Friday, February 22, 2013

ህወሃት ሊወድቅ ነው (ለነጻነታችን እንጨክን ፡ እንቆሽሽ!) – በያሬድ አይቼህ



ገዢው ፓርቲ ለጥገናዊ ለውጥ ምንም አይነት ቦታ የማይሰጥ መሆኑን በተደጋጋሚ ግልጽ አድርጓል። አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትርም ይህንኑ ጉዳይ አስምረውበታል። ከዚህ የተነሳ ከገዢው ፓርቲ ጋር የነበረው የምርጫ ትግል በአጠቃለይ መክኗል። ዛሬ አገራችን ሙሉ በሙሉ ወደ ነጻነት ትግል ምዕራፍ ገብታለች።
ፓለቲካ አይነት ፡ አይነት አለው። የምርጫ ፓለቲካ እና የነጻነት ፓለቲካ አንድ አይደሉም። የምርጫ ፓለቲካ ንጹህ ነው ፡ ጭምት ነው። የነጻነት ፓለቲካ ግን ይጨክናል ፡ ይቆሽሻል።
የአገራችን ዘመናዊ የፓለቲካ ታሪክ ሲቃኝ በተደጋጋሚ የሚታየው ፡ ባለፉት 40 ዓመታት አብይ ለውጥ አራማጆች ከየዋህነታቸው እና ከንጹህ የፓለቲካ ስልታቸው የተነሳ ለአገራቸው የነበራቸው ራዕይ ተጨናግፏል ፡ መክኗል ፤ ኢትዮጵያ ያፈራቻቸው ብዙ ታላላቅ ሊሂቃኖቻችንም በከንቱ ጠፍተዋል።
ካለፉት ያልተሳኩ የነጻነት ሙከራዎች ተምረን ፡ አሁን ያለውን ትልቅ የነጻነት ዕድል በተሳካ መልኩ ለመጠቀም ከፈለግን ፡ ለነጻነታችን መጨከን እና መቆሸሽ አማራጭ የሌለው መንገድ ሆኗል።
ሙከራ 1፦ መንግስቱ እና ገርማሜ ነዋይ
አፄ ኃይለስላሴ ላይ ተደርጎ የነበረው የ1953 ዓ.ም የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ አራማጆች ፡ ወንድማማቾቹ መንግስቱ ነዋይ እና ገርማሜ ነዋይ ፡ ውጥናቸው ለምን እንደ መከነ ሲመረመር ዋናው ምክንያቱ ንጹህና ጭምት የፓለቲካ ስልት ነው።
የንጉሳዊው ስርዓት በኢትዮጵያ ጭሰኛ ላይ ያደርግ የነበረውን ጭቆና ችላ ማለት ያልቻሉት ወንድማማቾች ፡ ንጉሱን ከስልጣን አስወግደው ፍትሃዊ የመንግስት እና የምጣኔ ሃብት ስርዓት ለመቅረጽ መመኘታቸው ድንቅ ነበር።
ሆኖም ግን እቅዳቸው ያልበሰለ ፡ ያልጨከነና ለመቆሸሽ ያልደፈረ ነበር። ከዚያም የተነሳ መፈንቅለ መንግስቱ ከሸፈ። መግደል የነበረባቸውን በጊዜው አለመግደላቸው ፡ ማሳተፍ የነበረባቸውን ባለማሳተፋቸው ፡ መቅደም የነበረባቸውን ባለመቅደማቸው የተነሳ የነበራቸው ራዕይ ተኮላሽቷል። የመፈንቅለ መንግስቱ ጠንሳሾች የዋህነታቸውና ፡ ንጹህነታቸው አስበልቷቸዋል።
ሙከራ 2፦ ጄኔራል መርድ ፡ ጄኔራል አምሃ እና ጄኔራል ፋንታ
በ1980 ዓ.ም የደርግን ስርዓት የተቃወሙ ጄኔራሎች ኮሎኔል መንግስቱ ሃይለማሪያምን ከስልጣን አንስተው ፡ በጊዜው ከነበሩ አማጽያን ጋር ተወያይተው አገራዊ ሰላም እና ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ለመፍጠር መፈንቅለ መንግስት ሞክረው ነበር። ሙከራው አልተሳካም ነበር። ያልተሳካበትም ምክንያት ያው ንጹህና ጭምት ስልት ነበር።
የመፈንቅለ መንግስቱ ሙከራ የተከሰተው ኮ/ል መንግስቱ ወደ ምስራቅ ጀርመን ለጉብኝት ሲሄዱ ነበር። በዚህ ወቅት የጠንሳሾቹ ትልቁ ስህተት ተፈጸመ። ስህተቱም “ኮ/ሉ ይበሩበት የነበረውን አውሮፕላን አየር ላይ እንዳለ ይመታ” የሚለውን ሃሳብ አለመቀበላቸው ነው።
“አውሮፕላኑ የህዝብ ንብረት ነው” ፡ “በአውሮፕላኑ ውስጥ ፡ ከኮ/ል መንግስቱ ሌላ ፡ የሌሎችን ሰዎች ህይወት ማጥፋት የለብንም” ከሚሉ ንጹህና ጭምት የፓለቲካ ስልቶች የተነሳ ኮ/ሉ ምስራቅ ጀርመን በሰላም ደረሱ። መፈንቅለ መንግስቱም መከነ።
