Wednesday, January 23, 2013

የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ክፍያ ሳይፈጽም ጫወታ ማሰራጨቱ የሚዲያ ስነምግባርን የጣሰ ውንብድና ነው ተባለ


ጥር ፲፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ለ ኤል ሲ ቱ የተባለ የቴሌቪዥን ጣቢያ ክፍያ ሳይፈጽም የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከዛንቢያ ቡድን ጋር ያደረገውን ጫወታ ማሰራጨቱ የሚዲያ ስነምግባርን የጣሰ ውንብድና ነው ተባለ::
ምንጮቻችን ባደረሱን መረጃ መሰረት የአፍሪካ ዋንጫ የቴሌቪዥን ስርጭት ባለመብት ለሆነው ለ ኤል ሲ 2 ክፍያ ሳይፈጽም ስርጭቱን ማስተላለፉ ተመልክቶል::
በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የተፈጸመውና ውንብድና የተሰኘው ለስርጭቱ ባለመብት የ 18 ሚሊዮን ብር ሳይከፍል ጠልፎ በህገወጥ መንገድ ባስተላለፈው ጨዋታ ባለመብት የሆነው ድርጅት በህግ ይጠይቀው አይጠይቀው የተባለ ነገር የለም::
የሆነ ሆኖ የኢትዮጵያና የዛምቢያ ጨዋታ ሲደረግ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ክፍያ ሳይፈጽም ጫወታውን በውንብድና በመውሰድ እያስተላለፈ መሆኑን ከደቡብ አፍርካ የስፓርት ተንታኞቹ እየተቹበት እንደነበር ያገኘነው መረጃ ያስረዳል::
ምንጮች እንዳመለከቱት የኢትዮጵያና የዛምቢያ ጨዋታ እየተካሄደ እያለ ያለክፍያ በመጥለፍ ኢቲቪ ሲያስተላልፍ የነበረው ስርጭት ሲቆረጥ በዲኤስ ቲ ቪ ጨዋታውን የሚከታተሉ ያለችግር ማየታቸውን ለመረዳት ተችሎል::
አሁን ዘግይቶ በደረሰንመረጃ መሰረት የተቀሩትን ጨዋታዎች ከባለመብቱ ድርጅት ተከራይቶ ለማሳየት የ ኢቲቪ ሰዎች እየተደራደሩ መሆኑ ተመልክቶል::

    No comments:

    Post a Comment