Friday, December 7, 2012

በባህር ዳር ፍተሻው ተጠናክሯል ሲሉ ነዋሪዎች ገለጹ


ህዳር ፳፰ (ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-ለኢሳት የደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው  ህዳር 29/ 2005 ዓ.ም በባህር ዳር ከተማ የሚያከብረውን የብሄር ብሄረሰቦች ቀን ተከትሎ ወደ ባህር ዳር የሚገቡ ንፁሀን ዜጎችን በሁለቱም የተሽከርካሪ መግቢያዎች እና በአውሮፕላን የሚገቡትን በፍተሻ
እያጨናነቀ፣ ነፃነታቸውን በእጅጉ እየገፈፈ እና ህዝቡን ከመንገዱ እያስተጓጎለ ይገኛል በማለት ነዋሪዎች ገልጸዋል።
ግርማ አያሌው የተባለ ነጋዴ፣ ጌትነት ታየ የተባለ አርሶአደርና ውብሸት የተባለ ተማሪ ምክንያቱ ሳይታወቅ ተይዘው ወደ አዲስ አበባ ተወስደዋል።
ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናትን ጨምሮ ከተለያዩ አካባቢዎች እና ብሄር ብሄረሰቦች የተወከሉ ሰዎች በከተማዋ ይገኛሉ።

No comments:

Post a Comment