Saturday, November 30, 2013

ከኢትዮጵያ ዜጎች ጋር በተያያዘ በሳውድ አረቢያ ከፍተኛ የሆነ አደጋ ማንዣበቡን ኢትዮጵያውያን ተናገሩ

ኢሳት ዜና :-በሳውድ አረቢያ የሚታየው ሁኔታ እጅግ አስፈሪ ነው ይላሉ ያነጋገርናቸው ዜጎች። ከ40 ሺ በላይ ኢትዮጵያን በእስር ቤቶች ውስጥ ይገኛሉ። ወደ አገራቸው ለመመለስ የሚፈልጉ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ቀናቸውን ይጠባባቃሉ። የኢትዮጵያ መንግስት በመቶ ሺ የሚቆጠረውን ስደተኛ ለማስተናገድ የመደበው የሰው ሀይል 40 ብቻ ነው። የሳውድ አረቢያ መንግስት ደግሞ በተዘዋዋሪ መንገድ ኢትዮጵያውያን ከአገሪቱ ምድር ተጠራርገው እንዲወጡ እየቀሰቀሰ ነው። ሁኔታው በዚህ ከቀጠለ፣ በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ አደጋ ሊፈጠር ይችላል ብሏል  አንድ ስሙ እንዳይገለጽ የፈለገ ጋዜጠኛ።
በዛሬው እለት በተለያዩ የሳውዲ ከተሞች የተበተነው የኤስ ኤም ኤስ መልዕክት  ህጋዊ ለተባሉትም ሆነ ህገወጥ ለሚባሉት ኢትዮጵያውያን የማስጠንቀቂያ ደወል ነው ይላሉ እኝህ ጋዜጠኛ።
በሞባይል ስልኮች የተበተነው ኤስ ኤም ኤስ ኢትዮጵያውያንን ቀጥራችሁ የምታሰሩ እንዲሁም መኖሪያ ቤት ያከራያችሁ ሁሉ በአስቸኳይ እንድታስወጡ፣ ይህን ባታደርጉ ግን 100 ሺ ረያል ትከፍላለችሁ የሚል እንደሆነ ያነጋገርናቸው ኢትዮጵያውያን ገልጸዋል። ይህን መልእክት ተከትሎ በርካታ ኢትዮጵያውያን ከተከራዩበት ቤት ተባረዋል። 9 ኢትዮጵያውያንን ወደ አስጠጋው ኢትዮጵያዊ በመደወል መታሰቢያ ቀጸላ አነጋግራቸዋለች። እርሱ እንደሚለው መልክቱ መተላለፉን ተከትሎ ጓደኞቹ ከቤታቸው እንዲወጡ ተደርጎ በእርሱ ቤት ተጠልለዋል::
ከቤታቸው ከተባረሩት መካከል አንዱ ከ8 ወራት በፊት አባቱ ቤታቸውን ሸጠው ፣ በኪራይ ቤት እየኖሩ በህጋዊ መንገድ እንደላኩት ይናገራል። አሁን ቤትክን ለቀህ ውጣ ተብሎ ህይወቱ አደጋ ላይ ወድቋል::
የሳውዲ መንግስት በኦፊሴል እንዲህ አይነት መልክት ያስተላልፍ እንደሆነ የጠየቅነው ጋዜጠኛ፣ መንግስት በቀጥታ እንዲህ አያደርግም ነገር ግን እርሱ ባሰማራቸው ሰዎች አማካኝነት መልክቶችን እንደሚሰድ ይታወቃል ብሎአል።
የኢትዮጵያ መንግስት ጠንካራ የዲፕሎማሲ ዘመቻ በማድረግ በመቶሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን ህይወት መታደግ ሲችል በቀን ይህን ያክል ሰው አስመጣሁ በማለት ፕሮፓጋንዳ ይነዛል የሚለው ጋዜጠኛው፣ በሳውዲ የቀረው ኢትዮጵያዊ ወደ አገር ቤት የተመለሰውን በብዙ እጥፍ ይበልጣል ሲል በአገሪቱ ያለውን እውነታ አስረድቷል።
በሌላ በኩል ከሳውድ አረቢያ ወደ የመን የገቡ 3 ሺ ያክል ኢትዮጵያውያን በምግብ እጥረት ተጎሳቁለው እንደሚገኙ እስር ቤት ድረስ በመሄድ ጋዜጠኛ ግሩም ተክለሀይማኖት ጎብኝቷቸዋል።

Thursday, November 28, 2013

ፍትህ የጎደለው ስደት እስከ መቼ!


ከሀና ሰመረ (ኖርዌይ)
hannasemere@yahoo.com


የምንሰማውና የምናየው የኛው ከልክ ያለፈ አሳዛኝ ዜና አላስችል ቢለኝ እንደው ትንሽ የውስጤን ሀዘን እና ብሶቴን
ቢገልፅልኝ ብዬ ብዕሬን አነሳው::

እኔ የምላቹ እንደው የሰው ልጅ እንዲህ እንዴት ከፋ? አምላክ በራሱ አምሳል የፈጠረውን ሰውን የሚያህል ክቡር
ፍጡር ለማጥፋት እንዲህ መሯሯጥ ምን የሚሉት ነው? እኛ ኢትዮጵያኖች ለምን ይሆን እንዲህ በየቦታው
ስቃያችን የበዛው? እውነት ግን የምላችሁ ወገኖቼ አያት ቅድመ አያቶቻችን አገራችንን ከወራሪ ጠላት ጠብቀው
ያስከበሩ እና እንዳስከበሩ ሲነገር የቆየው የጀብዱነት ታሪክ በደመ ነፍስ በሚወዛወዘው በወያኔ ድርጅት ከስር
መሰረቱ ለማፍረስ የታለመ ነው:: ይህንን እኩይ ተግባር በቸልተኝነት መመልከት ከታሪክ አጥፊው ጎራ አብሮ
ከመሰለፍ ተለይቶ አይታይም:: ግን እስከመቼ ብለን የጊዜ ቀጠሮ ይዘን ነው አያቶቻችን ደምና አጥንት ከፍለው
ባስረከቡን ሀገር ላይ ነፃነታችንን ተነፍገን ተራ እየጠበቅን የስደትን መራራ ፅዋ የምንጎነጨው ግን እስከመቼ?
ይህንን ጥያቄዬን ልብ ያለው ለራሱ ይመልስ::

ኢህአዴጋውያንን ሳይሆን በመላው አለም ያሉ ኢትዮጵያውያንን በሙሉ ያሳዘነና ያስቆጣው በሳውዲ አረቢያ
የሚኖሩ ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን ላይ የሚደርሰውን በርካቶችን እስከ ሞት ፤ ሴት እህቶቻችንን እስከ መደፈር
፡ እንዲሁም ወንድሞቻችንን ለከፍተኛ ድብደባ ከዳረገውም በላይ የህወሀት አባላት በሳውዲ አረቢያ ልጅም
ዘመድም ስለሌላቸው ወገኖቻችንን ካሉበት ችግር ለማውጣት የተከፈለ አመርቂ እንቅስቃሴ የለም:: እንዲያውም
በተገላቢጦሽ አረቦቹ በመለስ ዜናዊ ለብዙ ዓመታት በሊዝ የሰጣቸውን መቶ ሺህ ሄክታር የኢትዮጵያውያኑ መሬት
ላይ ህይወታቸውን ላጠፉ ፤ ሰብዓዊ መብታቸውን ለገፈፉ ፡ እንዲሁም ደማቸውን ላፈሰሱት ለሳውዲ አረቢያ
ህዝብ ቀለብ ሩዝ እያመረቱ ነው::

ይህም አልበቃ ብሎ ኢትዮጵያኖች ፍትህን ፍለጋ
በተሰደዱበት ዓለም ሁሉ በሙሉ ነፃነት
የወገኖቻቸውን በደል እልህ በተሞላበት ተቃውሞ
ሲያሰሙ ፤ ህዳር 6 ቀን 2006 ዓ.ም ከጠዋቱ
5:00 ሰዓት በተለምዶ ወሎ ሰፈር ተብሎ
በሚታወቀው አካባቢ ከአይቤክስ ሆቴል
ፊት ለፊት በሚገኘው የሳውዲ አረቢያ ኤምባሲ
ደጃፍ ላይ የተቃውሞ ድምፃቸውን ሊያሰሙ
የተሰበሰቡትን በተወለዱበት እና በገዛ ሃገራቸው
የወገኖቻቸውን ስቃይ እንዳይቃወሙ
በፖሊስ የመባረርና ከፊሉም ለእስር ተዳርጓል::

ግን ማን ይሆን ስደትን ሐሴት አድርጎ ቀዬውን ጥሎ በባዕድ ሀገር የሚንከራተት? ፍትህ ቢጓደልበት፤የብልሹ
አስተዳደር ግፍና የጭቆና ቀንበር ከአቅሙ በላይ ቢሆንበት እንጂ፤ ለዚህ ሁሉ ችግሮች ተጠያቂው ለዜጎቹ
ህልውናና ክብር ግድ የለሽ የሆነው መንግስት ተብዬው ነው:: ለነገሩ ወያኔ ብዙ ትንንሽ አድርጎ ከፋፍሎ የወሰነውን
እኛ ካላፈራረስነው ችግራችንም ማብቂያ አይኖረውም የወያኔም አላማ ግብ ይመታለታል ስለዚህ ወገኖቼ “ህዝብ
መንግስትን ሳይሆን መንግስት ህዝብን” አገልጋይ የሚሆንበትን ስርዓት ለመገንባት እንዲሁም ለዚህ ያበቃንን
ስርዓት ለማስወገድ ድክመታችንን በጋራ መፍታት የትግሉ ቅድመ ሁኔታ መሆን አለበት::

ኧረ ማንን ይሆን እንክርዳዱን ከስንዴው አንጓሎ እንዲያስወግድልን የምንጠብቀው?

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!

http://addisvoice.com/wp-content/uploads/2013/11/Hanni-file-21.pdf

ፍትህ የጎደለው ስደት እስከ መቼ!

http://addisvoice.com/wp-content/uploads/2013/11/Hanni-file-21.pdf

Wednesday, November 27, 2013

ፍትሕና ነፃነት እንፈልጋለን

(በ ለምለም ሀይሌ) 
ባሁኑ ግዜ በሀገራችን ያለውን ሰላማዊ ትግል አስመልክቶ የተለያዩ ነጥቦችን ማንሳት ይቻላል። ከአመት በላይ ያስቆጠረውን የድምጻችን ይሰማ ሰላማዊ ትግል፣ የሰማያዊ ፓርቲ እና የአንድነት ፓርቲ እያደረጉት ያለውን ከፍተኛ የሆነ እንቅስቃሴ ይህ ነው የሚባል አይደለም። በተለይ በ 2009 ዓ ም በወጣው ANTI TERRORISM LAW በታጠረውና ምንም አይነት የመናገር ነጻነት በሌለበት ሀገር ውስጥ ሆነው ራሳቸውን ለአደጋ አጋልጠው በሀገራችን ያለውን የመብት ረገጣ፣የዜጎች ያለአግባብ መፈናቀል ይብቃ በማለት እያደረጉት ያለውን ከፍተኛ ትግል ይህ ነው የሚባል አይደለም። ይህ ነገር ለሌሎች አስተማሪና በተለይ እዚህ ነጻነት ባለበት ሀገር ለምንኖር ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን የበለጠ እንድንሰራና እንድንታገል የሚያደርግ ነው።
የሰማያዊ ፓርቲ በቅርብ ግዜ እያደረገ ያለው ከፍተኛ ትግልና ሰላማዊ ሰልፍ የሚኖረውን የህዝብ ብዛት ስንመለከት፣ ለወጣለት አላማ ምን ያህል ቆርጦ የተነሳ ህዝብ እንዳለ እንረዳለን። ሆኖም ግን በዚህ ትግል ውስጥ የሚደርስባቸው እና እየደረሰባቸው ያለ ከፍተኛ የሆነ ችግር እንዳለ ግልጽ ነው።
በተለያዩ ቦታዎች የቅስቀሳ ስራቸውን እንዳያደርጉ ከመታገድ ጀምሮ እስከ ድብደባና እስር ያሉ ጉዳቶች ይደርስባቸዋል። ያልተፈቀደላችሁ ቦታ ቅስቀሳ አካሂዳችዃል፣ እንዲሁም ያልተፈቀደላችሁ ቦታ ሰላማዊ ሰልፍ ወታችዃል በሚሉ ጥቃቅንና ተልካሻ ምክንያቶች ከሚድያ ሽፋን ውጭ በመሆን በአባላቱ ላይ እየደረሰ ያለውን ድብደባና እስር፣ ይህን ሰላማዊ ትግል ለማስቆም ከተደረጉ ጥረቶች መሀከል ይጠቀሳሉ።
ነገር ግን የትግሉ መሪዎች ይህን ሁሉ በገዢው መንግስት እየደረሰባቸው ያለውን ችግር በመቋቋም የያዙትን አላማ ከግብ ለማድረስ ያላሰለሰ ጥረት እያደረጉ ይገኛሉ። ለ22 አመት በአንድ ጨቋኝ መንግስት ስትመራ ለቆየች ሀገር ትክክለኛና ደሞክራሲያዊ የሆነ አስተዳደር ለማምጣት ከፍተኛ የሆነ መስዋእትነትን ይጠይቃል።


