ይወስዳሉ ይዋሳሉ እንዴ? ምን ነካዎት አቶ ተራማጅ? ምንም እንኳን ተጋቢዎቹ አስቀድመው የጨረሱት ጉዳይ ቢሆንም የወላጅ ፈቃድ ይሁንታና ቡራኬ እንዴት አያስፈልግም ጃል? ልጅን ያህል ነገር ማንነቱ ላልተነገረዎትና ለማያውቁት ሰው ባለቤት እንደሌለው እቃ ብድግ አድርጎ ሲወስድ ዝም ይሉታል እንዴ? ወይም ደግሞ ከሱቅ ገዝተው እንደሚተኩት እቃ ዝም ብለው ብድግ አድርገው ይሰጡታል እንዴ? ኧረ ከሱቅ የገዙት እቃም ቢሆን እንኳ ለማያውቁት ሰው ዝም ተብሎ ብድግ ተደርጐ አይሰጥም፡፡ አቶ ተራማጅ ለመሆኑ ሴት ልጅ አለዎት እንዴ? ይሄን ሲሉ እሷን አስበዋል? ምን ያህልስ ይሳሱላታል?
ለዚህ ዓይነት ስሕተት የዳረግዎትና ወደፊትም የሚዳርግዎት ምን እንደሆነ ልንገርዎት? እርስዎ ለማንነትዎ ለመለያዎ ያለዎት ግምትና የሚሰጡት ዋጋ ዝቅተኛ ወይም የተበላሸ ነው፡፡ በመሆኑም ይህ የውስጥ የተበላሸ እምነትዎ የሆነ ነገራችንን ለመተቸት ሲያስቡ ትክክለኛ መመዘኛ እንዳይኖርዎ ከባድ ተጽእኖ ያሳድርብዎታል በመሆኑም ነገሩን በትክክል ለመረዳት ከስሩና ከተለያየ አቅጣጫ ማየት እንዳይችሉ ያደርግዎታል፡፡ እናም እናማ ከእንደዚህ ዓይነት ራስን ከባድ ትዝብት ላይ ከሚጥል ስሕተት ላይ ይጥልዎታል ማለት ነዋ፡፡ አቶ ተራማጅ ይህንን መልስ ለመስጠት የሚያስችል ጊዜ አልነበረኝም ተመሳሳይ ዓይነት የተሳሳተ አስተሳሰብ ያላቸው ዜጐች ብዙ በመሆናቸውና የተላለፈውም በፌዲዮ (በነጋሪተወግ) በመሆኑ ሊያሰናክሏቸው የሚችሏቸው ሰዎች ብዛት አሳስቦኝ በእርስዎ ምክንያትነት ማድረግ ያለብኝን አድርጌ በአጭሩ መልስ መስጠት እንዳለብኝ ስለተረዳሁእንጂ፡፡ ወደፊት እንደ ሁኔታው ለሚያቀርቧቸው ተመሳሳይ ጽሑፎች በተቻለኝ መጠን በሆደሰፊነት መልስ ለመስጠት እሞክራለሁ፡፡ ነገር ግን እባክዎትን ለሚተቹት ነገር ጥልቅ የሆነ ምርመራ እና ግንዛቤ ደርዝ ያለው ምክንያታዊነት ይኑርዎት፡፡ በተቻለዎ መጠን ሚዛናዊ ይሁኑ እንደዚህኛው ዓይነት ጽሑፍዎት ግልብ አይሁን እንዲያም ሲል ደግሞ ለማንነትዎ ለመለያዎ ተቆርቋሪነትን ይጨምሩበት በትክክለኛ አተያይ ይሁን እንጂ የሚተች ወይም የሚነቀፍ ነገር ካለብንም ሳይሳቀቁ ይተቹ ይንቀፉ ነገር ግን የሚተቹብን ወይም የሚነቅፉብን ነገር የእኛ እንከን ብቻ ወይም ከሌሎች አንጻር ስንታይ የባስነው እኛ መሆናችንን እርግጠኛ ይሁኑ፡፡ በተረፈ እንደወረደ ስሜታዊነት በተንፀባረቀበት ሁኔታ ጽሑፉን ስለጻፍኩ ወይም መልስ ስለሰጠሁ ይቅርታዎ አይለየኝ” ብየ ነበር የመለስኩት ለወ/ሮ ገነትም ተስማሚ ሆኖ ስላገኘሁት ነው እዚህ ላይ ማንሣቴ፡፡
