Tuesday, January 29, 2013

ከግብርና የተገኘው የውጭ ምንዛሬ ከግማሽ በታች ቀነሰ


ጥር ፳፩ (ሀያ አንድቀን ፳፻፭ /

ኢሳት ዜና:-በግብርና ዘርፍ ባለፉት ስድስት ወራት የሆልቲካልቸር፣ሥጋና የቁም እንስሳት የወጪ ንግድ ገቢ
በአስደንጋጭ ሁኔታ ማሽቆልቆሉን አቶ ተፈራ ደርበው የግብርና ሚኒስትር ዛሬ ለፓርላማው ያቀረቡት ሪፖርት
ጠቆመ፡፡

2005 የኢትዮጵያ የበጀት ቀመር የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት ከሥጋና ከቁም እንስሳት ከወጪ
ንግድ(ኤክስፖርት) 299 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር ለማግኘት ታቅዶ ማሳካት የተቻለው ከግማሽ በታች
ማለትም 130 ሚሊየን ወይም የዕቅዱን 44 በመቶ ያህል ነው፡፡ከዚህ ገቢ ውስጥ 71 በመቶ የቁም እንስሳት
ድርሻ ሲሆን ቀሪው 29በመቶ ከሥጋ ኤክስፖርት የተገኘ ነው፡፡

በሆልቲካልቸር(አበባ፣አትክልትና ፍራፍሬዘርፍም በስድስቱ ወራት ከኤክስፖርት 105 ሚሊየን ዶላር የተገኘ
ሲሆን ይህም ከዕቅዱ ጋር ሲነጻጸር አፈጻጸሙ 46 በመቶ ነው፡፡

የኤክስፖርት ገቢው በምን ምክንያት እንደቀነሰ ሚኒስትሩ ለፓርላማው በንባብ ባቀረቡት ሪፖርት ላይ
የጠቀሱት ነገር የለም፡፡

በአምስት ዓመቱ የመንግስት መርሃግብርን የተለጠጠ ዕቅድ ለማሳካት በሚል ሁሉም መንግስታዊ ተቋማት
የተለጠጠና ሊፈጸም የማይችል ዕቅድ ከመያዛቸው ጋር በተያያዘ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተለይ የኤክስፖርት
ገቢው ከዕቅዱ አንጻር ሲመዘን በከፍተኛ ደረጃ ማሽቆልቆል እየታየበት መሆኑን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው
ምንጮች በተደጋጋሚ መግለጻቸው የሚታወስ ነው፡፡

በዚህ ደካማ መንግስታዊ አፈጻጸምም ሶስተኛ ዓመቱን የያዘው የአምስት ዓመት የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን
ዕቅድ የመሳካቱ ጉዳይ ጥያቄ ምልክት ውስጥ መግባቱም በመታየት ላይ ነው፡፡

በኢትዮጵያ የሚታየው የውጭ ምንዛሬ እጥረት ከፍተ ደረጃ መድረሱን መረጃዎች አመልክተዋል። ችግሩ
በዚሁ ከቀጠለ መለስተኛ መሻሻል አሳይቶ የነበረውን የዋጋ ግሽበት ቀድሞ ወደ ነበረበት ቦታ ሊመልሰው
ይችላል የሚል ፍርሀት አለ።

No comments:

Post a Comment