ስለዚህም ይህንን በአለም ያለ የነጻነት ናፋቂ ኢትዮጵያውያን እና በተለይም በሀገር ውስጥ ላለው ከማንም ቀድሞ ጥቃት ለሚደርስበት ወገናችን ከጎን በመሆን ይህን ሰላማዊ ትግል ከዳር ለማድረስ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳንል በጋራ በመሆን በወያኔ መንጋጋ ውስት ወድቃ ያለችውን ሀገራችንን ነጻ እናውጣት።

Monday, November 25, 2013

ግድ የለሹ መንግስት ተብዬው!

ከሀና ሰመረ (ኖርዌይ)
hannasemere@yahoo.com


የምንሰማውና የምናየው የኛው ከልክ ያለፈ አሳዛኝ ዜና አላስችል ቢለኝ እንደው ትንሽ የውስጤን ሀዘን እና ብሶቴን ቢገልፅልኝ ብዬ ብዕሬን አነሳው::

 እኔ የምላቹ እንደው የሰው ልጅ እንዲህ እንዴት ከፋ? አምላክ በራሱ አምሳል የፈጠረውን ሰውን የሚያህል ክቡር ፍጡር ለማጥፋት እንዲህ መሯሯጥ ምን የሚሉት ነው? እኛ ኢትዮጵያኖች ለምን ይሆን እንዲህ በየቦታው ስቃያችን የበዛው? እውነት ግን የምላችሁ ወገኖቼ አያት ቅድመ አያቶቻችን አገራችንን ከወራሪ ጠላት ጠብቀው ያስከበሩ እና እንዳስከበሩ ሲነገር የቆየው የጀብዱነት ታሪክ በደመ ነፍስ በሚወዛወዘው በወያኔ ድርጅት ከስር መሰረቱ ለማፍረስ የታለመ ነው::እ ይህንን እኩይ ተግባር በቸልተኝነት መመልከት ከታሪክ አጥፊው ጎራ አብሮ ከመሰለፍ ተለይቶ አይታይም:: ግን እስከመቼ ብለን የጊዜ ቀጠሮ ይዘን ነው አያቶቻችን ደምና አጥንት ከፍለው ባስረከቡን ሀገር ላይ ነፃነታችንን ተነፍገን ተራ እየጠበቅን የስደትን መራራ ፅዋ የምንጎነጨው ግን እስከመቼ? ይህንን ጥያቄዬን ልብ ያለው ለራሱ ይመልስ::

ኢህአዴጋውያንን ሳይሆን በመላው አለም ያሉ ኢትዮጵያውያንን በሙሉ ያሳዘነና ያስቆጣው በሳውዲ አረቢያ የሚኖሩ ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን ላይ የሚደርሰውን በርካቶችን እስከ ሞት ፤ ሴት እህቶቻችንን እስከ መደፈር ፡ እንዲሁም ወንድሞቻችንን ለከፍተኛ ድብደባ ከዳረገውም በላይ የህወሀት አባላት በሳውዲ አረቢያ ልጅም ዘመድም ስለሌላቸው ወገኖቻችንን ካሉበት ችግር ለማውጣት የተከፈለ አመርቂ እንቅስቃሴ የለም:: እንዲያውም በተገላቢጦሽ አረቦቹ በመለስ ዜናዊ ለ60 ዓመት ሊዝ የሰጣቸውን መቶ ሺህ ሄክታር የኢትዮጵያውያኑ መሬት ላይ ህይወታቸውን ላጠፉ ፤ ሰብዓዊ መብታቸውን ለገፈፉ ፡ እንዲሁም ደማቸውን ላፈሰሱት ለሳውዲ አረቢያ ህዝብ ቀለብ ሩዝ እያመረቱ ነው::

ይህም አልበቃ ብሎ ኢትዮጵያኖች ፍትህን ፍለጋ በተሰደዱበት ዓለም ሁሉ በሙሉ ነፃነት የወገኖቻቸውን በደል እልህ በተሞላበት ተቃውሞ ሲያሰሙ ፤ ህዳር 6 ቀን 2006 ዓ.ም ከጠዋቱ 5:00 ሰዓት በተለምዶ ወሎ ሰፈር ተብሎ በሚታወቀው አካባቢ ከአይቤክስ ሆቴል ፊት ለፊት በሚገኘው የሳውዲ አረቢያ ኤምባሲ ደጃፍ ላይ የተቃውሞ ድምፃቸውን ሊያሰሙ የተሰበሰቡትን በተወለዱበት እና በገዛ ሃገራቸው የወገኖቻቸውን ስቃይ እንዳይቃወሙ በፖሊስ የመባረርና ከፊሉም ለእስር ተዳርጓል::

ግን ማን ይሆን ስደትን ሐሴት አድርጎ ቀዬውን ጥሎ በባዕድ ሀገር የሚንከራተት? ፍትህ ቢጓደልበት፤የብልሹ አስተዳደር ግፍና የጭቆና ቀንበር ከአቅሙ በላይ ቢሆንበት እንጂ፤ ለዚህ ሁሉ ችግሮች ተጠያቂው ለዜጎቹ ህልውናና ክብር ግድ የለሽ የሆነው መንግስት ተብዬው ነው:: ለነገሩ ወያኔ ብዙ ትንንሽ አድርጎ ከፋፍሎ የወሰነውን እኛ ካላፈራረስነው ችግራችንም ማብቂያ አይኖረውም የወያኔም አላማ ግብ ይመታለታል ስለዚህ ወገኖቼ “ህዝብ መንግስትን ሳይሆን መንግስት ህዝብን” አገልጋይ የሚሆንበትን ስርዓት ለመገንባት እንዲሁም ለዚህ ያበቃንን ስርዓት ለማስወገድ ድክመታችንን በጋራ መፍታት የትግሉ ቅድመ ሁኔታ መሆን አለበት::

ኧረ ማንን ይሆን እንክርዳዱን ከስንዴው አንጓሎ እንዲያስወግድልን የምንጠብቀው?


“እኔ ራሴ ስድስት ያበዱ ሴቶችን ይዤ መጥቻለሁ..” ራውዳ ጀማል – ከሳዑዲ ተመላሽ ኢትዮጵያዊት (ቃለ ምልልስ)

በሃገር ቤት እየታተመ የሚወጣው አዲስ አድማስ ጋዜጣ ከሳዑዲ አረቢያ ወደ ሃገራቸው ከተመለሱ ኢትዮጵያውያን ጋር ቃለ ምልልስ አድርጓል። ቃለ ምልልሱ ዘ-ሐበሻ ከዚህ ቀደም ትዘግባቸው የነበሩ የሳዑዲ ሕይወቶችን የሚያጠናክሩ በመሆናቸው ጋዜጠኛ አበባየሁ ገበያው ያደረገችውን ቃለምልልስ ለአንባቢዎቻችን እንደወረደ ይኸው፦
ራውዳ ጀማል ትባላለች፡፡ የሃያ ዓመት ወጣት ናት፡፡ ስለራስዋም ሆነ በሳኡዲ ስላሉ ኢትዮጵያውያን ወቅታዊ ሁኔታ ስታወራ እያለቀሰችና እየተወራጨች ነው፡፡ ለማነጋገር ስቀርባት “ወንድ ከሆናችሁ ጋዜጠኞች ነን፣ የህዝብ አፍ ነን ካላችሁ፤ እዚህ ተቀምጣችሁ፣ “ሁለት ሰው ሞተ” እያላችሁ ከምታቅራሩ ሳኡዲ ሂዱና በየቀኑ ሁለት ሶስት ሰው የሚሞትበትን እልቂት ተመልከቱ፣ “ሰዎቹን ምን እየሰራችሁ ነው?” ብላችሁም ጠይቁልን” አለችኝ። መቅረፀ ድምፄን ሶስት አራት ጊዜ ያስጠፋችኝ ቢሆንም በመጨረሻ ግን ለቃለ ምልልስ ፈቃደኛ ሆነችልኝ፡፡
ስንት ዓመት ቆይተሽ መምጣትሽ ነው?
ከሁለት ዓመት በኋላ ነው የመጣሁት፡፡ እስከ አስረኛ ክፍል የተማርኩት አዲስ አበባ ቢሆንም፤ የኮምቦልቻ ልጅ ነኝ፡፡
እንዴት ነበር የሄድሽው?
በፓስፖርት… በኮንትራት ነበር የሄድኩት … ካላስ! የሰውየው ልጆች ግን “የማይሆን” ፊልም ተመልከቺ እያሉ ያስቸግሩኝ ነበር፡፡ ሲመረኝ ጠፍቼ ወጣሁ፡፡ ከዚያም ከጓደኞቼ ጋር በነፃነት ቤት ተከራይተን እየኖርን፣ በ1800 ሪያል ተቀጥሬ መስራት ጀመርኩኝ፡፡ ቤተሰቤንም ገንዘብ እየላኩ እረዳ ነበር፡፡
ወደ አገርሽ እንዴት ተመለስሽ?
ውጡ ሲባል… ረብሻ ሲነሳ.. ጓደኞቻችን ሲሞቱ.. ሲደፈሩብን.. ‘ድሮም ስደተኛ ክብር የለውም’ ብዬ ተመልሼ መጣሁ..ከሚገሉኝ ከሚያበለሻሹኝ ብዬ እጄን ሰጠሁ፡፡ ብዙ ኢትዮጵውያኖች ችግር ላይ ናቸው.. እባካችሁ ድረሱላቸው፡፡ ብርዱም ፀሃዩም ሲፈራረቅባቸው.. ያሳዝናሉ፡፡ ብዙ ያልመጡ አሉ፤ መምጣት እየፈለጉ፡፡ ስቃይ ላይ ናቸው፡፡ እኔ አሁን አስራ ሶስት ቀን ታስሬ ነው የመጣሁት፡፡ እስቲ ስለ እስሩ ንገሪኝ … ሁለት ቀን ያለ ምግብ ያለ ውሃ ነው የታሰርነው። ከዛ በኋላ ግን ጥሩ ምግብ ሰጥተውናል፣ ጥሩ መኝታም አግኝተናል፡፡ ብዙዎቹ ግን ከእኛ የባሰ ችግር ላይ ናቸው፡፡ መጠለያ ያላገኙ አሉ… ኤምባሲያችንም አይሰማም እንጂ ስንት ጊዜ ደውለን ተናግረናል መሰለሽ፡፡ ግን የሚሰማ የለም፡፡ ከአገራችን ውጡ ካሉ በኋላ ትዕግስት ያጡና መልሰው ይዩዙናል፡፡ በዛን ጊዜ አበሻው፣ ሻንዛ/ጩቤ ይመዛል፡፡ ፖሊስ ራሱን ለማዳን ይተኩሳል። እኔ እንደውም ደህና ነኝ፤ እዛ ላሉት ድረሱላቸው። በምድረ ዱርዬ እየተደፈሩ ነው ያሉት /ለቅሶ/ ስንት ህፃናት አሉ የሚሞቱ፣ የሚታመሙ፡፡ ስንመጣ ደሞ፤ ሻንጣ አትያዙ ተብለን ተመናጭቀን…በጥፊ ተመትተን..መከራችንን በልተናል፡፡
ወንዶችና ሴቶች ለብቻ ነበር የተቀመጣችሁት?
የተቀመጣችሁት አትበይ! የታሰራችሁት በይ፡፡ … የሴት እስር ቤት ለብቻው ነው በሴቶችና በህፃናት ለቅሶ የተሞላ ነው፡፡ እኔ ራሴ ስድስት ያበዱ ሴቶችን ይዤ መጥቻለሁ…/ለቅሶ/
አሁን ቤተሰብ እየጠበቅሽ ነው?
ነበረ ግን ሻንጣዬ ጠፋብኝ፡፡ በርግጥ ጤነኛ ሆኖ መምጣትም ቀላል አይደለም፡፡ እዛ ያሉትን ጥለናቸው ስንመጣ እያለቀስን ነው፡፡ እስር ቤቱ ውስጥ አንድ እርጉዝ ሞታብናለች፡፡ እዛው እስር ቤት እያለን ምጥዋ መጣ፤ ግን የህክምና እርዳታ ባለማግኘትዋ ሞተች፡፡
እስር ቤት ያሉት ምን ያህል ይሆናሉ?
ሰማኒያ ክፍል አለ..በየክፍሉ ስልሳ አምስት ስልሳ አምስት ሰው ነው ያለው፡፡ መካሲመሺ እስር ቤት ይባላል፡፡ የወንድና የሴት እስር ቤት የተራራቀ ነው፡፡ በጣም ረጅም ከመሆኑ የተነሳ በመኪና እንጂ በእግር አይሞከርም፡፡ በአሁኑ ሰዓት በከተማው ያለው እስር ቤት ሞልቶ የመዝናኛና የስብሰባ አዳራሹን ሁሉ እስር
ቤት አድርገውታል፡፡ የተደፈሩት የሞቱት..ሴቶች ብዙ ናቸው፡፡ አንዷን እርጉዝ ለሶስት ሲደፍሯት ሞታለች፡፡
የሌሎች አገር ስደተኞችም እየወጡ ነው ተብሏል…
አዎ፡፡ ኢትዮጵያዊው ከበደሉ ብዛት የተነሳ እየተናነቀው እኮ ነው ግጭቱ የሚከረው፡፡
ሚስቱን እህቱን ከእጁ መንትፈው ሊወስዱበት ሲሉ ነው ጦርነት የሚነሳው፡፡ አበሻ ወንድ እየሞተ ያለው ‹‹ሴቶቻችንን አትንኩብን..›› ስለሚል እኮ ነው፡፡ ኤምባሲው ሊደርስላቸው ይገባል፡፡
source: zehabesha