በጣም የገረመኝ ነገር ቢኖር ሌላው ቀርቶ ወ/ሮ ገነት ግራ አዝማች ቀኝ አዝማች ደጅ አዝማች የማሳሰሉት አገርኛ የጦር መሪዎች ሥያሜዎችን መጥላት ለወ/ሮ ገነት ግራ ዘመምነት ነው፡፡ ጋዜጠኛ ወ/ሮ መዓዛ ውይይታቸውን ሲጀምሩ ወ/ሮ ገነትን በቅርቡ ፒ.ኤች.ዲዎን ሠርተዋልና ዶክተር እያልኩ ልጥራዎት ወይ? ብላ ብትጠይቃቸው ወ/ሮዋ ምን አሉ? ከህክምና ዶክተሮች በቀር ያሉ ባለ ፒ.ኤች.ዲዎች ዶክተር ተብለው መጠራታቸው ትክክል እንዳልሆነ ተናግረው ሲያበቁ “አሁንማ በምህንድስና የመጀመሪያ ዲግሪ ያለው ሁሉ ኢንጂኒየር እየተባለ ይጠራ ጀመር እኮ!” ሲሉ አሸሞሩ ቀጠሉና “እኔ ዶክተር እከሌ ኢንጂነር እከሌ ሲባል እንደድሮው ደጅ አዝማች እከሌ ቀኝ አዝማች እከሌ የተባሉ ነው የሚመስለኝ” በማለት ያልበሰለና አስገራሚ አስተሳሰባቸውን ገለጡልን፡፡ ቆይ እኔን የሚገርመኝ ወ/ሮ ገነት በዛሬው ዘመን ጄኔራል እከሌ ኮሎኔል እከሌ ሲባል ግን ይመችዎታል አይደል? በባዕድ ቃል የሚጠራው የጦር መሪዎች ሥያሜ ሲስማማዎት ሀገርኛው ግን ያቅለሸልሽዎታል ለምን? ግራ ዘመም በመሆንዎ የራሳችንን መጥላት ስላለብዎ ይሆን? ለመሆኑ የዚህችን ሀገር ነጻነት ያለእነዚህ የጦር መሪዎች ለማሰብ ይችላሉ? አዎ በእርግጥ ታሪክ ሠሪው ሰፊው ሕዝብ ነው ነገር ግን ንብ ያለ አውራው ይሰማራል ይዘምታል እንዴ? የትኛው ሕዝብና የት ነው ያለ መሪ ታሪክ የሠራ? ለምንም ጉዳይ ቢሆን ሲያስቡት አመራር ሳይኖር ሕዝብ እንዴት ሊሠማራና ሥራውን ጉዳዩን ሊከውን ይችላል? የጥላቻዎ ምንጭ ምን እንደሆነ ልንገርዎ? ከቅጥረኛነትዎ የተነሣ እውስጥዎ ያለው የጸረ ኢትዮጵያ ስሜትዎ ነው እንዲህ እንዲያስቡ የሚያደርግዎት፡፡
ለዚህም ነው ኢትዮጵያን ለ40 ዓመታት ያህል ወራ አማራን (የነገሥታቱንና የክርስቲያኑን ወገን) ከአክሱምና አካባቢው መንጥራ ባጠፋችው የተቀረውንም እንዲሰደድና እንዲበተን ባደረገችው፣ አብያተመንግሥታቱንና አብያተክርስቲያናቱን በውስጣቸውም የያዙትን ቅርሳቅርሶች አቃጥላ አፈራርሳና አውድማ የሀገሪቱን ሥልጣኔ ሀብትና የሰው ኃይሏን አጥፍታ ሀገሪቱን ለከፋችግር በዳረገችው ከዚህ ክፉ ሥራዋ በስተቀር አንዲት እንኳን መልካም ሥራ የሚጠቀስ ነገር በሌላት የጥፋት ልጅ በዮዲት ጉዲት ሲጠሩ ኩራት የተሰማዎት፡፡ በቀረቡበት መድረክ ሁሉ ዮዲት ጉዲት ስለ መባልዎ በተጠየቁ ቁጥር መልካም ሥራ ሠርታ እንዳለፈች ሁሉ “እሷ እኮ ታሪክ አላት” እያሉ የሌላትን መልካም ገጽታ ለማስያዝ ጥረት የሚያደርጉት፡፡ ለመሆኑ ምንድን ነው ይሄ ታሪኳ? ተብለው ቢጠየቁ ምን ብለው ሊመልሱ ነው? እርስዎ እኮ አያፍሩም “ሀገር ስላቃጠለች” ይሉ ይሆናል፡፡ ሌላ ሊባል የሚችል ነገር የላትማ! አየ ወ/ሮ ገነት፡፡ እንዴ! እንዴ! አንድ ነገር ትውስ አለኝ ይሄ ባለፈው ሰሞን “እኔ ተሰውሬ የነበርኩት ነቢዩ ኤልያስ ነኝ ከብሔረ ሕያዋን መጣሁ” እያለ ስንት የዋሀንን ያጃጃለው አይሑድ “ዮዲት ጉዲት ሀገር አልሚ እንጅ ታሪክ አለ እንደምትሉት ሀገር አጥፊ አይደለችም ስሟን ሲያጠፉ ነው” እያለ እንዲሰብክ ያደረጉት እርስዎ ይሆኑ? መቸም አያደርጉም አይባሉም እኮ ጠረጠርኩ፡፡
