Monday, June 17, 2013

የምእራብ ጎንደር ወይና ደጋው ክፍል በር የሌላቸው የወያኔ እስርቤቶች ስለመሆናቸው፤


ከመካከለኛው ምስራቅ የሚነሱ ጠላቶች ሁልጊዜም ኢትዮጵያን ሲአጠቁ መረማመጃ ያደረጉት ዋና ከከሰላ እስከ ኦሜድላ (ጎጃም) ያለው አካባቢ ነበር። የነዚህ ተጋፊ የኢትዮጵያ ጠላቶችን የመጀመሪያ ገፈታ ቀማሽ የምእራብ ጎንደር ህዝብ ነበር። ለአጼ ተዌድሮስ መነሳት ለአጼ ዮሃንስም መሰዋእትነት ምክንያት የሆኑት በዚሁ አካባቢ የኢትዮጵያን ልእልና ለመድፈር የተደረጉ ሙከራዎችና ጦርነቶች ናቸው። የምእራብ ጎንደር ህዝብም ድንበሩን ለመከላከል ሲል ያልተቋረጠ መስዋእትነትን ከፍልበታል።
በአስራ አምስተኛዉ ምዕተ አመት (ከግራኝ መሃመድ ወረራ) ጀምሮ የአርማጭሆ፣ የወልቃይት፣ የጠገደ፣ የጫቆና የቋራ ህዝብ ‘ድንበር ጠባቂ’ ተብሎ ስያሜ ተሰጥቶት በማህል ኢትዮጵያ በሚነሳ ጦርነት እንዲይሳተፍ በአዋጅ የተከለከለ ነበር። በዚህም ምክንያት የወልቃይት፣ ጠገደ፣ የአርማጭሆ፣ የጭልጋና የቋራ ህዝብ ቤተሰቡን ያሰፈረው ከጠላት ለመመከት የተሻለ ከሆነው ከወይና ደጋው ነው። የምእራብ ጎንደር ወይና ደጋዎች፤ አዲረመጥ የተባለውን የወልቃይት ከተማና አካባቢውን፣ ቀራቅር የተባለውን የጠገደ ከተማና አካባቢውን፣ የአርማጭሆ የጭልጋና የቋራ ወይና ደጋ መሬቶችን ያጠቃልላል። ይሁንና የወይና ደጋው አፈር በውሀ የተሸረሸረ፣ መሬቱም በህዝብ ሰፈራ የተሰላቸና የተጣበበ በመሆኑ በቆሎና ድንች ከመሰለ አነስተኛ ምርቶች በስተቀር የወይና ደጋው ህዝብ የሚተዳደረው በቆላው መሬት በሚያመርተው ምርትና ከብት እርባታ ነው። ለአለፉት ሁለት መቶ አመታት ደግሞ የወይና ደጋው ህዝብ እርሻውንና ከብት ርቢውን በመከተል በቆላዎች ሰፈራዎችን አስፋፍቶ፤ በወልቃይት መዘጋ (አዲጎሹ፣መጉእ፣ቃሌማ፣እጣኖ፣ማይሃርገጽ)፣ የሁመራ፣ የዳንሻ፣ የአብደራፊ፣ የመተማና በቋራ እንደ ዮሀንስ የመሳሰለትን ከተሞችን ቆረቆረ። ይህ ደግሞ የድንበር
ጥበቃውን በይበልጥ አጠናከረው። በዚህም ምክንያት ነበር ጣሊያን በወልቃይት፣ በጠገደ፣ በአርማጭሆና በመተማ አካባቢ ከፍተኛ ሽንፈት የደረሰበትና አካባቢውም ከየትም ለመጣ የኢትዮጵያ አርበኛ ቡድን ከፍተኛ ምሽግ ሆኖ የቆየው። የወያኔ መሪዎች ግን ገና ሀ ብለው እንቅስቃሴ ሲጀምሩ ዋና ተልእኮ አድርገው የያዙት የዚህን ዳር ድንበር ጠባቂ ህዝብ የጀርባ አጥንት መስበር ነው።ይህንንም ህዝብ ነው ትግሬ ባለመሆኑና በተለይም አማራ በመሆኑ ከምድር ገጽ ለማጥፋት በወያኔ እቅድ የወጣለት።
