Thursday, July 25, 2013

አውራምባ ታይምስ የእስክንድር ነጋ ባለቤት ጋዜጠኛ ሰርካለም ፋሲል “ከእኛ እንደ አንዱ ሆነች” አለ!


July 25, 2013
Serkalem
አውራምባ ታይምስ የእስክንድር ነጋ ባለቤት ጋዜጠኛ ሰርካለም ፋሲል “ከእኛ እንደ አንዱ ሆነች” አለ!
አውራምባ ታይምስ ድረ ገጽ ታማኝ ምንጮቼ ነገሩኝ ሲል እንደነገረን ከሆነ ጋዜጠኛ ሰርካለም ፋሲል አንድ ልጇን ናፍቆት እስክንድር ነጋን ይዛ አሜሪካ ገብታለች፡፡
ሰርካለም የዛሬ አመት ለባለቤቷ እስክንድር ነጋ የተሰጠውን አለም አቀፍ ሽልማት ለመቀበል አሜሪካ አቅንታ የነበረ ሲሆን አሁን ግን ወደ አሜሪካ የሄደችው ላትመለስ መሆኑን አውራምባ ምንጮቼ ነግረውኛል ብሎናል፡፡ (በቅንፍም የእኛ ምንጮች ግን እስካሁን ምንም አልነገሩንም፡፡) ከቅንፍ ውጪ አውራምባን ለመረጃው እናመሰግናለን!  በአዲስ መስመር፤
መንግስታችን ሆይ…
ተከፍተን
ተገፍተን
ተሰደን
ተሳደን
ሄደን
ካገር ወጥተን
ሰፋልህ ሰፈሩ…
ሞላልህ አኬሩ…
ወይስ ይቀጥላል
እስክናልቅ ካገሩ…!?

No comments:

Post a Comment