እናም ለዚህ ነው በእሷ ስም መጠራትዎት ሊያኮራዎት እንጅ ሊያሸማቅቅዎት ያልቻለው፡፡ ከወያኔም ጋር እንዲያብሩና ከዚህ የጥፋት ጎጠኛ ቡድን ጋር ተሰልፈው ማጥፋትዎ ቅንጣት ሊሰማዎት ያልቻለውና መልካም እንደሠራ ሰው የሚያንቀባርርዎት፡፡ አየ ድንቁርና፡፡ ወ/ሮ መዓዛ “ፕሮፌሰር ዐሥራት ዮዲት ጉዲት ብለው ስም አወጡልዎት” ብላ ስትጠይቅዎት እኔ በዐይነ ሕሊናየ እንዴት እንደሚሆኑ የሣልኩዎት እንደተኮነነች ነፍስ ሽምቅቅ እንደሚሉ አድርጌ ነበር፡፡ ቢሉም ግን ይሄንን የተሰማዎትን መጥፎ ስሜት ደብቀው ምንም እንዳልተሰማዎት አስመስለው የሆነ ነገር ይመልሳሉ ብየ ስጠብቅ እርስዎ ግን እውነተ ጉዲት አስደሳች ነገር እንደሰሙ ሁሉ እየተፍነከነኩና ኩራት እየተሰማዎት “እሷ እኮ ታሪክ ያላት ናት” ብለው ሲመልሱ አሁን እኒህ ሴትዮ ምናቸው ነው የተማረው? ብየ ነበር እራሴን የጠየኩት፡፡
በነገራችን ላይ ፕሮፌሰር ዐሥራት እርስዎን ዮዲት ጉዲት ብለው ስም ሲያወጡልዎት እርስዎ እሽ እያሉ ለምን? እንዴት? ሳይሉ በፍጹም ታዛዥነት ለጥፋት ቡድኑ መጠቀሚያ በመሆን ወያኔ እርስዎን ብዙ ያስጠፋዎታል ብለው በማሰብ እንጅ በራስዎ በጭንቅላትዎ አስበው የመወሰን ሥልጣን ኖሮዎት የሚያደርጉት ነገር ይኖራል ብለው ያንን ከመፍራት እንዳልሆነ ጠንቅቀው የሚያውቁት ይመስለኛል፡፡
ለምሳሌ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የተባረሩት የ41ዱን ዶክተሮችና ፕሮፌሰሮች በእርግጥ የተባረሩት 42 ነበሩ አንደኛው ግን አቶ ማንትስ የተባለው ሳይገባው ከእነሱ ጋር ተቆጥሮ የተባረረና ወዲያውም የወያኔ ቀንደኛ ደጋፊ የሆነ በመሆኑ የእሱ መቀነስ ትክክል ነው፡፡ እናም እነኝህ 41 ዶክተሮችና ፕሮፌሰሮች ሲባረሩ የእርስዎ የግል ውሳኔ ሊሆን እንደማይችል ማንም ሊረዳው የሚችለው ጉዳይ ነው፡፡ የዚህም ማረጋገጫ የሚሆነው እነሱን ካባረሩ በኋላ እነሱ ይሰጧቸው የነበሩትን ኮርሶች እነሱ ባስተማሯቸው በፍሬሽ (ደራሽ) ተመራቂዎች እንዲሸፈኑ መደረጉና ከፊሎቹ ዲፓርትመንቶችም (ክፍል ጥናቶች) ከናካቴው ተዘግተው መቅረታቸው ነው፡፡ ይህ የደነቆረ ፖለቲካዊ ውሳኔ መሆኑን እንጅ አሥተዳደራዊ ውሳኔ መሆኑን አያሳይም፡፡ የሚገርመው ይሄንን ካደረጋቹህ በኋላ የተከተለው ችግር እውነቱ ፈጦ እየታየ የብቃት ማነስ ብላቹህ መናገራቹህ ነው፡፡ ይሄ ምላሻቹህ የእነሱ ጉዳይ በተነሣ ቁጥር የምትሰጡት አሳፋሪ ምክንያት እንደሆነ አውቃለሁ፡፡ ከ12 ዓመታት በፊት በፋና ሬዲዮ የቀጥታ የስልክ ውይይት ላይ ይሄንን ጉዳይ አንስቸ ወያኔን በምወቅስበት ጊዜ አንድ የወያኔ ሹም የሥራ ኃላፊ የመለሰው መልስ አሁን እርስዎ የተናገሩትን ነው፡፡ የብቃት ማነስ የተባውን ክስ ሐሰተኛነት እንዲያጋልጡ አስከትየ ላቀረብኩለት ጥያቄዎች ግን ከመርበትበት በስተቀር ሊያቀርበው የቻለው በልስ አልነበረም፡፡
