Sunday, September 15, 2013

አርከበ ‘ለቀቀ’ ወይስ ‘ከዳ’???


አርከበ ዑቅባይ ከህወሓት ጉባኤ በኋላ ስራው በአግባቡ እንደማይሰራ እንዲሁም በቅርቡ ከነቤተሰቡና ከወንድሙ አቶ ጌታቸው ጋር ፓርቲውና ሐላፊነቱ ትቶ አሜሪካን ሀገር መግባቱ ፅፌ ነበር። ‘ፓርቲውና ሐላፊነቱ ትቶ አሜሪካ ገባ’ ማለትና ‘ፓርቲውና ሀገሩ ከዳ’ ማለት ፍፁም የተለያዩ ናቸው። እኔ አርከበ ‘ከዳ’ ብዬ አልፃፍኩም። አርከበ አልከዳም፣ ለቀቀ እንጂ።
ፓርቲ ወይ ሀገር መክዳት (defect ማድረግ) ሌላ ከባድ ነገር ነው። አርከበ ፓርቲውና ሀገሩ እስካልከዳ ድረስ እንደማንኛውም ዜጋ ወደ ሀገሩ መመለስ ወይ ከሀገሩ መውጣት ይችላል። መክዳት ወይ defect ማድረግ የራስን ፓርቲ በመተው የሌላው ተቃራኒ ፓርቲ እስከመቀላቀል ይደርሳል። ስለዚህ ዳንኤል ብርሃነ Daniel Berhane) መልቀቅና መክዳት አትቀላቅል። ያልተፃፈውን አታንብብ።
ሌላው የተክለወይኒ አሰፋ ጉዳይ ነው። አንድ ግዜ ተክለወይኒ ወደ አሜሪካ ሂዶ እዛው መቅረቱና ይህን መረጃ የሰማሁትና ራሴ ያላረጋገጥኩት መሆኔ በመጥቀስ ፅፌ ነበር። አሜሪካ መቅረቱ ትክክል ነበር። እርግጠኛ ያልሆንኩበት መረጃ በምን ጉዳይ እንደቀረ ነበር።
በኋላ እንዳረጋገጥኩት ግን ተክለወይኒ አሜሪካ የቀረው ለሕክምና እንጂ ለፖለቲካ ጥገኝነት አልነበረም። እናም ከጤና ምርመራ በኋላ ተመልሶ መጣ። ወድያው ትግራይ ከገባ በኋላ ወደ ሀገሩ መግባቱ ፅፌያለሁ። ተክለወይኒ ከአሜሪካ መመለስ ከነበረት ግዜ በሃያ (20) ቀናት ግዜ ዘግይቶ ነበር የገባው። ከጓደኞቹ ጋር አልነበረም የተመለሰው፤ ግን የዘገየው ለጤና ምርመራ ነበር።
አሁን ደግሞ የህወሓት የትግራይ ቁልፍ ሰው አቶ ቴድሮስ ሓጎስ በጠና ታሞ በአሜሪካን ሀገር ሕክምና እየተደረገለት ነው።
It is so!!!
Abraha Desta

No comments:

Post a Comment