ኦባንግ – ከዓለምአቀፍ ተቋማት ጋር እየሠራሁ ነው አሉ

የሳዑዲ ልዑል አንጋቾቻቸውን አወደሱ

obang-o-metho-hearing


በሳዑዲ አረቢያ በኢትዮጵያውያን ላይ የደረሰውንና እየደረሰ ያለውን ፈር የለቀቀ አስነዋሪ ግፍ ዓለምአቀፍ ይዘት እንዲኖረው ለማድረግ ከሰብዓዊ መብት ተሟጋች እና ሌሎች ዓለምአቀፋዊ ድርጅቶች ጋር እየሠሩ መሆናቸውን አቶ ኦባንግ ሜቶ በተለይ ለጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ ተናገሩ፡፡ የሳዑዲ ልዑል ሰብዓዊነት የረገፈበትንና በግፍ የተሞላ የወሮበላ ተግባር የሚፈጸምበትን አሰቃቂ ተግባር የሚከናውኑትን አንጋቾች አሞካሹ፡፡
ያለ አንዳች ልዩነት ኢትዮጵያውያን በኅብረት ድምጻቸውን በማሰማት እየተቃወሙት ያለውን ኢሰብዓዊ ተግባር አስመልክቶ በተለያዩ መንገዶች ይፋ ከሆኑት በተጨማሪ ድብቅ መረጃዎች እየተሰበሰቡ መሆናቸውን ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ዋና ዳይሬክተር አስታውቀዋል፡፡ ዳይሬክተሩ አቶ ኦባንግ ሜቶ የጋራ ንቅናቄው ከዓለምአቀፍ የመብት ተቋማት ጋር በቅርበት እየተሰራ ስላለው ዝርዝር ጉዳይ ግን ከሁኔታው ምስጢራዊነት አኳያ ማብራሪያ ከመስጠት ተቆጥበዋል፡፡
“አልዘገዩም” በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱም “አኢጋን ችግር በተከሰተ ቁጥር የሚቋቋምና የሚፈርስ የዕቁብ ይዘት ያለው ድርጅት አይደለም፡፡ ወይም እሣት ሲነሳ ድምጽ እያሰማ እንደሚከንፍ የእሣት አደጋ መኪና የሚመሰል ድርጅት አይደለም” በማለት የጋራ ንቅናቄውን የተጠና አካሄድ በመጠቆም የመለሱት አቶ ኦባንግ ይህ ችግር እንደሚከሰት አስቀድሞ ማስጠንቀቂያ መስጠታቸውን ተናግረዋል፡፡
ችግሩ አስቀድሞ እንደሚከሰት ቢታወቅም ምላሽ የሚሰጥ ብቃት ያለው አካል ባለመኖሩ አንገት የሚያስደፋና ኃፍረት የሚላብስ፤ “አገር አለኝ ወይ?” የሚል ጥያቄ የሚያስነሳ በኢትዮጵያ ታሪክ ተሰምቶና ታይቶ የማይታወቅ ኃፍረት ሊደርስብን ችሏል፡፡ “ይሁን እንጂ” አሉ ኦባንግ “ይህ መራር ዜና ከተሰማበት ሰዓት ጀምሮ የጋራ ንቅናቄው የበኩሉን” ሲያደርግ መቆየቱን አመልክተዋል፡፡
“ከተለያዩ ዓለምአቀፋዊ ተቋማት፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች፣ አግባብ ካላቸው መንግሥታዊ አካላትና በተለያየ ደረጃ ላይ ከሚገኙ የሳዑዲ ባለስልጣናት ጋር ተነጋግረናል” በማለት አቶ ኦባንግ ተናግረዋል፡፡ ለዓብነት ያህልም የሳዑዲ ም/ጠ/ሚ/ር እና የመከላከያ ሚ/ር፣ የውጭ ጉዳይ ሚ/ር፣ የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚ/ር፣ የፍትሕ ሚ/ር እና ሌሎች ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታቸውን የመንግሥት መ/ቤቶችን ጨምሮ በአውሮጳና በሰሜን አሜሪካ የሚገኙትን የሳዑዲ ኤምባሲዎችን እንዲሁም የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ጉዳይ ኮሚሽነርን፣ የአፍሪካ የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ACHPR)፣ ወዘተ ማነጋገራቸውንና በየደረጃውም ምላሽ ማግኘታቸውን አመልክተዋል፡፡
በመላው የመካከለኛው ምስራቅ አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ጉዳይ ዕረፍት የሚሰጥ እንዳልሆነ የጠቆሙት “ጥቁሩ ሰው” ሳዑዲ ካላትና ከምትከተለው “የበርህን ዝጋ ፖሊሲ” አንጻር በአካል በቦታው ላይ ከመገኘት ይልቅ አቅም ካላቸው ዓለምአቀፋዊ አካላት ጋር በአፋጣኝና በቅርበት መሥራቱ ድርጅታቸው የወሰደው አማራጭ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ የሎጂስቲክሱ ጉዳይ መስመር ሲይዝም የጋራ ንቅናቄው ከዚህ በፊት በየአገራቱ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ጉዳይ ሲያስፈጽምበት የነበረውንና በውጤታማነቱ የሚታወቀውን አማራጭ እንደሚተገብር ጨምረው ገልጸዋል፡፡
ኢህአዴግ አገርን እንደሚያስተዳድር ድርጅት በዜጎቹ ላይ እየደረሰ ያለውን አስነዋሪ ተግባር ትኩረት ሰጥቶ አለመመከቱ ተቃውሞ አስነስቷል፡፡ ይህንኑ አስመልክቶ አቶ ኦባንግ ሜቶ “ወገኖቻችንን ድንበር በማሻገርና ኤጀንሲ ከፍተው ወደ አረብ አገራት ሲልኩ የነበሩት ሁሉ ሕግ ፊት ቀርበው ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኙ የተለያዩ ተግባራት” እየተከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
alamudi-ሼክ መሐመድ አላሙዲ የሠራተኛ ኃይል ወደ ሳዑዲ እንዲላክ ከኢህአዴግ ጋር በይፋ ስምምነት ማድረጋቸው የሚታወስ ነው፡፡ ኢንቨስትመንትን በተመለከተ ከሚፈልጉበት ክልል መሬት ለመውሰድ፣ ከሚፈልጉበት ባንክ ኮሪደር ገንዘብ ለመበደር ገደብ የሌላቸውና በሞቀበት ሁሉ ባለመጥፋት በጀት መድበው በሚያስተዳድሯቸው ሚዲያዎች እንዲሁም አንደበታቸውን በሙስና ላሰሯቸው ባለሥልጣናት “ኢትዮጵያዊ ነኝ” እያሉ በተገኙበት ቦታ ሁሉ ለሚዲያ ፍጆታ የሚደሰኩሩትና ግጥም የሚያስደረድሩት ሼክ መሐመድ አላሙዲ፣ “ወገኔ” የሚሉት ሕዝብ በአባታቸው አገር ወሮበሎች ሲያልቅና ሲጨፈጨፍ ዝም ማለታቸው ኢንቨስትመንቶቻቸውን ጥያቄ ውስጥ ከትቷል፡፡
አንዳንዶች እንደሚሉት ይህ አሰቃቂ ድርጊት መስመር ለቅቆ ከመውጣቱ በፊት የሳዑዲ አረቢያ ዜጎችን ከርስ እንዲሞላ በኢትዮጵያ የተቋቋመው ሳዑዲ ስታር ኩባንያ በገንዘብ እጥረት ሊዘጋ እንደሚችል መዘገቡ የሚታወስ ነው፡፡ በወቅቱ ሪፖርተር ባወጣው ዘገባ ሳዑዲ ስታር በኪሣራ ወደ መዘጋት መድረሱ የኩባንያው “ባለቤት የሆኑትን ሼክ ሙሐመድ አል አሙዲንና የሳዑዲ ዓረቢያን ስም የሚያጎድፍ ከመሆኑም ባሻገር፣ ኢትዮጵያ ውስጥ እስኪታክት የተወራለት ይህ ፕሮጀክት መና መቅረቱ ሁለቱን አካላት በሕዝቡ ዘንድ ለከፍተኛ ትችትና ወቀሳ እንደሚያጋልጣቸውም” ጠቁሞ ነበር፡፡
mohammed bin nayef
ልዑል ሞሐመድ ቢን ናይፍ
በአሁኑ ጊዜ “ሕገወጥ ናችሁ” በሚል ሰብዓዊነት የጎደው እርምጃ እየተወሰደባቸው ያለው የበርካታ አገራት ዜጎች በተለይም ኢትዮጵያውያን ላይ የሚፈጸመውን ሰቅጣጭ ተግባር ሕገወጦችን የማባረር “ዘመቻ” በማለት ያቃለሉት የሳዑዲው አገር ውስጥ ሚ/ር ልዑል ሞሐመድ ቢን ናይፍ ወንጀለኛ ሬንጀር ለባሾችን፣ ፖሊሶችንና ወሮበሎቹን ሸባቦች አደፋፍረዋል፡፡ “ዘመቻው ይቀጥላል … በተወሰነ ጊዜ የተገደበ አይደለም” በማለት “እስክንጨርስ እንጨርሳችኋለን” የሚመስል የማፊያ መሪ መሰል መልዕክት ለአንጋቾቻቸው አስተላልፈዋል፡፡
አብዛኛዎቹ ኢትዮጵያውያን በሕጋዊነት የሚኖሩትም ጭምር በሳዑዲ ያለው ሁኔታ አሳሳቢነት ወደፊት ችግር ውስጥ ሊከትታቸው እንደሚችል በመገመት ወደ አገራቸው መመለስ ይፈልጋሉ፡፡ በአሁኑ ወቅት ለከፍተኛ ሰቆቃ የተጋለጡት ኢትዮጵያውያን “ቤት አለን ቤታችን መልሱ” እያሉ የሰቆቃና የድረሱልን ጥሪ በሚያስተላልፉበት ወቅት ሰብዓዊነት የጎደላቸው የኢህአዴግ መሪዎች ይህ ነው የሚባል አፋጣኝ ምላሽ መስጠት አለመቻላቸው “በእርግጥ ኢትዮጵያውያን አገር አላቸው?” ብሎ የሚያስጠይቅ እንደሆነ በርካታዎች የሚጋሩት ነው፡፡
አቶ ኦባንግ በበኩላቸውም የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለአንድ ሳምንት ሥራውን አቋርጦ እንኳን ቢሆን ስደተኞቹን ባፋጣኝ የማመላለስ ተግባር መፈጸም ይገባው ነበር በማለት ቁጭታቸውን ተናግረዋል፡፡ ዜጎች በእንደዚህ ዓይነት ሁኔታ ህይወታቸው እየተቀጠፈ “3ሺህ ዛሬ ገቡ … ድምሩ 10ሺህ ሆኗል …” የሚል የሞላ ጎደለ ቁማር ዓይነት ጨዋታ በትዊተር መጫወት የቴድሮስ አድሃኖምን ዘመነኛነት ሳይሆን ለሰውልጅ ህይወት ያላቸውን ደንታቢስነት የሚያሳይ መሆኑን ሁኔታው ያስቆጣቸው አስተያየት ሰጥተዋል፡፡ አቶ ኦባንግም “ቤቴ መልሱኝ” ብሎ ለሚለምን አንድ ዜጋ የተከፈለው ተከፍሎ ትራንፖርት በማቅረብ ክቡር ህይወትን በአስቸኳይ ለመታደግ አለመቻል ለትውልድ የሚተላለፍ የታሪክ ጠባሳ መሆኑን በአጽዕኖት ተናግረዋል፡፡

