Thursday, November 22, 2012

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተቆርቋሪ ተማሪ አለ ?


ድሮ ድሮ አዲስ አበባ ዮኒቨርሲቲ የምንሰማው ዜና የሃገራችው ውስጥ ያለውን የመብት ረገጣ  በመቃወም  ፣ የምርጫ መጭበርበርን  ትከትሎ,,,,,  ወዘተ  ተቃወሙ ወይም ድምፃቸውን አሰሙ ሲባል ነበር ። ከተወሰነ ጊዜ በኃላ አዲስ አበባ ዮኒቨርሲቲ አለ እንዴ  እስኪባል ድረስ ዝምታው ሰፍኑዋል ። ከምር ግን በአዲስ አበባ ዮኒቨርሲቲ  ለ ኢትዮጵያ በህዝብ ላይ የሚደርሰው የሰብዓዊ መብት ረገጣ  የሚቆረቆር ዜጋ እንዴት ይጠፋል ። አንድ የ ፌስ ቡክ ጓደኛ ፖስት ያደረገው ነገር  ላስታውሳችሁ ምን አለ መሰላችሁ ¨አዲስ አበባ ዮኒቨርሲቲ ወደ ካድሬ ማሰልጠኛነት ተቀይሯል  ¨ ነበር ያለኝ  ይህ ነገር እውነት ይሆን ? እንደሚታወቀው  በዮኒቨርሲቲዎች ውስጥ የወያኔ ቡችላዎች  ያነፈንፋሉ ፤ ግን እንዴት በወገናችን  ላይ የሚደርሰው   ኢ ሰብዓዊ መብት ረገጣ  በቃ የሚል ይጠፋል !!! እስኪ አለመታደል ሆኖ አዲስ አበባ ዮኒቨርሲቲ የሚገኙ ተማሪዎች  በሃገሪቱ እየተባባሰ ያለውን የመብት ረገጣ ተቃውመው ድምጳቸውን አሰሙ የሚል አስደሳች ዜና  ለመስማት ባንታደልም ። ይህንን  ዜና እነሆ ፦
በአሁኑ ዝርፊያ ከ 50 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ ንብረት አጥቷል
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የአይቲኤስሲ ላብራቶሪ ሰሞኑን ለሁለተኛ ጊዜ ተዘረፈ፡፡
ሪፖርተር ምንጮቹን ጠቅሶ እንደዘገበው ለሁለተኛ ጊዜ ሰሞኑን የተዘረፈው የ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢንስቲትዩቱ ላብራቶሪ እጅግ በጣም ውድ የሆኑ፣ የዘመኑን ቴክኖሎጂዎች ያካተቱና በብዙ ሚሊዮን ብር የሚገመቱ ንብረቶቹን አጥቷል።
ዝርፊያው የተፈፀመው የዲፓርትመንቱን በር ቁልፍ በመስበር እንደሆነም ምንጮቹ ገልጸዋል።
የተወሰዱት ኮምፒውተሮችና የላብራቶሪ ዕቃዎች ግምት ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ ሊበልጥ እንደሚችል ያመለከተው ጋዜጣው፤ጉዳዩን ፖሊስ ይዞ እየመረመረው መሆኑንም ጠቁሟል፡፡
በዝርፊያው ተጠርጥረው ከታሰሩት ውስጥ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ በፍሪላንሰርነትና በቋሚነት የሚያገለግሉ ሠራተኞች እንደሚገኙበት ተመልክቷል፡፡
በዩኒቨርሲቲው ተከስቷል ስለተባለው ዝርፊያ ማብራሪያ እንዲሰጡ የተጠየቁት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ነፃነት ይልማ፦ ‹‹ጉዳዩን ፖሊስ ስለያዘው ምንም ማለት አልችልም፤›› የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
በዝርፊያው ተጠርጥረው በጃንሜዳ አካባቢ በሚገኘው ፖሊስ ጣቢያ ስለታሰሩት ተጠርጣሪዎችና ፖሊስ ስለደረሰበት የምርመራ ውጤት ማብራሪያ ለማግኘት የተደረገው ጥረት አለመሳካቱም ተገልጿል፡፡

No comments:

Post a Comment