እርስዎም እንዲህ በይ ተብለው ያኔ የተሰጥዎትን መልስ ሳይረሱ ከስንት ዓመታት በኋላም ያችኑ ሳይጨምሩ ሳይቀንሱ ተፏት፡፡ ሞጋች ጋዜጠኛ ስላላጋጠምዎት ዕድለኛ ነበሩ ሐሰተኛ ምክንያት ሰጥተው ተሳድበውም ለማለፍ ቻሉ፡፡ ከዚህ ውጭ ያለው ምክንያት እውነተኛውና ትክክለኛው በመሆኑ ሰዎቹ እንደዜጋና እንደምሁር በሀገራቸው ጉዳይ ላይ በያገባኛል ስሜት ምሁራዊ አስተዋጽኦ ለማበርከት መጣራቸው ሕገ መንግሥታዊ መብታቸው በመሆኑና በዚህ ምክንያት ሰውን ከሥራ ገበታው ማባረር አንባገነንነታቹህን የሚያጋልጥ ስለሆነ ከመዋሸት ውጭ አማራጭ አልነበራቹህም፡፡ ባይሆን የምትሰጡት ሐሰተኛ ምክንያት በቅጡ (ቴክኒክሊ) ሲታይ ሐሰትነቱ በቀላሉ ሊታወቅ የማይችል ማድረግ ግን ነበረባቹህ፡፡ በነገራችን ላይ ይህች አሁን እርስዎ ያሏት ምክንያት እኮ ተሽራ ተሳስተን ነው በሚል በ1997ዓ.ም. በአቶ መለስ ተቀይሯል አልሰሙም ማለት ነው? ወ/ሮ ገነት እንዲያው ግን ሌላው ሌላውን ይተውትና ደርግን “ምሁራንን እንዲሰደዱ ያደረገ የተማረው ክፍል ጠላት ነው!” እያሉ ለሚከሱና ለሚንገበገቡ ዱላውንም ለቀመሱ ለእርስዎ ለሕሊናዎ ይሄንን የማባረር ውሳኔ እንደምን በጸጋ ሊቀበሉት ቻሉ፡፡ ነው ወይስ ያ ስሜትዎ የውሸት ነበር? አዎ በእርግጥም የውሸት ነው፡፡ ስለ ሰብአዊ መብቶችና ደርግ በዜጎች ላይ ስለፈጸመው ግፍ እንደዚያ በስሜት የሚናገሩት የውሸትና የማስመሰል ነው፡፡ ልጅዎ ምን አድርጎ ሥልጣንዎን መከታ በማድረግ ኃይልዎን አላግባብ በመጠቀም ምን እንዳይደረግ እንዳደረጉ የሚረሱት አይመስለኝም፡፡ ወ/ሮ ገነት እስኪ ለአንድ አፍታ እራስዎን በሰለባ ቤተሰብ ቦታ አድርገው ያን አደጋ ለማሰብ ይሞክሩ? ምን ተሰማዎት? ሲጀመር የሰብአዊና የዜጎች መብት የሚያንገበግበው የሚቆረቁረው የሚሰማው ቅንና ስስ ልብ ቢኖርዎት ኖሮ በምንም ተአምር ወያኔ ሊሆኑና ወያኔነት ሊስማማዎት ባልቻለ ነበር፡፡ በዚህ ላይ ደሞ አማራ ሆነው! አይ ወ/ሮ ገነት አማራ ነኝ ሲሉ ግን ትንሽ አያፍሩም? መቸም ወያኔ ለአማራ ምን አስቦለት ሥልጣን ከያዘ ማግስት ጀምሮ ምን ሥልጣን ከያዘ ገና በረሀ እያለ ጀምሮ ምን አስቦበት እስከአሁንም ምን እያደረገው እንደሆነ በገሀድ በአደባባይ የሚታይ ነገር ነውና ከሆድዎ ሻገር ብሎ ማሰብ የሚችል ጭንቅላት ስለሌለዎት እንጅ ነጋሪ የሚያስፈልግዎ አልነበረም፡፡ እባክዎን አማራ ነኝ አይበሉ እንዳልሆኑ እኔ እነግርዎታለሁ፡፡ ስለዚህ ወ/ሮ ገነት የሚያስብ ጭንቅላት ካለዎት እርስዎ ምንም ሊሉ የሚችሉበት አፍ የለዎትምና ነውረኛ ማንነትዎን እንደታቀፉ ነግቶ ውርደትዎን እስኪከናነቡ ድረስ አርፈው ይቀመጡ እሽ?