Saturday, November 23, 2013

Ethiopian migrants victimised in Saudi Arabia

The recent appalling events in Saudi Arabia have brought thousands of impassioned Ethiopians living inside the country and overseas onto the streets.
ethi.migr.in saudi
Racism and hate running through the streets
In the last 10 days persecution of Ethiopian migrant workers in Saudi Arabia has escalated. Men and women are forced from their homes by mobs of civilians and dragged through the streets of Riyadh and Jeddah. Distressing videos of Ethiopian men being mercilessly beaten, kicked and punched have circulated the Internet and triggered worldwide protests by members of the Ethiopian diaspora as well as outraged civilians in Ethiopia. Women report being raped, many repeatedly, by vigilantes and Saudi police. Ethiopian Satellite Television (ESAT), has received reports of fifty deaths and states that thousands living with or without visas have been detained awaiting repatriation. Imprisoned, many relay experiences of torture and violent beatings.
Earlier this year the Saudi authorities announced plans to purge the kingdom of illegal migrants. In July, King Abdullah extended the deadline for them to “regularize their residency and employment status” [from 3 rd July] to November 4th [HRW]. Obtain the correct visa documentation, or risk arrest, imprisonment and/or repatriation. On 6th November, Inter Press Service (IPS) reports, Saudi police, “rounded up more than 4,000 illegal foreign workers at the start of a nationwide crackdown,“ undertaken in an attempt (the authorities say), to reduce the 12% unemployment rate “creating more jobs for locals”.
Leading up to the “crackdown” many visa-less migrants left the country: nearly a million Bangladeshis, Indians, Filipinos, Nepalis, Pakistanis and Yemenis are estimated to have left the country in the past three months. More than 30,000 Yemenis have reportedly crossed to their home country in the past two weeks,” and around 23,000 Ethiopian men and women have “surrendered to Saudi authorities” [BBC].
Most news sources are funded by corporations and investors. Their goal is to drive people to advertisers while pushing the corporate agenda. NationofChange is a 501(c)3 organization funded almost 100% from its readers–you! Our only accountability is to the public. Click here to make a generous donation.
The police and civilian vigilante gangs are victimizing Ethiopian migrants, residing with and without visas; the “crackdown” has provided the police and certain sectors of the civilian population with an excuse to attack Ethiopians. Press TV reports that “Saudi police killed three Ethiopian migrant workers in the impoverished neighborhood of Manfuhah in the capital, Riyadh, where thousands of African workers, mostly Ethiopians, were waiting for buses to take them to deportation centers.” Hundreds have been arrested and report being tortured: “we are kept in a concentration camp, we do not get enough food and drink, when we defend our sisters from being raped, they beat and kill us,” a migrant named Kedir, told ESAT TV. Women seeking refuge within the Ethiopian consulate tell of being abducted from the building by Saudi men and raped. ESAT, reports that several thousand migrants have been transported by trucks to unknown destinations outside the cities.
Whilst the repatriation of illegal migrants is lawful, the Saudi authorities do not have the right to act violently; beating, torturing and raping vulnerable, frightened people: people, who wish simply to work in order to support their families. The abuse that has overflowed from the homes where domestic workers are employed onto the streets of the capital reflects the wide-ranging abuse suffered by migrant workers of all nationalities in Saudi Arabia and throughout the Gulf States.
Trail of abuse
This explosion of state sponsored violence against Ethiopians highlights the plight of thousands of migrant workers in Saudi Arabia. They tell of physical, sexual and psychological abuse at the hands of employers, agents and family members. The draconian Kafala sponsorship system, (which grants ownership of migrants to their sponsor), together with poor or non-existent labour laws, endemic racism and gender prejudice, creates an environment in which extreme mistreatment has become commonplace in the oil-rich kingdom.
There are over nine million migrant workers in Saudi Arabia, that’s 30% of the population. They come from poor backgrounds in Sri Lanka, the Philippines, Indonesia and Ethiopia and make up “more than half the work force. The country would grind to an embarrassing stand still without their daily toil. “Many suffer multiple abuses and labor exploitation [including withholding of wages, excessive working hours and confinement], sometimes amounting to slavery-like conditions”, Human Rights Watch (HRW) states.
The level of abuse of domestic workers is hard to judge: their isolation combined with total control exerted by employers, together with government indifference, means the vast majority of cases go unreported. Until August this year there was no law covering domestic abuse. Legislation has been passed: however, the authorities, HRW reports “are yet to make clear which agencies will police the new law…without effective mechanisms to punish domestic abuse, this law is merely ink on paper.” All pressure needs to be exerted on the rulers of Saudi Arabia to ensure the law is implemented and enforced so victims of domestic violence feel it is safe to come forward.
Ethiopian governments negligence
Whilst thousands of its nationals are detained, beaten, killed and raped, the Ethiopian government hangs its negligent head in silence in Addis Ababa, does not act to protect or swiftly repatriate their nationals, and criminalises those protesting in Addis Ababa against the Saudi actions.
Although freedom to protest is enshrined within the Ethiopian constitution (a liberal minded, largely ignored document written by the incumbent party), dissent and public demonstrations, if not publicly outlawed, are actively discouraged by the Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF) regime. In response to the brutal treatment meted out by the Saudi police and gangs of vigilantes in Riyadh and Jeddah, outraged civilians in Addis Ababa staged a protest outside the Saudi Embassy, only to be confronted by their own police force, wielding batons and beating demonstrators. Al Jazeera reports that police “arrested dozens of people outside the Saudi embassy [in Addis Ababa] in a crackdown on demonstrators protesting against targeted attacks on Ethiopians in Saudi Arabia.” A senior member of The Blue Party, Getaneh Balcha was one of over 100 people arrested for peacefully protesting.
The government’s justification, rolled out to defend yet another suppressive response to a democratic display, was to assert that the protest “was an illegal demonstration, they had not got a permit from the appropriate office”: petty bureaucraticnonsense, hiding the undemocratic truth that the government does not want public protests of any kind on the streets of its cities: effectively, freedom of assembly is banned in Ethiopia. The protestors, he said, “were fomenting anti-Arab sentiments here among Ethiopians.” Given the brutal treatment of Ethiopians in Saudi Arabia, anger and anti-Saudi sentiment (not anti Arab) is, one would imagine understandable, and should be shared by the Ethiopian government.
The people of Ethiopia are living under a duplicitous highly repressive regime. The EPRDF consistently demonstrates it’s total indifference to the needs and human rights of the people. Freedom of expression, political dissent and public assembly is denied by a regime that is committing a plethora of human rights violations in various parts of the country, atrocities constituting in certain regions crimes against humanity. In fact, according to Genocide Watch, the Ethiopian government is committing genocide in the Somali region, as well as on the “Anuak, Oromo and Omo” ethnic groups (or tribes).
The recent appalling events in Saudi Arabia have brought thousands of impassioned Ethiopians living inside the country and overseas onto the streets. This powerful worldwide action presents a tremendous opportunity for the people to unite, to demand their rights through peaceful demonstrations and to call with one voice for change within their beloved country. The time to act is now, as a wise man has rightly said, “nothing happens by itself, man must act and implement his will”.
Posted by Addisu Wond.
http://www.nationofchange.org/

Overrakte brev til ordføreren

 
...
INTERNASJONAL SOLIDARITET. Lomjta Baheru overrekker ordfører John Opdal et brev som skal sendes til den norske regjeringen. Foto: Ernst Olsen

Overrakte brev til ordføreren

Flyktninger og asylsøkere fra Etiopia og Eritrea overrakte ordfører John Opdal et brev som forteller om den vanskelige situasjonen til landsmenn bosatt i Saudi-Arabia.

 
 

Lørdag 16. november var flyktninger og asylsøkere fra Etiopia og Eritrea samlet i Odda sentrum.
De minnet ofrene etter alle de grufulle overgrepene mot deres landsmenn i Saudi-Arabia den siste tiden.
Dette er en hendelse som i norske medier har havnet litt i skyggen av den tragiske naturkatastrofen på Filipinene.
Onsdag fikk gruppen fra Etiopia og Eritrea presentere sitt budskap for Odda kommunestyre.
Ordfører John Opdal fikk overrakt et brev der det settes fokus på overgrepene mot deres landsmenn i Saudi-Arabia, de skriver også om gjentatte brudd på menneskerettighetene i sitt eget hjemland.
Gruppen av flyktninger, som satt på galleriet, ba ordføreren videresende brevet til den norske regjeringen.
- Vi takker lokalpolitikerne i Odda for at vi fikk slippe til, og håper de vil støtte oss i det videre arbeidet, sa Lomjta Baheru som overrakte brevet.

Saturday, November 16, 2013

Riyadh is Flooding with Rain !…ሪያድ በጎርፍ ተጥለቅልቃለች!!! video


11
This is much more serious than I initially thought. I’m getting images from twitter of users taking photos in Riyadh right now and it looks like the entire city is drowning. Weather experts are saying Kuwait is going to rain heavily for the entire weekday so I can’t imagine how bad it’s going to get.
Here’s a gallery of photos being shared on twitter:
asdfghjkzxl

ይድረስ ለኢትዮጵያ ፖሊሶችና የመከላከያ ሰራዊት አባላት


ዋና ጠላታችን የትግሬ ነፃ አውጪ ወያኔ ነው!

