Wednesday, March 27, 2013

እንደዛቱት አቶ አማረ አሞኘ የጠ/ፍርድ ቤት የመሃል ዳኛ በችሎት አልተገኙም::


ዛሬ ማርች 27/2005 ዓ.ም ለመጨረሻ ጊዜ ተብሎ የተቀጠረው የእነ እስክንድር ነጋ ይግባኝ ለኤፕሪል 8 ቀን 2013 መዘዋወሩ ተሰማ። በዛሬው የፍርድ ቤት ውሎ ፍርድ ቤቱ እንደተለመደው ጉዳዩን ለመርመርና ለመወሰን ተጨማሪ ጊዜ ያስፈልገኛል ባለው መሠረት ተጨማሪ ጊዜ ጠይቋል።
ከሰሞኑ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ከአዲስ አበባ “ይህን ሰው አሻባሪ ነው ብላችሁ ስትከሱት ያቀረባችሁት ማሰረጃ በተለያየ ጊዜ የፃፈውን ፅሆፎች፣ ቃለ-መጠይቆች እና በአንድ የፖለቲካ ፓርቲ መድርክ ላይ ተናገረው ያላችሁትን ብቻ ነው፡፡ ሌላው ቀርቶ ፅሁፉና ንግግሩ ያስከተለው አደጋ አልተገለፀም፤ ወይም ምንም አይነት አደጋ አላስከተለም ማለት ነው፡፡ ይህ ደግሞ ተከሳሹ ላይ ቅጣት ለመጣል አያስችልም፡፡ ስለዚህም ሌላ ጥፋተኝነቱን የሚያረጋግጥ ማሰራጃ ካላችሁ አቅርቡ? አሊያም በሚቀጥለው ቀጠሮ ሲቀርብ በነፃ እለቀዋለሁ፡፡”ብለው እስከ ሚ/ሮች ምክር ቤት ድረስ ሄደዋል የተባሉት ዳኛ አማረ አሞኘ በችሎቱ አለመገኘታቸው ተናግረዋል።

No comments:

Post a Comment