እስከአሁን ድረስ እኔ በእርግጠኝነት የድንቁርና ምንጩ ምን እንደሆነ አላውቅም፡፡ በተፈጥሮው ደንቆሮ የሆነ እንደሌለ ግን እርግጠኛ ነኝ፡፡ የድንቁርና ካፋቱ ልክን አለማሳወቁ ሰውን ያለ ፍርሐትና ሐፍረት በድፍረት ማናገሩ ነው፡፡ ወ/ሮ ገነት “የኢትዮጵያ ሴቶች” ብለው አጠቃለው በመጀመል ሀገራችን ኢትዮጵያ ሴቶችን በተመለከተ ተስተካካይ የሌለውን ቀና አስተሳሰብና በሀገራችን ታሪክ ሴቶች ምን ያህል ቦታ እንደነበራቸው ማጤን ይገባቸው እንደነበር መጽሐፍ ለመጻፍ የተነሣ ሰው አይደለም የቡና ወሬ ለሚያወራ ሰው እንኳ የሚዘነጋ ጉዳይ አልነበረም፡፡ ወ/ሮ ገነትን ግን ይሄ ጉዳይ ጨርሶ አላሳሰባቸውም እንዲያው ብቻ አፋቸው እንዳመጣላቸው “ሴቶች በኢትዮጵያ እንደሰው አይቆጠሩም” ሲሉ በውይይታቸውም ያውም አእላፋት እየሰሙ ይሄ የቅጥረኛነት አጀንዳቸው እውነት መስሎ እንዲታሰብላቸው በሀገራችን የሴቶችን ገናናነት የሚመሰክረው ታሪክ የያዘው የሀገራችን ታሪክ ድራሹ እንዲጠፋላቸው እየተመኙ የደደረ ድንቁርናቸውን በሚቀፍ መልኩ ሲያሳዩን ቅንጣት እንኳን አልተሰማቸውም፡፡ ወ/ሮ ገነት እርስዎ እንደሰው ሳይቆጠሩ ኖረው ከሆነ ይሄ ከራስዎ ከግል ማንነትዎ ጋር በተያያዘ የራስዎ ችግር እንጅ የሀገሬና የወገኔ ችግር እንዳልሆነ ላረጋግጥልዎት እወዳለሁ፡፡
ወ/ሮ ገነት ለመሆኑ ሀገራችን ኢትዮጵያ ሴቶች ብቃት እንዳላቸው አውቃ በታሪኳ ከ15 በላይ ሴቶችን ለመጨረሻው የሥልጣን ደረጃ ያበቃች ሀገር እንደሆነች ያውቃሉ? ግራ ዘመም ስለሆንኩ ነባሩን የሀገር ማንነት ባሕል እሴቶችን በሙሉ መጥላት አለብኝ ብለው እያሰቡ እንዴት ብለው ሊያውቁ ይችላሉ? ይሄንን የሀገሬን ስኬት እርስዎን ቀጥረው የራሳቸውን ችግር የእኛ ችግር እንደሆነ አድርገው በእርስዎና በመሰሎችዎ አፍ የሚናገሩት አውሮፓውያን እንኳን አግኝተውት ያውቃሉ? አይደለም 15 አንድ እንኳን አይደለም በጥንት ዘመን አሁን ሠለጠን በሚሉበት ዘመን እንኳን ያሳኩ ሀገራትን ሊጠቅሱልኝ ይችላሉ? እኔ ግራ ዘመም ነኝና ይሄንን ታሪካቹህን መቀበል መመስከር አልችልም ብለው የሚያምኑ ቢሆንም እንኳን ዝም ይባላል እንጅ ታዲያ እንደሌለ አድርገው ያወራሉ እንዴ! ነውር አይደለም? ለነገሩ እርስዎ ነውር የት ያውቁና፡፡
ወ/ሮ እርስዎ እያሉ ያሉት “ሀገራችን ሴቶች ሴት በመሆናቸው ብቻ የሚጠቁባት ሀገር ናት” ነው የሚሉት እኔ ደግሞ ፍጹም ሐሰት ነው እያልኩዎት ነው ያለሁት፡፡ ምክንያቱም ሴቶችን የሚያጠቁ ወይም የሚበድሉ ባሎች ወይም ጓደኞች ወይም ወንድሞችን ስናይ ሴቶቻቸውን የሚያጠቋቸው ሴት ስለሆኑ ወይም ወንድ ስላልሆኑ አይደለምና፡፡ ሴት ስለሆነች ወይም ወንድ ስላልሆነች ብቻ ጥቃት የሚያደርስ ሰው ካለ እስካሁን ሰምቼ ዐይቸም አላውቅም ይኖራል ብዬም አልገምትም አለ ከተባለ ግን ይህ ሰው ጤነኛ ባለመሆኑና ለየት ያለ (Exceptional) በመሆኑ ጉዳዩ መታየት ያለበት በተለየ ሁኔታና ቦታ እንበል ለምሳሌ በአእምሮ ሕሙማን ማዕከላት ዓይነት ቦታ ነው፡፡