በየቦታው ተበትናችሁ ለአገር የሚበጅ ስራ እየሰራን ነው ለምትሉ የፖሊስና የመከላከያ ሰራዊት አባላት በሙሉ። እንዴት ከርማችሁልኛል? እንደ አገር ልጅ ብናፍቃችሁም እንኳ የናንተ እንጀራና የኔ ኑሮ አልገጥም ብሎ ካጠገባችሁ ከራቅሁ አመታት አልፈዋል። ብዙ ሰዎች የሰው ልብ ያላችሁ፣ አዛኝ አንጀት ያላችሁ መሆናችሁን ይጠራጠሩ ይሆናል። እኔ ግን እንደሱ አላስብም ብዙዎቻችሁ ድህነት በግዱ ገፍትሮ እዚህ ውስጥ እንደ ጨመራችሁ አውቃለሁ። ምክንያቱም ብዙ ጓደኞቼ የሚላስ የሚቀመስ ሲያጡ፣ እንደኔ ለመሰደድ መድፈር ሲያቅታችውና ቢፈልጉም እንኳን ሱዳንና ኬንያ የምታደርስ ገንዘብ በማጣታቸው እንጀራ ብለው የገቡ ብዙ እንዳሉ አውቃለሁ። እነዚህ በሙሉ የድሀ ልጆች ቤት ተቀምጦ በረሀብ ከመሞት የምችለውን አድርጌ እኖራለሁ ብለው እንደሚኖሩ አውቃለሁና በተለይ እናንተ ከዚህ የመከራ ማጥ እንድትወጡልኝ አምላኬን መለመን አልተውኩም። ግምገማ ፈርታችሁ የራሳችሁን ወገን በዱላ መጨፍጨፍ እንዴት እንደሚሰማ አውቀዋለሁ። ባዶ እጁን ያለን ሰውማ በጥይት መግደል የባሰ ነው። በተለይ ያልበላን ሆድ ተርቦ የሚያውቅ ሆድ እንዲህ ያለውን ግፍ በደንብ ያውቃል። ዞሮ ዞር የሚመታውም ሆነ የሚገደለው የናንተ ዘመድ እንኳን ባይሆን አንዱ ቦታ ተመድቦ የሚሰራ የባልደረባችሁ ዘመድ መሆኑ መች ይቀራል።
ጫካ የነበራችሁና ለነፃነት ሲባል የተቀላቀላችሁ ወገኖቼም ብትሆኑ ብዙዎቻችሁ የድሀ ገበሬ ልጆች ናችሁ ወይም ነበራችሁ። ድህነት ጣዕሟን ታውቃላችሁ። ወገናችሁ በሰው አገር እንደ ውሻ ሲቀጠቀጥ ወንጀለኛ ነው ወይም ሕገ ወጦች ናቸው ተብሎ ይበሏቸው የሚል አንጀት ይኖራችሃል ብዬ አላስብም። ከተወለደበት ቀዬ ወደማያውቀው አገር ብን ብሎ የሚሄደው የቸገረው ብቻ ነው። እጅና እግር እያለኝ እናትና አባቴ በረሀብ አይሞቱም ያለ ብቻ ነው። የምታጠባው ጡት ደርቆባት ልጆቿን የምታቀምሰው አጥታ ባሏ እጅና እግር እያለው ስራ አጥቶ ሲንከራተት ያየች ነች ጉዱን እያወቀች አረብ አገር የምትሄደው። አንዳንዶቻችሁ ሲከፋችሁ ምናባቱ ብላችሁ ጫካ እንደገባችሁት ባወጣ ያውጣው ብለው ያሉት የተሰደዱት የናንተው ቢጤ ምስኪኖች፣ ሀገራቸውንና ወገናቸውን የሚወዱ ድሆቹ ናቸው። ለነዚህ መከረኞች አለሁ ማለት ካቃታችሁ የትኛውን አገር ነው የምትጠብቁት? የትኛውን ነፃነት ለማምጣት ነው ጫካስ የገባችሁት? ምነው ታውቁት የለም የሱማሌ ስደተኞችን ተቀብለን አላኖርንም? ከ ኤርትራ የመጡ ስደተኞች ኢትዮጵያ ይኖሩ የለም? አረ ምን ስደተኞች ባለስልጣኖቹስ ቢሆኑ እነማን ሆነው ነው? ደግሞስ ከሀገራችን ይውጡ ካሉ አሳፍሮ መላክ ነው እንጂ እንደ አይጥ መንጋ መጨፍጨፉንስ ምን አመጣው? ምናልባት ጥፋት ስለሰሩ ነው ብለው ነግረዋችሁ ከሆነ ውሸት ነው። ሲብስባቸው የሚደርስላቸው ሲያጡ ባንዲራ ለብሶ መታረድ ቢሰለቻቸው ነው መቆጣት የጀመሩት። እውነት ቢኖራቸው ኖሮ መረጃውን ሁሉ አይከለክሏችሁም ነበር። አይናችሁን ሸፍነው ጆሮአችሁን ደፍነው ከሰውነት ወደ አውሬነት ለመቀየር ስለሚፈልጉ ነው። አረቦቹ ኢትዮጵያውያኑን በስፋት መግደል የጀመሩት የሀገራችሁ መንግስት ውሰዱልን ብንል እምቢ ስላሉ ነው እያሉ ነው።
ወገኖቼ ያለባችሁን ችግር አውቃለሁ ብዙ ብጽፍ ለማንበብም እድል አታገኙ ይሆናል። ግን ትንሽም ቢሆን የተሰማኝን ስሜት ላካፍላችሁ ብዬ ነው። አይምሰላችሁ የናንተን ችግር ሕዝቡም ያውቀዋል። እናንተ የእንጀራ ጉዳይ ሆኖባችሁ እንጂ አንጀታችሁ እርር እንደሚል አውቃለሁ። ከዚያም በላይ ደግሞ ብዙዎቻችሁ እህቶቻችሁ የወንድም የእህቶቻችሁ ልጆች ሁሉ አረብ አገር እንዳሉ አውቃለሁ። አንዳንዶቻችሁ እጮዎቻችሁ ጭምር ትንሽ ገንዘብ ሰርተው ኑሮ ለማሳመር ሲሉ አረብ አገር እንደሄዱባችሁ ሁሉ አውቃለሁ። ያው ነና የኔም ዘመዶች እኔኑ እያስቸገሩ እዚህ ተቀምጠን የማይሆን ነገር ውስጥ ከመግባት ሲሉ ስቅቅ እያልኩ ገንዘብ እልክላቸው ነበር። ካልሆነልን በዝሙት መተዳደር ነው እድላችን ያሉኝም አሉ። እቤት ተቀምጨ ረሀብ በሶስት ቀን ከሚገድለኝ ትንሽ ፋታ የሚሰጠው ኤድስ ይሻላል የሚሉ ሁሉ እንዳሉ አውቃለሁ፣ እናንተም ይህን በደንብ ታውቃላችሁ። ይህን እየሰማ አልጨክን የሚል ሆድ ያለው ግማሹ ገንዘቡን ልኮ ሌላውም ጥሪቱን ሽጦ ወይም ተበድሮ ነወ የላከው። ይህ ወገኑን የአረብ መጫወቻ ሲሆን እንባ አይደለም ለምን ደም አያስለቅስም። እናንተ ከዚህ የባሰ ሀዘን ውስጥ እንደምትሆኑ አውቃለሁ። ለመነጋገር ቀርቶ ለማሰብም እንደምትፈሩ ይገባኛል። ጥርነፋው የሚያወላዳ አይደለም። ግን ከእሳት የሚያወጣ ሀይል ያለው አምላክ አለላችሁ። የወገን ግፍ በቃ በሉ። ስለወገናችሁ መዋረድ ተቆርቆሩ። ይህን ሰርቶ እንጀራ ከመብላት ታግሎ መውደቅ ይመረጣል በእውነት ክፉ እንዲነካችሁ አልፈልግም ነገር ግን በዚህ ከቀጠልን ለናንተም እየፈራሁ ነው።
እናንተ እኮ የሀገር መከላከያ እንጂ የባለስልጣን ዘበኛ አይደላችሁም። ሀገር ስትዋረድ የአስራ አምስትና አስራ ስድስት አመት ልጆች በስድስትና ሰባት ወንድ እየተደፈሩ ደም በደም ሆነው በየሜዳው ሲጣሉ ምን አንጀት ያስጨክናችሁ ይሆን? ወገኖቼ አገራችን ብዙ አምባገነን መንግስታትን አስተናግዳለች። ሰራዊቱና ፖሊስም ለዚህ መሳርያ ሆኖ ያገለገለበት ወቅት ነበር። ነገር ግን የሀገር መከላከያ ሙሉ በሙሉ በጠላት እጅ ወድቆ ለጠላት አድሮ ኢትዮጵያን በዚህ ደረጃ ያዋረደበት ጊዜ ኖሮ አያውቅም። የዚህ የጠላት ጦር አጋር መሆን ወንጀል ነው። ልጆቻችንን አትንኩብን ወንድም እህቶቻችንን አትግደሉብን ብለው ሰልፍ የወጡ ሰዎችን አረቦች ፊት፣ ኤምባሲያቸው ፊት ለፊት በናንተ ዱላ መጨፍጨፍ ወንጀል ነው። ጣልያን ኢትዮጵያን በወረረች ጊዜ ከጣልያን ጎን በመሰለፍ የሀገራቸውን ሕዝብ ያስጨፈጨፉ ጥቂት ባንዳዎች ነበሩ። የአንድ ሀገር ጦር እንዳለ የባንዳ ሰራዊት ሲሆንና ለእለት እንጀራ ሲባል የዚህ ጦር አባል መሆን ጭካኔ ነው አውሬነትም ነው። አውሬም እንኳ የራሱን ዘር መልሶ አይበላም። ለመሆኑ እናንተ ከማን ተፈጠራችሁ?
ይህ ጭካኔያችሁን የተመለከተ ኢትዮጵያዊ የያዛችሁትን ቆመጥ ተቀብለው ሊያደርጓችሁ የሚችለውንስ ታውቁ ይሆን? ወገናችሁን በመጨፍጨፍስ የደም እንጀራ ስትበሉ እንቅልፍስ እንደምን ትተኛላችሁ? ድህነት ክፉ ነው ሆድ ብዙ ያደርጋል ግን አሁን በቃ ልትሉ ይገባል። ልታምጹ እምቢ ለትሉ ይገባል። ጥያቄው የስልጣን አይደለም፣ የሀይማኖት አይደለም፣ የዘር አይደለም የነጻነት ጥያቄ ነው! የክብር ጥያቄ ነው! የ ኢትዮጵያዊነት ጥያቄ ነው።
ከጠላቶቻችን ጋር ተባብራችሁ የሀገራችሁን ሕዝብ ለመጨፍጨፍ ቁርጠኛ ሆናችሁ ከቀጠላችሁ ይሄ ሕዝብ ሊያደርጋችሁ የሚችለውን አስባችሁ ይሆን? ወገኖቼ ይህ ቀን ሳይጨልም እምቢ በሉ። ዘረኞች፣ የአረብ አሽከር ሆነው ሀገራችሁን መሬታችሁን እየሸጡ፣ ሚስት ልጆቻችሁን ለግርድና እየላኩ ሀብት ሲያጠራቅሙ የነሱ ዘበኛ መሆንና የእንደዚህ አይነት ከሀዲዎች አጋር መሆን ጨካኝነት ብቻ ሳይሆን የሀገር ጠላትነት ነው። በታሪክ የሚያስጠይቅ በክህደትም የሚያስጠይቅ ነው። እምቢ የምትሉበት ጊዜ አሁን ነው። በየሜዳው ላይ እየተደፈሩና እየተገደሉ ያሉ ኢትጵያውያን ደም ይፋረዳችኋል። ይህ መረጃ ለሁሉም ሊደርስ የሚገባው ነው ላልሰማው አሰሙ። ይህ የፍረሀት አጥር ይፈርሳል ያኔ የታጠቃችሁት መሳርያ ዋጋም አይኖረውም። ብዙዎች ወገኖቻቸውን ለመቀላቀል መነሳሳትን አሳይተዋልና እናንተም ተነሱ፣ ቁጣችሁን አሳዩ ወገናዊነታችሁን አስመስክሩ! አገራችሁን ኢትዮጵያንና ሕዝባችሁን ታደጉ። የመገናኛ ብዙሃን በድምጽም ቢሆን መልዕክቴን ያደርሱላችሁ ይሆናል አመጽ በልብ ይጠነሰሳል ሁኔታ ሲፈቅድ ደግሞ ይፈነዳልና ልባችሁ ይሸፍት እምቢታችሁን መግለጫ መንገድ አስቡ። ኢትዮጵያ ከዚህ መዐት ተውጣለችና የመፍትሄው አካል ሁኑ። አምላካችሁ የእውነቱን መንገድ ያሳያችሁ።
ወንድማችሁ ዳኛቸው ቢያድግልኝ
biyadegelegne@hotmail.com

Friday, November 15, 2013

TPLF security attacks peaceful protesters at the Saudi Arabia embassy in Addis Ababa, Ethiopia


Today around 5:15 AM Ethiopia local time few protesters were out on the streets and we have witnessed federal police were attacking them. Among them there were old people. What’s even more heart breaking was the Saudi Embassy people were sitting on their roof tops and smiling when the TPLF federal police beat up their own people. The idea of coming together today was not about the current government. It’s about our people who are being brutalized in Saudi Arabia.

