Tuesday, February 26, 2013

በጋምቤላ ነዳጅ ተገኘ


ቱሎው ኦይል የሚባለው የነዳጅ ፍለጋ ላይ የተሰማራው ድርጅት እያካሄደ ያለው ቁፋሮ ውጤታማ መሆኑንና ቁፋሮው በተሳካ መልኩ እየተካሄደ በመሆኑ በአጭር ጊዜ ውጤቱን እንደሚያስታወቁ ሚኒስትሯ መናገራቸውን ተመልክቷል። በጋምቤላ ነዳጅ እየፈለገ ያለው የካናዳ ኩባንያ የተሳካ ውጤት እያስመዘገበ በመሆኑ ተጨማሪ ቦታ እንደተሰጠው ይፋ መደረጉ ይታወሳል። ከአካባቢው የሚወጡ መረጃዎች ነዳጅ እንዳለና ጥቅም ላይ መዋል እንደሚችል በመረጋገጡ ተጨማሪ ቦታ መከለል አስፈልጓል።
በፊርማው ወቅትም የማዕድን ሚኒስትሯ ወይዘሮ ስንቅነሽ እጅጉ “ነዳጅ ፈላጊ ኩባንያው በሃገሪቱ ጥናቶችን ሲያደርግ እንደመቆየቱና በሌሎች ሃገራትም ስኬታማ ስራዎችን እንደመስራቱ፣ ፍለጋው ውጤታማ ይሆናል ብለን እናምናለን” ብለዋል። የኩባንያው ዋና ስራ አስፈጻሚ ጀምስ ፍሊፕስ  “በኢትዮዽያም ተስፋ ሰጪ ጥናቶችን አካሂደናል ወጤታማ እንደምንሆነም እምነታችን ነው” ማለታቸውን ፋና ገልጿል።

No comments:

Post a Comment