የግንቦት 1980ው ሙከራ ከየዋህነት እና ከገርነት የተነሳ ከሸፈ። ያኔ ጄነራሎቹ ጨክነው እና ቆሽሸው ቢሆን ኖሮ ፡ አሁን አገራችን የትግራይ ጠባብ ብሄርተኞች ግዛት ከመሆን ይልቅ ፡ የህዝባዊና ዴሞክራሲያዊ መንግስት የመመስረት አጋጣሚያችን ሰፊ ይሆን ነበር።
ሙከራ 3፦ አዲስ አጋጣሚ
አገራችን ላለፉት 21 ዓመታት ስታምጥ ኖራ አሁን ከምጧ የምትገላገልበት ወቅት ላይ ደርሳለች። ህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ሊወጣበት የማይችለው አጣብቂኝ ውስጥ ገብቷል። ህወሃት እንደ ቀድሞው ተመልሶ ሊያንሰራራ አይችልም።
ሆኖም ግን ካለፉት ሁለት የነጻነት ሙከራዎች ተምረን አሁን ያገኘነውን አጋጣሚ በመጠቀም የስልጣንን ልጓም ለህዝብ ካላስጨበጥን ፡ ከጭምት እና ከንጹህ የፓለቲካ ስልት የተነሳ ፡ አዱሱ አጋጣሚ ሊያመልጠን ይችላል።
ስለሆነም ፓለቲካችን የምርጫ ፓለቲካ ሳይሆን የነጻነት ፓለቲካ ስልትን መጠቀሙ ቁልጭ ያለ ጉዳይ ነው። ሳንጨክንና ሳንቆሽሽ ነጻነት አይኖርም። በፍጹም አይኖርም። በጭራሽ አይኖርም። ልብ በሉ! ካለፈው ተምረን የተለየ ስልት ካልተጠቀምን ወደ ባርነት እና ወደ ጭቆና ተመልሰን እንዳረጋለን።
ምን እናድርግ? እንጨክን ፡ እንቆሽሽ!
ግልጽና ቁልጭ ያለ የነጻነት ትግል አማራጭ የሌለው ስልት ነው። በዚህ ወቅት “የትግራይ ህዝብ ወያኔ ነው ወይስ አይደለም?” የሚለውን የሞኝ ዘፈን ትተን ነገሩን ቀለል ማድረግ ነው። የትኛው ትግሬ ‘ነቅዟል’ ፡ የትኛው ትግሬ ‘አልነቀዘም’ የሚለው የሚታወቀው ከነጻነት በኋላ ብቻ ነው።
በነጻነት ትግል ወቅት ንጹሃን ሰዎች ሰለባ መሆናቸው የማይቀር ነው። ለዚያ ህሊናችንን እናስፋ። ህወሃት በስብሶ እንደ ተነቃነቀ ጥርስ ሆኗል ፡ የሚመነግለውና የሚነቅለው የህዝብ መስዋዕትነት ብቻ ነው።
በዚህ ወቅት ፡ ጽዋው እስኪሞላ እና የሃይል ሚዛኑ እስኪያዘነብል ድረስ ፡ ቢያንስ እንደ ግብጽ አብዮት 1 ሺ ሰማዕታት ፡ ቢበዛ ደግሞ እነደ ሶርያ የነጻነት ትግል ከ30 እስከ 60 ሺ ሰዎች ሊሰዉ እንደሚችል በመገንዘብ ህሊናችንን እናዘጋጅ። የሚሰዉ ይሰዋሉ።
ጥቂቶች ተሰውተው 80 ሚሊዮኖች ነጻ ይሆናሉ።
አዎ! የሚሰዉ ይሰዋሉ። “ለምን የድሃ ልጅ ይሙት?” “ለምን ዲያስፓራ አይዋጋም?” ለሚሉት የሰነፎችና የቱልቱላዎች ንትርክ አሁን ቦታና ጊዜው አይደለም። ህወሃት የትግራይን ህዝብ በዘፈን እና በከንቱ ሽንገላ አታሎ የእሳት ራት አድርጐ ስልጣን ላይ ተንፈራጥጧል። ዛሬ ለአገራችን ነጻነት የሚሰዉ ወገኖቻችን ይሰዋሉ።
ደም ሳይፈስ ነጻነት አይኖርም! ይህንን መራራ እውነታ እንቀበል። እንቆሽሽ። ከነጻነት በኋላ እንጸዳለን ፡ እንቀደሳለን።
ሌላው ጉዳይ ፡ የገዢው ፓርቲ ደጋፊዎች ላይ ፡ በተለይም በትግራያን ላይ ሊደርስ የሚችለውን ጥቃት መገንዘብ ነው። በህብረተሰባችን ውስጥ ትግራያን አበይት የስርዓቱ ተጠቃሚና ‘ባለጊዜ’ ናቸው ፡ የሚለው እምነት በሰፊው ስላለ በልዩ ልዩ ክልሎች የሚኖሩ ትግራያን ላይ ጥቃት ሊደርስ ይችላል። ያ አይነቱ ክስተት ሊያስደነግጠንም ፡ ከነጻነት ትግላችን ሊያደናቅፈንም አይገባም።
የገዢው ፓርቲ ካድሬዎች እና ‘ባለጊዜዎች’ ቢኮረኮሙ ፡ ኩርኩሙን ታሪክ ሚመዘግበው ለነጻነት ትግል ከሚከፈለው ዋጋ ጋር ደምሮ ነው። እግረ መንገዳችንን እነርሱንም ነጻ እናወጣቸዋለን።
ያም ሆነ ይህ፦ “ጅብ ከሚበላህ ፡ ጅብ በልተህ ተቀደስ።”

No comments:

Post a Comment