ዛሬ ማምሻውን ወያኔ እንደለመደው ያው "ሰልፉ ሌላ አላማ ነበረው!!" ብሎ ይወነጅላል በሽመልስ ከማል አንደበት:: ፖሊስ አሁንም ህዝቡን በማስፈራራት ላይ ነው ::ወሎ ሰፈር በሚገኘው ሳኡድኣረቢያ ኤምባሲ የተቃውሞ ድምጾች ለማሰማት የወጡ ዜጎች በፖሊስ ተደብድበዋል:: በርካቶች ታስረዋል:: ሰልፉም በፖሊስ ቆመጥ እና አላስፈላጊ እርምጃ ተበትኗል::


Image

Image

Image

Image

Image

Image

Image

Image

Thursday, November 14, 2013

መቋጫ ያጠው የወገኖቻችን ስቃይ እና ሞት በሳውዲ አረቢያ ፡አሁንም ቀጥሏል !

ትላንት አመሻሹ ላይ ሪያድ ከተማ በተለምዶ መንፍሃ እየተባለ የሚጠራ አካባቢ በሚገኙ ኢትዮጵያውያን አገርሽቶ በዋለው ተቃውሞ የተጓዳ የሞተ ባይኖርም ኢትዮጵያውያኑ ድምጻቸውን ከፍ አድረገው አንድነን አንድነን … መብታችን ይከበር ….እኛም ሃገር አለን ወዘተ… በሚል መፈክር ታጅበው ብሷታቸውን ሲያሰሙ መዋላቸውን የሚገልጹ የአይን እማኞች የሳውዲ የጸጥታ ሃይሎች ተቃውሞውን ለመብተን በከፈቱት ቶክስ ይሰማ በነብረው የጥይት ድምጽ አካባቢውን ወደ ጦርነት አውድማ ለውጦት ማምሸቱን የገልጻሉ። 
ይህንንም ተከትሎ በ10 ሺህ የሚቆጠሩ አውቶማቲክ የጦር መሳሪያ የታጠቁ ተጨማሪ ልዩ ፈጥኖ ደራሽ፡ ኮማንዶዎች ቦታው በመድረስ ተቃውሞውን መግታት ተችሎል ብለዋል ። እንዚህ ምንጮች ትላንት ተቀስቅሷ በነበረው ሁከት ጥቂት ተሽከርካሪዎች ላይ ጉዳት መደሱን ገልጸዋል። ሰምኑን የሳውዲ አረቢያ መንግስት በውጭ፡ሃገር ነዋሪዎች ላይ ያወጣው ህግ የግዜ ገደብ መጠናቀቁን ተከትሎ የሳውዲ ጸጥታ ሃይሎች በኢትዮጵያውያኑ ላይ እየወስዱ ባሉት የተናጥል እርምጃ አያሌ ወገኖቻችን ወደ ሃገሩ ለመምለስ ከየመኖሪያ ቤቱ ነቅሎ አደባባይ ቢወጣም ወደ ሃገር መግባት የሚያስችሉት ነግሮች በመንግስ በኩል ባለመኖሩ ከእልቂት ተርፈው ወደ እስርቤት የተጓጓዙ ከ 20 ሺህ የሚበልጡ ወገኖቻችን በምግብ ወሃ እና የመጸዳጃ ቦታ እጦት እይተሰቃዩ እንደሚገኙ ተግልጾል።
በአንድ ማጎሪያ 4 ቀናቸውን እንዳስቆጠረ የሚነገርለትን ኢትዮጵያዊ እና ሪያድ መንፍሃ ጅዳ እና መካ እስከነ ልጆቻቸው በየመገዱ ፈሶ ቁም ስቅሉን እያየ ያለውን በመቶሺህ የሚቆጠር ወገን ብሷት ለማድመጥም ሆነ ለማየት የመጣ የመግስት ባለስልጣን አለመኖሩ ተገልጾል። ይህ በዚህ እንዳለ ዛሬ ጅዳ በተለምዶ መስፈላ እይተባለ የሚጠራ አካባቢ በሳውዲ የጸጥታ ሃይሎች እና በኢትዮጵያውያን መሃከል በተነሳ ግጭጥ 76 ሰዎች መቁሰላቸውን የሚገልጹት ምንጮች በዛ ቀውጢ የቶክስ እሩምታ በጥይት ተደብድቦ የተገደለ ኢትዮጵያዊ ሊኖር እንደሚችል ግምታቸውን አስቀምጠዋል።
ተቀማጭነታቸው ሪያድ እና ጃዳ ከተማ በሆኑት በሳውዲ አረቢያ የኢትዮጵያው አምባሳደር እና የቆንስላው ጽ/ቤት ዲፕሎማቶች ላይ ተስፋ የቆረጠው ኢትዮጵያዊ ሰድተኛ እስካሁን በመግስት ወደ ሳውዲ አረቢያ ተጉዘዋል ያለው ለኡካን ቡድን ምንም አይነት የሚጨበጥ፡ነገር ባለምስራታቸው ኢትዮጵያውያኑ ለከፋ አልቂት በመዳረግ ላይ መሆናቸው ታውቋል።ሰሞኑን የውጭ፡ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ ክቡር አምባሳደር ዲናሞ ሙፍቲህ ኢትዮጵያውያኑ በሳውዲ አረቢያ እየተፈጸምባቸው ነው የሚባለው የጅምላ ግፍ እና በደል ይሄን ያህል የሚጋግነን እና ቦታ የሚሰጠው አለመሆኑን መግለጻቸው ይታወሳል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ትላንት ምሽት መንፉአ አካባቢ በተቀሰቀሰው ተቃውሞ ከ 17 በሚበልጥ አውቶብስ ተጭነው የተወሰዱ ቁጥራቸው በውል የማይታወቅ ህጻናት ሴቶች አረጋውያን ጨምሮ አያሌ ወገኖቻችን ከሪያድ የ6 ሰአታት ጉዞ በሃላ ያልታወቀ መድረ በዳ የሆነ አካባቢ እንዲወርዱ መገደዳቸውን እና የኢትዮጵያውያኑ እስካሁን ያሉበት ሁኔታ በውል እንደማይታወቅ ተገልጾል።
Ethiopian Hagere ከጅዳ በዋዲ

ኢትዮዽያዊያን በዋሽንግተን ዲሲ የሳዑዲ አንባሳደር ያስጨነቁበት ቪዲዮ ኮራንባቹ DC


ከምርጫ 97 ወዲህ በዋሽንግተን ዲሲ እንዲህ ያለ ሕዝብ ሰላማዊ ሰልፍ ሲወጣ ይህ የመጀመሪያው ነው። ኢትዮጵያውያኑ በሳዑዲ ኢምባሲ ደጃፍ ባደረጉት ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ሲላቀሱ፤ ብሶታቸውን ሲያሰሙ፤ ወገኖቻቸው መፍትሄ እንዲያገኙ ሲጠይቁ ውለዋል –። በሰልፉ ዙሪያ የሚደርሱንን መረጃዎች ይዘን እስከምንቀርብ ፎቶዎችን ይመልከቱ።

Wednesday, November 13, 2013

የእህታችን አሳዛኝ የቪድዮ መልዕክት ከሳዑዲ አረቢያ/A Very Sad Message from Saudi Arabia [Must Watch]



A Very Sad Message from Saudi Arabia [Must Watch] የእህታችን አሳዛኝ መ

http://www.youtube.com/watch?v=K26vG8MkFbQ

የ 19 አመት ኢትዮጵያዊ በሳውዲ ወረበሎች የመደፈርዋ አሳዛኝ ታሪክ


እንዲሉ ኢትዬጵያኖች እራሳችን የተውነውን መብታችንን ሌሎች እንዲያከብሩልን መፈለጋችን ላም አለኝ በሰማይ አይነት ነው የሆነብን ።የ አገራችን ችግር ምን እንደሆነ ለማወቅ የሚፈልግም እውቀቱ ያአለውም ያለ እስከማይመስል ድረስ የመክራ መአት በዜጐች ላይ እየደረስ ይገኛል።
መንግስት ነኝ ባዩ ቡድን ዜጐች ከሃገራቸው በስራ ሲወጡ የሚያስፈልገውን ደንብ እና ስርዐት ተክትለው መውጣት ሲገባቸው ኤጀንሲ ነን በሚሉ ወሮበሎች ዜጎች ሲሽጡ በግልጽ እየታየ አንድም ሃላፊነት የሚሰማው የአገር ተቆርቆቋሪ ባለስልጣን እንዴት አገራችን አጣች ? እንዴት በንግዱ እና በፓለቲካው መስክ የ እረጅም ግንኙነት የነበራት አገር እና ሕዝቦቿ በኢትዮጵያዊያን ዜጎች ላይ ይሄን አይነት እርምጃ ሊወስዱ ቻሉ ?እነዚህን እና ሌሎች ጥያቂወች ጠይቄ መልስ ለማግኘት በጣም በመጨነቅ ምንም እንደማይጣ ስለተረዳሁ ጥያቄዎቸን አቁሜ ከሳውዲ አካባቢ የስማሁትን እንደወረደ ላካፍላችሁ ወደድሁ ምን አልባት ስተነፍስው ይቀለኝ ይሆናል በማለት ታሪኩን እነሆ፦
በሰሞኑ የዜጎቻችን ለቅሶ ያላሳዘነው እና ያልተቆጨ መችም የለም ይሄ ግን ጨርቅን አስጥሎ ያስኬዳል ነገሩ እንዲህ ነው
አባት፥ጎረምሳ ወንድ ልጅ እናት እና የ 19 አመት ልጅአገረድ ሴት ልጅ አንድ አፓርትመንት ውስጥ እንዳሉ ቤታቸው በ6 የሳውዲ ጎረምሶች በሩ ተሰብሮ አባት ፥እናት እና ጎረምሳ ወንድም እያየ የ 19 አመት ልጅአገረድ ልጃቸው እና እህቱ ለ 6 ስትደፈር እያዩ ምንም ማድረግ አለመቻል እናት ስታነባ ማየት የ ልጃቸውን ደም እና ህመም የ እህቱን ስቃይ እያየ ምንም ማድረግ ያልቻለ ወንድም ይሄን ሁሉ ስቆቃ እየሰማ ዝም ያለ መንግስት የሌሎች አገር መንግስቶች እና መገናኛ ብዙሀኖች ስምተው ጥያቄ ሲጠየቊ ህገ ወጦች ናቸው ብለው የሚመልሱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማየት እና መስማት በ ልጆቹ እና በወገኖቹ ላይ የሚደርሰው መከራ የማያሳስበው ሕዝብ ማየት እረ ሰዎች ምን ነካን እዚች እህታችን እና ቤተሰቧ ጋ የደረሰው የ እኛ እህት ላይ አይደለም የደረሰው እኛ ልጅ ላይ አይደለም የደረሰው እስኪ ሁላችንም እራሳችንን በቦታው ላይ እንዳለን እናስብ እራሱ ዲና ሙፍቲ ተብየውም የ እራሱን ልጅ 6 አረቦች አይኑ እያየ እንደ እንደ እንስሳ ሲደፍሩአት ምን ይሰማዋል;አንገት የተፈጠረው አዙሮ ለማየት ነው::ከዚህ በላይ ለመቀጠል የሞራል ብቃት ስላጣሁ ፍርዱን ለ አገሬ ሰዎች እተዋለሁ።
እግዚአብሄር የኢትዮጵያውያን እንባ ያብስ።
Samuel Ali
SOURCE: freedom4ethiopian

