Monday, July 22, 2013

የካድሬው የፍቅር ደብዳቤ (አቤ ቶኪቻው )

cccc
የካድሬው የፍቅር ደብዳቤ
(አቤ ቶኪቻው ) funny,8-)
መሠረት ገና ስምሽን ስጠራው የአገራችን የመሠረተ ልማት አውታሮች ዝርጋታ የደረሱበትን የላቀ ደረጃ እያስታወስኩ…
ልቤ ሃሴት ታደርጋለች፡፡ በዚህ ጊዜ፣ “እንኳንስና ከእርሷ፣ ከስሟ ፍቅር ቢይዘኝ ምን ይገርማል”?! ስል አስባለሁኝ፡፡
መሲ ከሁሉ አስቀድሜ አንቺን የፈለግኩሽ ለጊዜያዊ መሳለጫ ሳይሆን ቀጣይነት ላለው ፍቅር መሆኑን ልገልጽልሽ እወዳለሁ፡፡
የኔ ቆንጆ ከመሬት ተነስቼ እንደ ማንም ጎረምሳ ዳሌሽን፣ ፀጉርሽን እና አጎጠጎጤሽን አይቼ ብቻ የወደድኩሽ አይምሰልሽ፡፡
እንዲያ ስል ደግሞ አካላዊ ውበትሽ አይማርከኝም ለማለት አይደለም፡፡
ዓይኖችሽ ውስጥ ቅንነት፣ ታማኝነት፣ ግልጽነት፣ ተጠያቂነት፣ በሥልጣን ያለአግባብ አለመበልፀግ በአጠቃላይ አስሩንም
የሥነ ምግባር መርሆዎች ይነበቡበታል፡፡
የጥርሶችሽ አቀማመጥ እና አደራደር በአገራችን ያለውን የብሔር ብሔረሰብ እና ሕዝቦች በመፈቃቀድ እና በመቻቻል
እንዲሁም በእኩልነት አብሮ መኖርን ይመስላል፡፡
ገበያ ተኮር በሆነው ግብርናችን የሚመረተው፣ በማዳበሪያ ብቻ ሳይሆን በግብርና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች ልዩ እገዛ በቅሎ
የሚዘናፈለውን የምርጥ ዘር ሰብልን በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የተከታተለ ሰው ፀጉርሽን ሲመለከት “የት ነው የማውቀው?”
ብሎ ግር ሳይለው አይቀርም፡፡ አንድ ናቸዋ”
ጡቶችሽ የሽብር ጥቃት እና ሕገ መንግሥታዊውን ሥርዓት ለማፍረስ የሚሞክሩ የጎዳና ላይ ነውጠኞችን ለመከላከል ዘብ እንደቆሙ መንታ ፌዴራል ፖሊሶች ቀጥ ብለው ላያቸው ከአሁን አሁን ተኮሱ የሚል ድንጋጤን ይፈጥራሉ፡፡
(አበበ ቶላ፤የአቤ ቶኪቻው ሽሙጦች፣2002)

No comments:

Post a Comment