Wednesday, March 27, 2013

ፈለገ ፕ/ር አስራት ወልደየስ የትውልዳችን ቃልኪዳን ነው!


“ዛሬ ውድ ሀገራችን ደብዘዋ ጠፍቶ፣ ሕዝቧ ምስቅልቅሉ ወጥቶ ፣ሥነልቡናው እየተሰለበ፣ዓይኑ እያየና ጆሮው እየሰማ፣ ባህሉ እየተንቋሸሸ፣ታሪኩ እየተደለዘና ቅርሱ እየተመዘበረበት የውሻ ሞት እየሞተ ነው። በእንደዚህ ያለ የመከራ ጊዜና ወቅት አንገቱን ደፍቶ፣ያልከፋው መስሎ ሆደሰፊ በመሆንና ሳይቸኩል ፈጣሪውን ለምህረት እየተማፀነ ራሱን ሳያጋልጥ ለትግል የሚሰናዳ ታላቅ ሕዝብ የኢትዮጵያ ሕዝብ ብቻ ነው። ፀረ ኢትዮጵያ ኃይሎች የደገሱለት ድግስ እንደሱማሌና እንደላይቤሪያ እንዲሆን ስለነበረና ይህም አልሳካ በማለቱ፤ ይሄን ውጤት ያስገኘው የኢህአዴግ መልካም አስተዳደር ነው በማለት ዓለምን አደንዝዘው ያዙት። ይህም ድንዘዛ እንዲቀጥል ከኢህአዴግ ጋር በመተባበር ኢትዮጵያ ውስጥ ፍጹም ሰላም መኖሩን፣ፕሬዚዳንት መንግስቱ ኮሚንስቱ ስለተነሱለት በደስታና በመፈንደቅ መኖሩን ፤ የአፍሪካ ምሳሌ የሚሆን ዲሞክራሲ እየፋፋ መሆኑንና ከአንዳድ ጥቃቅን ችግሮች በሰተቀረ የሰብኣዊ መብት በኢትዮጵያ መከበሩን ዲሞክራት ሀገሮች ነን የሚሉ ሁሉ ህዝባቸው በማታለል ላይ ናችው።”
ፕ/ር አስራት ወልደየስ በመዐህድ የወጣቶች ስብሰባ ላይ ከተናገሩት የተወሰድ።
ሙሉ ንግግራቸውን ከታች ካለው ቪዲዮ ላይ ይከታተሉ።
http://www.ethiotube.net/video/19536/Professor-Asrat-Woldeyes

No comments:

Post a Comment