Saturday, November 9, 2013

እነ ጀማነሽ ድብደባ እየተፈፀመብን ነው አሉ

ፕ/ር ይስማውና ሌሎች አባላት ክስ ተመስርቶባቸዋል
“የማህበረ ስላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ” ማህበር አባላት፤ በተናጥል እና በጋራ በምናራምደው እምነት ምክንያት ህገመንግስቱ የሰጠን መብት ተጥሶ ድብደባ፣ ወከባና እንግልት እየተፈፀመብን ነው፤በአባላቶቻችን ላይም ክስ እየተመሰረተ ነው ሲሉ አማረሩ፡፡ አርቲስት ጀማነሽ ሠለሞን አባል የሆነችበት ማህበረ ስላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ “ኤልያስ መጥቷል፣ ሰንበት ቅዳሜ ነው፣ አርማችን ቀስተደመና ነው” የሚሉና መሠል ሃይማኖታዊ ሃሳቦችን የሚያራምድ ሲሆን አባላቱ ሃይማኖታዊ አስተምህሮአቸውን በተለያዩ መንገዶች ለሰዎች ለማስተማር ሲሞክሩ ለህይወታቸው አስጊ የሆኑ ጥቃቶች እየተፈፀሙባቸው እንደሆነና በአቃቤ ህግ ክስ እንደቀረበባቸው ለአዲስ አድማስ ገልፀዋል፡፡ ከአዲስ አበባ 65 ኪ.ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው አሌልቱ ከተማ አቡነ ተክለሃይማኖት ፅላልሽ ገዳም አጥቢያ ነዋሪና የገዳሙ አገልጋይ እንደሆኑ የገለፁት ወ/ሮ ቀለመወርቅ ጀማነህ፤ የማህበረ ስላሴ አባልና አገልጋይ በመሆናቸው ብቻ በቤተሰቦቻቸው ላይ ውክቢያ፣ እንግልትና ድብደባ እንደተፈፀመባቸው ተናግረዋል፡፡
ግለሰቧ እንደሚሉት መስከረም 24 ቀን 2006 ዓ.ም የገዳሙ የሃይማኖት አባቶች፤ ቤተሰቦቻቸውን ሰብስበው “ልጃችሁ ሃይማኖታችንን እያጠፋች ነው” በሚል እንዳነጋገሯቸውና ከዚህ ድርጊት እንድትታቀብ አድርጉ የሚል ማሳሰቢያ እንደተሰጠ ገልፀዋል፡፡ የማህበረ ስላሴ አባላትን ወደ ገዳሙ ለበረከት ሐምሌ 30ቀን 2005 መጋበዛቸውን የሚገልፁት ወ/ሮ ቀለመወርቅ፤ ይህን በመፈፀማቸው “ሃይማኖታችንን የሚያጠፋ ተግባር ፈጽመሻል” ማለት፣ እንደበድብሻለን የሚል ዛቻ እንደደረሰባቸው አስታውሰው፤ ጥቅምት 17 ቀን 2006 ዓ.ም ዛቻው በቤተሰባቸው አባላት ላይ እንደተፈፀመ ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል፡፡
በእለቱ በወላጅ እናታቸው ቤት በተዘጋጀ የመታሰቢያ ዝክር ላይ ተከፍለው ወደመጡበት ሲመለሱ መንገድ ላይ ድብደባ የተፈፀመባቸው የቤተሰባቸው አባላት፤ በአካባቢው ማህበረሰብ እርዳታ እና በፖሊስ ትብብር ወደ ፖሊስ ጣቢያ በመሄድ ክስ ማቅረባቸውንና ጉዳዩም በህግ እየታየ መሆኑን ወ/ሮ ቀለመወርቅ ገልፀዋል፡፡ ከድብደባው ጋር በተያያዘም በድርጊቱ ተሣትፈዋል ተብለው የተጠረጠሩ የሃይማኖት አባቶችም ታስረው መለቀቃቸውን እኚሁ ቅሬታ አቅራቢ አክለው ተናግረዋል፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ የገዳሙን የስራ ሃላፊዎች በስልክ ለማነጋገር ያደረግነው ተደጋጋሚ ሙከራ ባይሳካም ጉዳዩን የያዙት የወረዳው ፖሊስ ባልደረባ አቶ ገዙ ወርቁ፤ የተፈፀመው ድርጊት ገና በምርመራ ሂደት ላይ መሆኑን ገልፀውልናል፡፡ የማህበሩ አመራር አባላት ለዝግጅት ክፍላችን ባቀረቡዋቸው የክስ ዝርዝር ሰነዶች እንደተመለከተው፤ ከማህበሩ አመራሮች አንዱ የሆኑት ፕሮፌሰር ይስማቸው አለሙን ጨምሮ በባህርዳር እና በደብረ ብርሃን የሚገኙ አባላቶች አስተምህሮውን በመስበካቸው የወንጀል አንቀጽ ተጠቅሶባቸው ክስ እንደተመሠረተባቸው ተመልክቷል፡፡
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህር በሆኑት ፕ/ር ይስማው ላይ የተመሠረተባቸው ክስ እንደሚያስረዳው፤ ተከሳሹ በ28/07/2005 ዓ.ም ከሌሊቱ 10.00 ሰዓት በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01 ክልል፤ ልዩ ቦታው ቦሌ ሚካኤል ቤተክርስትያን ውስጥ የቅዳሴ ስነ ሥርዓት እየተካሄደ እያለ ወደ ቤተመቅደስ በመግባት “ኤልያስ መጥቷል የተዋህዶን ነገር በደንብ መናገር አለብኝ፤ እናንተ በከንቱ ነው የምትደክሙት፤ ኦርቶዶክስ ትክክለኛ ሃይማኖት አይደለም፤ በውስጡ ቅባትና ዘጠኝ መለኮት የሚገለጽበት ነው፡፡
እውነተኛ እና ትክክለኛ ሃይማኖት ተዋህዶ ብቻ ነው፤ ይሄንን እውነታ ለህብረተሰቡ አስተምራለሁ እሰብካለሁ” በማለት ሃይማኖታዊ ስነሥርዓቱ እንዲታወክ እና ረብሻ እንዲፈጠር ያደረገ በመሆኑ፤ በፈፀመው ሃይማኖታዊ ሠላምና ስሜት መንካት ወንጀል ተከሷል ይላል፡፡ በባህርዳር ዙሪያ ወረዳ ጽ/ቤት በአቃቤ ህግ ክስ የተመሠረተባቸው አቶ ጌጤ ሣህሉ ንጋት የተባሉ የማህበሩ አባል በቤተክርስቲያን ላይ የንግግር ወንጀል ፈጽመዋል የሚል ክስ የቀረበባቸው ሲሆን በደብረ ብርሃን ለባሶና ወራና ወረዳ ፍ/ቤትም አቶ አበበ ነጋሽ የተባሉ ግለሰብ፤ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖትን በማሽሟጠጥና በማራከስ እንዲሁም የተለያዩ በራሪ ወረቀቶችን በመበተን ፈፀሙ በተባሉት ሃይማኖታዊ ሠላምና ስሜት መንካት ወንጀል መከሰሳቸው ታውቋል፡፡

Friday, November 8, 2013

የኢትዮጵያዉያን ስቃይና መከራ በሳዉዲ አረቢያ

(በሳዲቅ አህመድ)