ጉዳዩ ወይም ችግሩ ግን ፈጽሞ የማኅበረሰቡ ተደርጎ መታየት የለበትም፡፡ ይህንን ካደረግን ግን ማኅበረሰቡን መስደብና ማዋረዳችን ነው፡፡ በደል የተፈጸመባቸውን ሴቶች የበደል ዓይነቶች ያየን እንደሆነ እነዚያ የተፈጸሙ በደሎች ሁሉም በተመሳሳይ ሁኔታ በወንዶችም ላይ የሚፈጸሙ ናቸውና፡፡ በመሆኑም በደሉ የተፈጸመባት ሴት ያ በደል የተፈጸመባት ሴት በመሆኗ አይደለም ማለት ነው፡፡ ታዲያ ምንድነው? ያልን እንደሆነ በጉልበትና በመሳሰሉት ነገሮች በደል ከሚያደርሰው ሰው ያነሰች ስለሆነች ነዋ! በማነሷም በጉልበት ከእሱ ማነሷን ምቹ ሁኔታ ተጠቅሞ ከእሷ የሚፈልገውን ነገር ለማግኘት ወይም ለመበዝበዝ ነው፡፡ ወንዶች ያላቸውን ጉልበት የሴቶች ሴቶች ያላቸውን የአቅም ውሱንነት ለወንዶች አድርገን ብናስበው ይህ አሁን በሴቶች ላይ እየተፈጸመ ነው ያሉት ችግር ሁሉ የሚታሰብ ባልሆነም ነበር፡፡ በመሆኑም ጉዳዩ የጉልበተኞች እና የአቅመ ውስኖች ጉዳይ እንጂ በፍጹም የጾታ ጉዳይ ወይም ሴት እና ወንድ የመሆን ጉዳይ አይደለም ማለት አይመስልዎትም ወ/ሮ ገነት? በወንዶችም ላይ የሚፈጸመው ይሄው ነውና፡፡ ጉልበተኛው አቅመ ቢሱን ወይም ደከም ያለውን ሲጎዳው ሲያጠቃው ሲበድለው ሲበዘብዘው እንደሚታየው ሁሉ ማለት ነው፡፡ ሕፃናት ወንዶች አንዳንዴም አዋቂ ወንዶች ለመግለጽ የሚቀፍ የጥቃት ሰለባ እየሆኑ ባሉበት ሁኔታ የጥቃት ዓይነቶችን በፆታ ወስነን እንዴት ነው የሴቶች እንደዚህ ልንል የምንችለው? ፆታ የለየ ጥቃት ከሌለስ እንዴት ነው ጥቃትንና ፆታን ልናያይዝ የምንችለው?
በዚህም ምክንያት የሴቶች ምንትስ የሴቶች እንደዚህ አሁንም የሴቶች ቅብርጥስ የሚባሉ ነገሮች ሁሉ ችግሩንና ጉዳዩን በትክክል ማየት መግለጽ መወከል ካለመቻላቸው የተነሣ ሥያሜዎቹ ፈጽሞ አይመቹኝም፡፡ ይሄ እንዲያውም የእናንተ ቁማር ይመስለኛል፡፡ ኅብረተሰቡን በተገቢው መንገድ ማስተዳደር ሲያቅታቹህ ወይም ከማኅበረሰቡ ለሚሰነዘሩ ጥያቄዎች መልስ መስጠት ሲሳናቹህ የማኅበረሰቡን ትኩረት ማስቀየሻ እና ከእናንተ ላይ ዞር ማድረጊያ ለዚያ ማኅበረሰብ እዚያው ባለበት የሚይዝላቹህን ፆታን እና የመሳሰሉትን ርእሰ ጉዳዮች መሠረት ያደረጉ የተለያዩ የቤት ሥራዎችን ሆን ብላቹህ ትፈጥራላቹህ፡፡ ይሄም እንግዲህ ከቤት ሥራዎቹ አንዱ መሆኑ ነው፡፡ ይህን ስል ግን ለተገፉ ወይም ለተጠቁ ሰዎች ጥብቅና አይቆም ይረሱ ይገለሉ ማለቴ እንዳልሆነ መረዳት የሚችል ጭንቅላት ያለው ሰው ሁሉ ይረዳኛል ብዬ እገምታለሁ፡፡ ነገር ግን ዓላማችን የተገፉትን ወይም የተጠቁትን ሰዎች መብት ማስከበር ወይም ማስጠበቅ ከሆነ፤ይሄንንም ለማድረግ አቅምን አይቶ ወይም ገምቶ በአቅም ውስንነት ምክንያት በተወሰኑ የማኅበረሰብ ክፍል ላይ ብቻ አትኩሮ መሥራት ካስፈለገ ወይም ግድ ካለ፤ በተሳሳተ ሚዛን ጾታን መሠረት ባደረገ ሥያሜ በጅምላ የሴቶች መብት በማለት ሳይሆን የተጠቂ ሴቶች ጉዳይ ወይም የተበደሉ የግፉአን ማለትም የተገፉ ሴቶች መብት ተከራካሪ ወይም አስጠባቂ ቢባል ትክክለኛ ሥያሜ ይሆናል ብዬ አምናለሁ፡፡ ምክንያቱም የማይጠቁና ያልተጠቁ ሴቶች አሉና፣ ያልተገፉና የማይገፉ ሴቶች አሉና፣ የተከበሩ እና የሚከበሩ ሴቶች አሉና ለእኛ ለሐበሾች ይሄ ሊነገረንና በዚህ ልንታማ ጨርሶ የሚገባ ጉዳይ አልነበረም፡፡ ከተሞከረም ድፍረት ነው፡፡
