Monday, March 18, 2013

የዮናታን ጉዳይ ፍርድቤት ሲቀርብ እኛ ሁላችን መቅረባችንን መዘንጋት የለብንም(አጭር ማስታወሻ)


በእዚህ ሳምንት በኖርዌይ ትልቅ ኢትዮጵያን በተመለከተ ከተዘገቡት ጉዳዮች አንዱ እና ዋናው  ሕፃን ዮናታን በኖርዌይ የመኖር ፈቃዱበፍርድቤት መወሰኑ ነበር።ሕፃን ዮናታን ከወላጆቹ ጋር በግድ ወደ ሃገሩ እንዲመለስ የኖርዌይ የኢሚግሬሽን ይግባኝ ቦርድ (The Immigration Appeals Board (UNE)) ወስኖ የነበረ መሆኑ ይታወቃል።የፍርድቤቱ የእዚህ ሳምንት  ውሳኔ ብዙዎቻችንንአስደስቷል።እርግጥ ነው ይህንን ያህል አንድ ስደተኛ አለምአቀፍ ሕግን ባልተከተለ መንገድ የስደተኛ መብቱ የፍርድቤት ጉዳይ መሆንነበረበት ወይ? የሚለው እራሱን የቻለ ጥያቄ ቢሆንም።ሆኖም ግን የኖርዌይ የሕግ አሰራርን የተመለከተ ስለሆነ እና ውሳኔው ከሌሎች ሕጎችጋር የሚኖረው ተቃርኖ አና  ስምምነት ኖርወጅያኖችን ብዙ አከራክሯል።ብዙዎችም መንግስታቸውን ወቅሰውበታል።ከእዚህ ባለፈደግሞ በአለምአቀፍ ግንኙነት ላይ የሚያመጣው አንደምታ ብቻ ሳይሆን አሁን በሀገሪቱ ውስጥ እየኖሩ ላሉት አያሌ የውጭ ሀገር ሕፃናትላይ የፈጠረው የስነ-ልቦና ጉዳት በእጅጉ ተፈርቷል።ለእዚህም ነው የኖርዌይ የመገናኛ ብዙሃንም ሆኑ ዜጎች ጉዳዩን የመነጋገርያ አርስትያደረጉት።

ለእኔ የሚታየኝ ግን አንድ አሳሳቢ ጉዳይ አለ። ናታን በኖርዌይ ቴሌቭዥን ዜናው ሲቀርብ እርሱ የመጫወቻ ዕቃዎቹን ይዞ ሲጫወት ነውየሚታየው። ሰው  ምን እያወራ እንደሆነ፣በቴሌቭዥን ይቅረብ አይቅረብ የእርሱ ጉዳይ አይደለም።ጫወታ ላይ ነው። ነገ ግን ዮናታንያድጋል።ሲያድግ ወላጆቹ ያዩትን ፈተና እርሱም ምን ተብሎ እንደነበር ከእነመረጃው ይመለከታል።ያንጊዜ ናታን ጥያቄዎች ይኖሩታል።እንዲህ የሚሉ -
''በሀገሬ ለምን መኖር አልቻልኩምለምን አባት እና እናቴ ተሰደዱእኛ ኢትዮጵያውያን ሀገር አጥተን ከኢትዮጵያ በብዙ ማይሎችየምትልቅ ሀገር መኖርያ ስጭን እያልን መለመን ነበረብን? '' የመሳሰሉት ጥያቄዎች። ይህን ጉዳይ የማነሳው ወላጆቹን ለመውቀስአይደለም። በሀገራችን ያለውን ፖለቲካዊ፣ማህበራዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ ችግር እናውቀዋለን።ወላጆቹም ከእዚህ የተለየ ማድረግ የሚችሉትነገር ሊኖር አይችልም።

የዮናታን ጥያቄ ግን አሁን ላለነው ትውልዶች ሁሉ ነው። ችግር አለብን።አዎን ሀገራችን የመናገር፣የመፃፍ ወዘተ ችግሮች ብቻ ሳይሆንየማሰብ ነፃነት እራሱ ደብዛው ጠፍቷል።የኑሮው ችግር ተባብሷል።ነገር ግን ናታንን ይህ ጉዳይ አሁን አይመለከተውም ።ሕፃንነውና።ትውልዱን ግን ይመለከታል።ባእዳን ሃገራት ለተወሰነ ጊዜ ያጠስልሉ ይሆናል።ዘለቀታነት ግን ሊኖራቸው አይችልም።አንድቀን ሀገሬየማለት ጥያቄ ይነሳል።ዛሬ ያላሰናዱት ሀገር ደግሞ ነገ ሀገር ሊሆን አይችልም። ዮናታን እና የዮናታን እኩዮች ሀገራቸውን ማየት እንዲችሉእና ትውልዱም በውጭ ሀገር ፍርድቤቶች እየተንከራተተ ’የመኖርያ ፍቃድ ስጡን’ ብሎ እንደፍልስጤማውያን ሀገር ለማኝእንዳይሆን፣ዮናታንም ነገ አድጎ እናንተስ የሀገራችሁን ችግሮች ለመፍታት ምን አደረጋችሁ?ብሎ ሳይወቅሰን ሀገራችንን ማሰናዳትችግሯንመፍታት፣ጉድፏን መጥረግ የእዚህ ትውልድ ዕዳ ነው። የዮናታን ጉዳይ ፍርድቤት ሲቀርብ እኛ ሁላችን በ አካል ባይሆን በዜግነት መቅረባችንን መዘንጋት የለብንም።
Refer Yonatan case court decisions
Click http://www.norwaypost.no/index.php/news/latest-news/28255-nathan-7-wins-against-the-immigration-appeals-board 
http://theforeigner.no/pages/news/norway-immigration-officials-lose-ethiopia-case/ 

አበቃሁ 
ጌታቸው በቀለ 
ኦስሎ 

No comments:

Post a Comment