Monday, January 21, 2013

ግብጽ ኢትዮጵያንና የናይል ተፋሰስ አገሮችን እያስፈራራች ነው


ካርቱምና ግብጽ ፊርማቸውን ያላኖሩበት የናይል ተፋሰስ አገሮች ስምምነት ዋጋ የሌለው መሆኑን አስታወቀች። የህዳሴ ግድብንም መጎነታተል ጀምራለች። የግብጽ የውሃ ሃብትና መስኖ ሚኒስትር ዶ/ር መሐመድ ባሃራ ከቻይና ዜና ወኪል ዡንዋ ጋር 12/2/2013 ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳስታወቁት የናይል ተፋሰስ አገሮች የሚያካሂዱት ማናቸውም ፕሮጀክቶች ግብጽን በአሉታዊ መልኩ የሚነካ ከሆነ አገራቸው ዝም አትልም።
(ፎቶ: saving water)
የግብጽ ውሃ ኮታ መቀነሱን ያስታወቁት ሚኒስትሩ ቻይና ለናይል የላይኛው ተፋሰስ አገሮች ከውሃ ፕሮጀክቶች ጋር በተያያዘ የምትሰጠው ርዳታ ግብጽን የሚጎዳ መሆን እንደሌለበት ማረጋገጥ እንዳለበት አሳስበዋል። የአባይ ተፋሰስ አገሮች ሙሉ በሙሉ በውሃው አጠቃቀም ዙሪያ አዲስ በተረቀቀው ስምምነት ላይ ፊረርማቸውን ያኖሩ ሲሆን ግብጽና ካርቱም አልፈረሙም። ካርቱም ለመፈረም መዘጋጀቷን በይፋ አስታውቃ ነበር።የኢትዮጵያ መንግስት በበኩሉ በአባይ ወንዝ ጉዳይ መጠቀም መብት ለድርድር እንደማይቀርብ፣ አሁን የተጀመረው ፕሮጀክትም ግብጽን እንደማይጎዳ በባለሙያዎች አስጠንቶ ማቅረቡ አይዘነጋም። ከሶስት ወር በኋላ የሚቀርብ የግብጽ ባለሙያዎች የተካተቱበት ጥናት እንደሚኖር መገለጹም የሚታወስ ነው።

No comments:

Post a Comment