ማንም ነጭ ለእኛ ለሐበሾች አፍ አለኝ ብሎ እና ደፍሮ በዚህ ርእሰ ጉዳይ ላይ ሐበሻን እንደ ሐበሻ ሊነቅፍ ወይም ሊኮንን የሚችልበት የሞራል (የቅስም) አቅም ብቃትና ነፃነት ከቶውንም የለውም፡፡ በታሪኩ የሴት መሪ አይቶ ወይም አግኝቶ ወይም አብቅቶ የማያውቅ ድኩም ኅብረተሰብ ከቀዳማዊት ሳባ (ከዛሬ 4380-4370 ለ10 ዓመታት የነገሠች) ጀምሮ እስከ ቀዳማዊት ዘውዲቱ ከ15 በላይ ገናና ብልህ አስተዋይ ብቁ ሴቶችን ያፈራንና ያበቃን ሕዝብ እና ሀገር ሊነቅፍ ሊመክር ሊኮንን ሊተች የሚችልበት ኧረ በየትኛው ሒሳብ ይሆን ወ/ሮ ገነት? እንደ አለመታደል ሆኖ በዚህ ዘመን ካለን ሐበሾች ጥቂት የማንባለው አፈር ያብላንና ለነገሩ በልተናል ከዚህ በላይ አፈር መብላት የት አለና፡፡ ክብራችንን ዋጋችንን (ቫልዩአችንን) ባለማወቅ የዚያ ችግር ባለቤት ወይም ተጠቂ የሆኑ የበርካታ ምዕራባዊያን ሀገሮች ጩኸት ሴቶችን ለመሪነት ማብቃት አይደለም ለሴቶች እንደ ሰው የሰውነት መብት ከሰጡ እንኳን ከአንድ የእድሜ ባለጸጋ እድሜ የማያልፉትን፣ የሴቶችን ሰብአዊ መብቶች ሕገ መንግሥቶቻቸውን ጨምሮ በተጻፉ ሕጎቻቸው ሁሉ በይፋ የደፈለቁትን ኅብረተሰቦች ወይም ሀገሮች ጩኸት የሴቶችና የወንዶች የሚል ልዩነት ሳታደርግ እስከ የመጨረሻው የሥልጣን ደረጃ አብቅታ ባረጋገጠች ሀገር፣ ሴት ልጅ ክብሯን ለመጠበቅ ካልሆነ በቀር ጾታዋን እንደበደል እንደእርግማን በመቁጠር ምንም ዓይነት ገደብ አድርጎ በማያውቅ ኅብረተሰብና ሀገር ኢትዮጵያ ውስጥ በእኛው በሐበሾች አፍ ስንጮኸው ጉዳዩ ምን ያህል አሳዛኝና ልብ የሚሠብር እንደሆነና በዚህ ዘመን ያለነውን ሐበሾች ያለንበትን የሞራል (የንቃተ ወኔ) ዝለት፣ ኪሳራና ዝቅጠት የሚያሳይ ይመስለኛል፡፡
ምንአልባት አንዳንድ የሚታዩ የሚመስሉ ነገሮች ካሉ ወይም ቢኖሩ እነኚህ የድህነት ገጽታችን የፈጠራቸው ሳንኮች የድሀነታችን መገለጫዎች እንጂ በፍጹም እንደ ሐበሻ የባሕላችን አካል ወይም የአስተሳሰባችን ደረጃ ሆነው አይደለም፡፡ አስተዋይ ልቡና ያለው ማንኛውም ሰው ይህንን በሚገባ ይረዳል፡፡ ሀገራችን ለሴቶች ያላት ክብርና ቦታ ተወዳዳሪ የሌለው ነው ይሄንንም አድርገን አሳይተናል፡፡ በሀገራችን እግዚአብሔር እንኳን በወንድ ብቻ አይጠራም በሴትም እንጅ ቅድስት ሥላሴ ተብሎ፡፡ ሀገርም እራሷ የምትጠራው በሴት ስም ነው እናት ሀገር በመባል፡፡ ሌሎች የሚወደዱ ነገሮች ሁሉ በሴት ስም ነው የሚጠሩት፡፡ ከዚህ በላይ የጾታ እኩልነት የት አለ? እስኪ ይሄንን የአስተሳሰብ ጣራ እንደኛ አንድ ሳያጓድል በቋንቋው በባሕሉ በሥልጣኔው የያዘ ሀገርና ሕዝብ ይጥሩልኝ?
ይሄን ይሄን እኮነው ድንቁርና የምልዎት ወ/ሮ ገነት፡፡ የምለው ነገር ሁሉ ይገባዎታል ግን? በእርግጥ ድንቁርና እኮ የሌለበት ሰው የለም ምን ያህል በማን ላይ ይጠናበታል ይገንበታል የሚለው ነው የሚለያየው እንጅ ሁሉም ሰው እኮ ድንቁርና አለበት፡፡ ምን ሰብስቦ አንድ ላይ እንዳጎራቹህ እንጃ እንጅ በወያኔ ቤት ያለው ድንቁርናና የደናቁርት ዓይነትና ብዛትማ ለጉድ ነው!