የመጣኸዉ ባዶህን ነው! ባዶ ሆነህም ትመለሳለህ!…ኢንተ-ጃኢ-ፋዲ ወተርጃእ-ፋዲ…የሳዉዲዎች አመለካከት!
የፈለጋቹበት ዉሰዱን ግን አትደብድቡን…ይላል ኢትዮጵያዊዉ…ለካስ አትደብድቡን ማለቱ የሚያስደበድብ ነበር…
አይደለም የሰዉ ልጅ እንስሳ እንኳ እንደዚህ አይደረግም። የምታዩአቸዉ ኢትዮጵያዉያን ስደተኞች በሳዉዲ ዜጎች ተይዘዉ ወደ ጀዋዛት (የስደተኛ መምሪያ) ሲወሰዱ ነዉ። እነዚህን ደሃና ከርታታ ኢትዮጵያዉያን በቁጥጥር ስር ያዋለዉ ያገሪቱ ፖሊስ ሳይሆን ያገሪቱ ዜጎች ናቸዉ።”እክስር የዱ!…እጁን ስበረዉ!…” ይላል አንዱ። ከታች ሆኖ የጣር ድምጽን የሚያሰማዉ ኢትዮጵያዊ “ሐላሊ…ሐላሊ… ላቤን ያፈሰስኩበት የልፋቴ ዋጋስ? በማለት ሲጠይቅ ዱላዉ ይጠነክርበታል።
ሰዉ የመሆን ማእረግን የተነፈገዉ ሌላኛዉ ኢትዮጵያዊ ደግሞ ዱላዉን እርግጫዉን እየዋጠ ስቃዩን ለመቀነስ “ኻላስ-አነ-ገልጣን…በቃ! በቃ! እኔ-ነኝ-ጥፋተኛ” ይላል። ከሳዉዲ ዜጎች አንደኛዉ ኢትዮጵያዉያኑ በመያዛቸዉ ባይከፋም ዱላዉን እንዲህ እያለ ይቃወማል “ተራ ኤይብ-መጅሙዓ-ተድርቡነ?… ይህ ነዉር ነዉ በህብረት ትደባደባላችሁ?” ግን ማን ሊሰማዉ። የኢትዮጵያዉያኑን የሰራ-አካል ማሰቃየት ብቻ ሳይሆን የሚያራግፉባቸዉም የቃላት ናዳ ስነልቦናን ይሰብራል።The Misery of Ethiopians in Saudi Arabia
አገር ዉስጥ ካለዉ ስቃይ ለመዳንና የተሻለን ህይወት ለራስም ለቤተስብም ለማምጣት የሚሰደዱት ኢትዮጵያዉን የሚደርስባችዉ መከራና እንግልት ተቆጥሮ አያበቃም። የሳዉዲ መንግስት የመኖሪያ ፈቃድ (ኢቃማ) የሌላቸዉ ወይም ከአሰሪያችዉ ጋር የማይሰሩ (ከፊል) በመጡበት የስራ ዓይነት (ሚህና) የማይሰሩት ከአገር እንዲወጡ ወይም የመኖሪያ ፈቃዳቸዉን እንዲያስተካክሉ የሰጠዉ ግዜ ስላበቃ ሰዎችን በዜግነት በሐማኖት ሳይለዩ ማፈሱን ተያዘዉታል። ባንጻሩ እነዚህ ሰደተኞችን ወደ ሳዉዲ በማስገባት ህገወጥ ተግባር የሚፈጽሙን የሳዉዲ ዜጎች መንግስቱ ወጥ የሆነ እርምጃ ሲወስድባቸዉ አይስተዋልም። ስለዚህ የሳዉዲ ዜጎችም ይሁኑ መንግስቱ ተጠያቂ ከመሆን አይድኑም።
ሰዎች ወደ ሳዉዲ እንዴት ይገባሉ የሚለዉን ስንቃኝ…
1) በሐሃጅና በኡምራ(ጸሎት)
ሰዎች ከተለያዩ አገራት ጸሎት እናደርጋለን በማለት ወደ ሳዉዲ ከደረሱ በሗላ እዚያዉ ይቀራሉ። እነዚህን ሰዎች ቀጥሮ በማሰራትም ይሁን ከቦታ ቦታ በድብቅ በማመላለስ ህገወጥ ተግባር ላይ የሚሰማሩት የሳዉዲ ዜጎች ናቸዉ። በነዚህ የሳዉዲ ዜጎች ላይ መንግስቱ በቂ የሆነ እርምጃ አይወስድም፤ የርምጃዉ ሰለባ የሚሆኑት ስደተኞቹ ብቻ በመሆናቸዉ መንግስቱ ተጠያቂ ነዉ።
2) የኮንትራት ስራ (ጠለብ)
በኮንትራት የሚመጡት ሰራተኞች ከዘመናዊ ባርነት ባልተናነሰ መልኩ ከፍተኛ ስቃይ ይደርስባቸዋል። ረጅም ሰዓታትን መስራት ብቻ  ሳይሆን ከኮንትራቱ ዉል ዉጪ ለዘመድና ለጎረቤት በተጨማሪ እንዲሰሩ የሚገደዱ አሉ። የጠለብ (የኮንትራት) ሰራተኞች ድብደባ፣ግርፋት፣አስገድዶ መድፈር (rape)ወዘተ ይደርስባቸዋል፤ በዚህም ሳቢያ ከአሰሪያቸዉ በመጥፋት በግል ተቀጥረዉ መስራት ይጀምራሉ።የሳዉዲ መንግስት ዜጎቹ የሰራተኛን መብት እንዲያከብሩ በቂ ግንዛቤን ባለመፍጠሩና  ይሕንን መስል ኢሰብዓዊ ድርጊት የሚፍጽሙትን ዜጎች ሕግ ፊት በተገቢዉ መልኩ ባለማቅረቡ ተባባሪ ያስመስለዋልና ተጠያቂ ነዉ።
2) በባህርና ድንበር አቋርጦ መግባት
የሳዉዲ ጎረቤት ከሆነችዉ የመን በኩል ብዙ ስደተኞች ወደ ሳዉዲ ይገባሉ። በተለይም ጀዛን የሚባለዉ የሳውዲ ግዛት ቀድም ሲል የየመን የነበረ ሲሆን ድንበሩን አንድ አይነት ጎሳዎች ብቻ ሳይሆን ቤተሰቦችም ይጋሩታል፤ በሁለቱም አገራት ያሉ የህግ አስከባሪ አካለት የሚዛመዱበት አጋጣሚ ብዙ ነዉ። በተቀነባበረ የኮንትሮባንድ ስራ ፖሊሶችና ድንበር ጠባቂ ሐይላት ሰዎችን በህገወጥ መንገድ በማስገባት ይተባበራሉ። የሳዉዲ መንግስት በድንበሩ ላይ ባሉ የህግ አስከባሪ ሐይላት ላይ በቂ ቁጥጥር ባለማድረጉ ተጠያቂ ነዉ።
ስደተኞች ወደ ሳዉዲ ሲገቡ የአገሪቱን ግዛቶች አቋርጠዉ ከቦታ ቦታ እንዲዘዋወሩ የኮንትሮባንድን ስራ የሚሰሩት የሳዉዲ ዜጎች ናቸዉ። ለምሳሌ አንድ ስደተኛ ከየመን ድንበር-ጀዛን ወደ ሪያድ ወይም ወደ ጂዳ መግባት ቢፈልግ በጭነት መኪና ከእቃ ጋር ተደብቆ እንዲገባ ይደረጋል፤ካልያም ወንዱ እንደሴት ቀሚስ-ሻሽ-የፊት መሸፈኛ እንዲለብስ ይደረግና የሳዉዲ ዜጎች እንደ ሚስት ወይም ልጆች ጭኖ በኮንትሮባንድ ሰዎችን ከቦታ ቦታ ያመላልሳሉ። በዚህ የኮንትሮባንድ ተግባር ፖሊስ (ሹርጣ) ተባባሪ የሚሆንበት አጋጣሚ ብዙ ነዉ። ለዚህ ህገ ወጥ ተግባር ከሳዉዲ መንግስት ሌላ ማንም ተጠያቂ ሊሆን አይችልም።
ወደ ሳዉዲ ለምግባት ኢቃማ (የመኖሪያ ፈቃድ) በዉድ ገዝተዉ የሚገቡ ስደተኞች አንዳንዴ የውሸት አሰሪያቸዉ (ከፊል) ጠፍቶባቸዉ የመኖሪያ ፍቃድ ለማዉጣት የሚቸገሩበት አጋጣሚ አለ። አንዳንዴም የመኖሪያ ፍቃዱን ቢያገኙም ፈቃዳቸዉ ሲቃጠል ለማደስ (ተጅዲድ) አሰሪያቸዉ ጠፍቶ ወይም ፍቃደኛ ሳይሆን ይቀርና ሳይወዱ በግድ ህገወጥ ይሆናሉ። ለዚህ ህገወጥና የተዝረከረከ አሰራር ከሳዉዲ መንግስት ሌላ ማን ተጠያቂ ሊሆን ይችላል?
በሳዉዲ ከተሞች ዉስጥ በስፋት ያሉት ጉዳይ ማስፈጸሚያ ቢሮዎች (መክተበል ሙአቂብ) የመኖሪያ ፍቃድን በተመለከተ የተለያዩ የማጭበርበር ስራዎች (ተዝዊር) በመስራት ይታወቃሉ። እነዚህን ጉዳይ ማስፈጸሚያ ቢሮ ከፍቶ ለመስራት የሳዉዲ ዜጋ መሆኑ ግዴታ ነዉ። በነዚህ ቢሮዎች የዉሸት የመኖሪያ ፍቃድን ከማዘጋጀት ጀምሮ፤ስደተኞች ያለ አሰሪያቸዉ (የዉሸት አሰሪም ቢሆን) ፍቃድ ከአገር ወጥተዉ እንዲመለሱ (ኹርጀል አዉዳ) እስክማድረግ ይሰራል። በነዚህ ቢሮዎች ዉስጥ ሌላዉ ቀርቶ ከስራ ሰዓት ዉጪ ከኢምግሬሽን (ጀዋዛት) በመመላለስ ባዶ ኢቃማ የመኖሪያ ፈቃድ በማምጣት የዉሸት የምኖሪያ ፍቃድ የሚሰጡ የመንግስት ሰራተኞች በርካታ (ነበሩ)ናቸዉ። በዉሸት ከአንድ አሰሪ ወደ ሌላ አሰሪ (ተናዙል-ነቅለል-ከፋላ) በማድረግም የሳዉዲ ህግ አስከባሪ አካላት በመተባበር ህገወጥነትን ያስፋፋሉ። ለዚህ ሁሉ ምስቅልቅል ተጠያቂዉ ዛሬ በየመንገዱ እንደ እንስሳ እየታደኑ ኢሰብዓዊ ተግባር የሚፈጽምባቸዉ ስደተኞች ሳይሆኑ የሳዉዲ መንግስት ነዉ። ከሳዉዲ መንግስትም ባሻገር አገሪቷን የተቆጣጠሩት የንጉስ አብድልአዚዝ ቤተሰቦች ያንበሳዉን ደርሻ ይይዛሉ።
በሳዉዲ ዉስጥ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን በተለያየ የሙያ ዘርፍ የተሰማሩ ሲሆኑ በትክክለኛዉ መንገድ ሰርትዉ የከበሩ፤ላገር፣ለቤተሰብ፣ለወገን የተረፉ በርካታ ናቸዉ። ባንጻሩም እንደ ወጡ የቀሩ፤ ጤነኛ ሆነዉ ታመዉ የተመለሱም ይኖራሉ። በህገወጥ መንገድ አረቄና አስካሪ መጠጥን በመጥመቅ ብሎም በዝሙት የሚተዳደሩም ይኖራሉ። በሺዎች የሚቆጠሩ እዚያዉ-ሳዉዲ የተወለዱ ኢትዮጵያዉያን ህጻናት ሲኖሩ በአገሪቱ ደንብ መሰረት ሁለተኛ ደረጃን ከጨረሱ በሗላ የኮሌጅ ትምርት የማግኘት እድላቸዉ የመነመነ ነዉ (አይቻልም ማለት ይቻላል)። አቅም ያለዉ ልጆቹን ወደ አዉሮፓ እና አሜሪካ ለከፍተኛ ትምርት ሲልክ ዉስን አቅም ያለዉ ልጆቹን ወደ ኢትዮጵያ ልኮ በተለያዩ ኮሌጆች ያስተምራል። ሁለቱንም ማረግ ያልችለ ልጆቹ ያለትምርት የሚባክኑበት አጋጣሚ ሰፊ ነዉ።የባህረ ሰላጤዉን ስደት አስመልክቶ ብዙ ግዜ የሚነገረዉ ለአቅመ አዳምና ሔዋን ለደረሱት ኢትዮጵያዉያን ሲሆን በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ የወደፊት እጣ ፈንታቸዉን የማያዉቁ ሕጻናት ስለተዘነጉ ለነርሱም ማሰቡ ታላቅ ሰብዓዊ ግዴታ ነዉ።
በዚህ መከራና ስቃያ ዉስጥ ላሉ ኢትዮጵያዉን ለመታደግ ለዜጎቹ የሚቆረቆር ሁነኛ መንግስት ቢያሻም ሪያድ ያለዉ የሳዉዲ ኤምባሲና ጅዳ ያለዉ የቆንስላ ጽ/ቤት በመጣመር ዜጎችን የሚበድሉ ቢሆኑ እንጂ ለዜጎች ደራሽ ሲሆኑ አይታይም። ከተወሳሰበዉ የሳዉዲ ህግ ለመዳንና የመኖሪያ ፍቃድን ለማደስ ለፓስፖርት እድሳት ኤምባሲ የሚሔዱ ኢትዮጵያዉን ከፍላጎታቸዉ ዉጪ ለአባይ ቦንድ ግዙ ተብለዉ እንደሚቸገሩ ቀደም ሲል የተዘገበ እዉነታ ነዉ።ኤምባሲዉ ኢትዮጵያዉያንን በዘር በብሔር እየመተረ በልማት ስም አፍን ብልጓም ሲዘጋ ኢትዮጵያዉያን በየመንገዱ ላይ ከእንስሳ ባነሰ መልኩ እየተደበደቡ እየተገረፉ ክብራቸዉ ተገፎ ወደ ማጎሪያ ቤት (ተርኺል) እየተወረወሩ ነዉ።
ይህ ኢሰብዓዊ ተግባር አለም አቀፋዊ ትኩረት እንዲያገኝ ለተለያዩ የስብዓዊ መብት ድርጅቶች ማሳወቁ ተገቢ ሲሆን ጉዳዩ ከፍትኛ የሚዲያ ሽፋን እንዲያገኝ ኢትዮጵያዉያን በያሉበት መንቀሳቀስ አለባቸዉ።የፖለቲካ ድርጅቶችም ኢትዮጵያዉያኑ የሚደርስባቸዉን በደል በማዉገዝ ለጉዳዩ ልዩ አትኩሮትን በመቸር አቅማቸዉ በቻለዉ መጠን ሊንቀሳቀሱ ይገባል። የተለያዩ የሐይማኖትና የሲቪክ ማህበራትም ይሁኑ አክቲቪስቶች በመጣመር የሳዉዲ ኤምባሲዎች በሚገኙበት አገራት ሰላማዊ ሰልፍን ቢያረጉ መግለጫዎችን ቢያወጡ የወገኖቻንን ስቃይና መከራን ማስቆም ባይችሉ እንኳ ሊቀንሱት ይችላሉና-ወገን ለወገን መድረሱ ግድ ይላል።
የመጣኸዉ ባዶህን ነው… ባዶ ሆነህም ትመለሳለህ…(ኢንተ፡ጃኢ፡ፋዲ ወተርጃእ፡ፋዲ) ለሚባሉት ኢትዮጵያዉይን ከኛ  ሌላ ደራሽ የላቸዉምንና እንድረስላቸዉ። ልብ ያለዉ ልብ ይበል!