ዛሬ የወልቃይት፣ የጠገደ፣ የአርማጭሆ፣ ጫቆና ቋራ ህዝብ አማራ በመሆኑ ብቻ ለዘመናት ከሞተለት መሬት ተፈናቅሎ በተጨናነቁ በምእራብ ጎንደር ወይና ደጋዎች ታጉሯል። የተጣበበው ህዝብ እንደ አባቶቹ ወደ ቆላ መሬቶቹ ወርዶ ከብት አርብቶና አርሶ እንዳይበላ የትግራይ ክልል አስተዳደር እስክ አፍንጫቸው ባስታጠቋቸው የትግራይ ሰዎች ይጠበቃሉ፤ ይህ አልበቃ ብሎ ደግሞ በወይና ደጋዎቹ ላይ በማንአለብኝነት የተደራጁት የወያኔ አስተዳዳሪዎች በሰበብ አስባቡ (መሳሪያ አሽገሀል ወዘተ) በማለት ሁለንም ቤተሰብ ያንገላቱታል፣ያስሩታል። በተለይ ወጣት ወንዶች ከፍተኛ ያፈና በደልም ይፈጸምባቸዋል።
በዘላቂ መንገድም የወይና ደጋው ህዝብ የሽንፈትና የወኔ መፍሰስ ስሜት እንዲያድርበት ወያኔ ከህዝቡ አብራክ የወጡትን ልጃገረዶችን በትግራይ ጎረምሳ ኮርማዎች ግብረ ስጋዊ አመጽ ያስፈጽምባቸዋል። ይህ በተለይ በወልቃይትና ጠገደ ወይና ደጋዎች በሰፊው የሚካሄድ ወንጀል ነው።
በአጠቃላይ ዛሬ የምእራብ ጎንደር ወይና ደጋዎች በር የማያስፈልጋቸው የወያኔ እስር ቤቶች ሆነዋል።
የመተማ ከተማና አካባቢው፤
ወያኔ በመተማ ከተማና በአካባቢው ያሉትን ገበሬዎችና የከተማው ነዋሪ ህዝብ ሰብስቦ ‚…አካባቢው ለጦር ክምችትና ለጦር ማእከላዊነት እንድሆን ስለተወሰነ ወደ ምስራቅ ባለው የወይና ደጋው ጥግ ለመስፈር ዝግጅት እንድታደርጉ…‛ የሚል ትዕዛዝ ተሰጣቸዉ። በ2009 (እ።አ።አ) ነብስ ገቢያ በሚባለው የቋራ ቆላ ክፍል የሱዳን ወታደር አርሻ አቃጥሎ፣ ንብረት ዘርፎና ወገኖቻችንን ማርኮ ወደ ሱዳን ሲወስድ መተማ የተከማቸው የወያኔ ወታደር አንድት ጥይት እንኳን አለመተኮሱን የኢትዮጵያ የድንበር ኮሚቴ በማያወላዳ ማስረጃ መመዝገቡ የሚታወስ ነው። ስለዚህም መተማ የተከማቸው የወያኔ ወታደር ዋና ተግባሩ የኢትዮጵያኖችን ድህንነት ለማስጠበቅ እንዳልሆነ ግልጽ ነው። ወታደሩ እስካሁን ድረስ ያሳየው ታሪክ ቢኖርም የአማራውን ገበሬ ማፈናቀል፤ ማሰር፣ መግደልና ሃብት ማቃጠል ነው። ወደፊትም ከዚህ
የተለየ አይጠበቅበትም። ይልቅስ በመተማ አቅጣጫ ያገረሸው የወያኔ መልቲ ዘመቻ ግልጽ ያደረገው ነገር፤
፩ .የትግራይ መስፋፋት በአብደራፊና በአካባቢው እንደማይቆም፤
፪. የትግራይን ግዛት ከጣና ባህርና ከተቻለም ባሁኑ ወቅት አባይን እገድባለሁ እያለ ከበሮ ከሚደልቅበት ቦታ ለማድረስ ለሚደረገው የመጨረሻው ዘመቻ የመጀመሪያው መስተንግዶ (አፒታይዘር) መሆኑ ነው።
አደፍርስ ደመላሽ

No comments:

Post a Comment