Monday, July 15, 2013

ሆድ ያባውን ሰላማዊ ሰለፍ ያወጣዋል

ሆድ ያባውን ሰላማዊ ሰለፍ ያወጣዋል

ሆድ ያባውን ሰላማዊ ሰለፍ ያወጣዋል

ባለፈው ጊዜ አዲስ አበባ በሰማያዊ ፓርቲ አዘጋጅነት ሰላማዊ ሰልፍ ተደርጎ ነበር፡፡ በሰልፉ ላይም ለገዢው ግንባር ኢህአዴግ ተነግሮታል፡፡ የምጠራጠረው መስማቱን ነው፡፡ ባለፈው ጊዜ ሟች ጠቅላ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሲናገሩ እንደሰማነው አንዲት እንስሳ አለች ትልልቅ አይን አላት ግን አታይም ትልልቅ ጆሮ አላት ግን በቅጡ አትሰማም… ብለውን ነበር፡፡ ይቺን የሰማቻቸው ጊዜ የአብዬን ወደ እምዬ ብላቸው ነበር አሉ… እስንስሳዋን ብዙዎቻችን እናውቃታለን… ለደህንነቷ ስንል ስሟን እንዝለለው…

ኢህአዴግዬ ትልልቅ መስሚያ ጆሮዎች ትልልቅ መመልከቻ ኤኖች አሏት ብዙ ጊዜ ግን በቅጡ ስታይ በቅጡ ስትሰማ አላየናትም፡፡ (የኔ እናት… እግዜር ቀላሉን ያደርግልሽ ብዬ ተቆርቋሪነቴን እገልፃለሁ)

ለማንኛውም እንዲህ የመስማት እና የማየት ችግር ያላለበት ሰው እንዲሰማን እና እንዲያየን ደመቅ ብሎ መታየት እና ጮክ ብሎ መጮህ ብቸኛው አማራጭ ነው፡፡

ትላንት በደሴ እና በጎንደር ህዝቡ ደምቆ ታይቷል ጮክ ብሎም ተናግሯል፡፡ አሁንም ኢህአዴግዬ መስማቷን አንጃ… ስለዚህ ዳግም ድምፃችንን ከፍ ማድረግ አለብን ማለት ነው፡፡

አንድነቶች እንደነገሩን በቀጣይም፤ በሃያ የኢትዮጵያ ከተሞች ሰልፎች ይደረጋሉ፡፡

የሀገሬ ሰው፤ ሆድ ያባውን ሰላማዊ ሰልፍ ያወጣዋል! ኢህአዴግ እስክትሰማን ድረስ ደጋግመን የሆዳችንን ልንነግራት ይገባል ያለ ይመስላል፡፡

ኢህአዴግ ሆይ ስሚ…!
Source: Abe Tokichaw

No comments:

Post a Comment