Wednesday, June 26, 2013

ምነዋ ! ማንዴላችን ? !

(ነብዩ ሲራክ)
ምነዋ ማንዴላ ታከተህ
 ጉዞህን በአጭሩ ገታህ ?
mandelaa እስር እንግልቱ ሳያቆምህ
 የእሳት ወላፈን ሳይገድብህ
 የአሸባሪነት ሰሙ ተሰጥቶህ
 ደብድባ ግርፋት መገለሉ ሳይበግርህ
ፍትህን ብለህ ፣ ፍትህ ናፍቀህ ፣ ፍትህ ተነፍገህ
 የነገን ብሩህ ህይዎት ሰንቀህ
በቆፍጣና ወኔ ተሞልተህ ፣
 መስመር ማለፋቸውን ነግረህ
ወጥ የመርገጣቸውን ነውር ፣
 በፈርጣማ ጡንቻ አንበርክከህ
ጭቆናን በጽኑ አውግዘህ
 ወህኒ በኩራት መውረዱ ሳያቆምህ
ረጅሙን መንገድ ተጓዠ አንተ እኮነህ !

አባት ማንዴላ !
ተምረህ ተመራምረህ
 ወኔን በጽናት ተክተህ
አድልኦን በአደባባይ አውግዘህ
 ትግሉን በህቡዕ መርተህ
ደቡበ አፍሪካን ነጻ አውጥተህ
 የአፖርታይድን አከርካሪ ሰብረህ
የመቻቻልን ፍቅርን አብሮነት
 በድል አጥቢያ አስመስክረህ ደም የተቃባ ህዝብን
አጨባብጠህ ነጭ ከጥቁር አስተቃቅፈህ
 የዘረኝነት በቀልን አጽድተህ
በቀልን በይቅርታ ሽረህ
 ጥላቻ የዘር ፖለቲካን አሸቀንጥረህ
አንድ ሁኑ ብለህ ፣ አንድ አድርገህ
 የአፍሪካን የነጻነት ችቦ ለኩሰህ
ከአጽናፍ እስከ አጽናፍ አብርተህ
 የአለም ጭቁን ህዝብ ተስፋ ሆነህ
ረጅም አድካሚውን ጉዞ ተጉዘህ
 የስልጣን ሽግግርን አምንህ
 የህዝብን አደራ ለተተኪው አስረክበህ
(ይህ ከግጥሙ ተቀንጭቦ የተወሰደ ሲሆን ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)
http://www.goolgule.com/why-mandela/

No comments:

Post a Comment