ድንቁርና አነስተኛም ሊሆን ይችል ይሆናል እንጅ የቀለም ቀንድ የበቃ ምሁር በሚባል ሰውም አይጠፋም፡፡ በትምህርት የሚወገድ የድንቁርና ዓይነት አለ በሌላ በኩል ደግሞ ፕሮፌሰር ተብሎም ፊደል ካልቆጠረ መሐይም በማይሻል መልኩ ድንቁርናውን ትምህርት የማያጠፋለት የሰው ዓይነትም አለ፡፡ የእርስዎ ድንቁርና መገለጫዎችን ልንገርዎት? በካፈርኩ አይመልሰኝ ፈረስ ሽምጥ መጋለብዎት፣ በእልሀቸው እያሉ በጥፋት ላይ ጥፋት በመደረብ ጌቶቸ ለሚሏቸው ምቹ አጋሰስ መሆንዎ፣ ምክንያታዊ አለመሆንዎ፣ ከተኮነንኩ አይቀር በሚል አስተሳሰብ በየትኛውም ቦታ በመቸም ሰዓት ገዢ ለሆኑ እውነቶች ለመገዛት አለመፍቀድዎ ለሞራል (ለቅስም) ድንጋጌዎች ጨርሶ ለመገዛትና ለመዳኘት አለመፍቀድዎና ጭራሽም ዐይንዎን በጨው አጥበው ሰው ምን ይለኛል ሳይሉ እየፈጠሩ እየቀጠፉ እየዋሹ ማውራትዎ ወዘተ. ናቸው፡፡ ያው ወያኔ ሆኖ ሕሊናንና ጭንቅላትን መጠቀም አይቻልም አይደል? እንዴት ብለው ታዲያ ከዚህ የድንቁርና በሽታ ይድናሉ? ያው መቸስ ቢጤ ከቢጤው ጋር አይደል የሚቧደነው? ወያኔ ሊሆኑ የቻሉትስ እንዲህ ዓይነት ሰው በመሆንዎም አይደል? እንጅ አሁን ማን ይሙትና የወያኔ ማንነት ማንን መማረክ ማንን ማታለል ይችላልና ነው ወያኔ የሆኑት? ደርግ የፖለቲካ ተቃዋሚዎቸ ናቸው በሚላቸው ላይ ግድያን ለሁለትና ሦስት ዓመታት የፈጸመውን ግፍ ወያኔ በዚህኛው ላይ ጠላትና መጥፋት ያለበት ብሎ የፈረጀውን ብሔረሰብ ጨምሮበት በከፋ መልኩ በግልጽም በስውርም ለ23 ዓመታት እየፈጸመው ያለውን ግፍ በደል ኢሰብአዊ ድርጊቶች ሳያውቁ ሳይሰሙ ቀርተው አይደለም፡፡ ዛሬ እነሱ እንኳን በሥራቸው አፍረው ሞራልም (ንቃትም) አጥተው እንደ ድሮው ደፍረው ማውራት በተውበት ዘመን ይህ ሥርዓት ለፍትሕና ለዲሞክራሲ ለእኩልነት የቆመ እንደሆነ አድርገው የሚወሸክቱት፡፡
ስለ ትምህርት ሥርዓቱ በሌላ ጽሑፍ እመጣልዎታለሁ ነገር ግን “ላለው የትምህርት ጥራት ማሽቆልቆል ተጠያቂው መምህሩ ነው ፖለቲካዊ በሆነ ምክንያት የትምህርት ሥርዓቱን ስላልተቀበለው” ማለትዎ ያልተቀበለበት ምክንያት ፖለቲካዊ ብቻ አይደለም እንጅ እውነትነት አለው፡፡ እንዲህ ከፊል እውነት መናገርዎም ጥሩ ነው ይበርቱ፡፡ ስለዚህ ወ/ሮ ገነት በሕዝብ ዘንድ ያላቹህን ተቀባይነት በሚገባ ያውቁታል ማለት ነው፡፡ መምህሩ ብቻ አይደለም የማይቀበላቹህ፡፡ መምህሩ ከሌላው ማኅበረሰብ ተነጥሎ ሊጠላቹህ ላይቀበላቹህ የሚችልበት ምክንያት ሊኖር አይችልም፡፡ ምክንያቱም መምህራን የኅብረተሰቡ አንኳር አካል እንጅ ከሌላ ዓለም የመጡ ልዩ ፍጥረቶች አይደሉምና፡፡ ሕዝብ ወዶ መርጦን እያላቹህ የምትወሸክቱት ውሸት መሆኑን ስላረጋገጡልን እናመሰግናለን፡፡ ስለዚህ በሌላ ጊዜ ሕዝብ መርጦን ፖሊሲያችንን (መመሪያዎቻችንን) ወዶልን ነው እያሥተዳደርን ያለነው ብለው ደግመው እንደማይዋሹን ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ አይደል ወ/ሮ ገነት?
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!
http://www.goolgule.com/genet-zewdie-is-it-really-how-it-is/