Monday, October 13, 2014

Breaking News – Teddy Afro Detained & released on 30 thousand birr bail

Breaking News – Teddy Afro Detained & released on 30 thousand birr bail


October 13, 2014
teddy-afro
The popular Ethiopian music star, Tewodros Kassahun aka Teddy Afro, has been detained this morning by Ethiopian police for what a local media radio outlet reported is related to “buying a car which has does not have its tax paid,  a car he purchased eight years ago.” He reportedly appeared at the Arada First Bench court this morning and the judge ordered that he should be released on a 30,000 birr bail although he has not been released even when the Radio program was on this after noon. The radio did not provide the details of the charge.
Teddy Afro was detained from 2009 to 2010 for “hit and run” by the same car he has been accused of tax evasion now, the Radio said.
Teddy Afro is famous for his songs that touch up on sensitive national issues, human rights, unity and loveand personal activism.
Source:: Debirhan
http://www.zehabesha.com/teddy-afro-detained-court-reportedly-orders-he-be-freed-on-bail-still-unreleased/

Friday, October 10, 2014

በኢትዮ ምህዳር ላይ የተከፈተው ክስ ላይ አለመግባባት ተፈጠረ


  • 4
     
    Share

‹ጋዜጣውንም ሆነ ጋዜጠኛውን አልከሰስኩም›› አቶ ማሙሸት አማረ

‹‹አቶ ማሙሸት የከሰሰበት ሰነድ በዝርዝር ተነቦልኛል›› ጋዜጠኛ ጌታቸው ወርቁ
MEADበኢትዮ ምህዳር ጋዜጣ ቅጽ ሁለት ቁጥር 80 ላይ የመኢአድ ሊቀመንበር አቶ አበባው መሃሪ በሰጡት ቃለ መጠይቅ ሊቀመንበሩ ‹‹ፖርቲውን እያፈረሱ ያሉት ምርጫ ቦርድ፣ ኢህአዴግና አቶ ማሙሸት አማረ በጋራ ሆነው ነው፡፡›› በሚል በሰነዘሩት ሀሳብ አቶ ማሙሸት አማረ ጋዜጣውን ከሰዋል በሚል የጋዜጣው ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ጌታቸው ወርቁ ማክሰኞ መስከረም 26/2007 ዓ.ም ማዕከላዊ ቀርቦ ቃል መስጠቱ ይታወሳል፡፡
ይሁንና አቶ ማሙሸት አማረ ጋዜጣውን አልከሰስኩም በማለት ዜናውን ያወጣውን የሰንደቅ ጋዜጣ ‹‹እንደ ጋዜጠኛ ግራና ቀኝ መረጃ ማየት ባለመቻላቸውና እኔንም ስላላናገሩኝ እንጅ እኔ አልከሰስኩም፡፡›› ሲሉ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ አቶ ማሙሸት ጨምረውም ‹‹አራዳ ፖሊስ ጣቢያ፣ አዲስ አበባ ፖሊስ፣ ማዕከላዊ ምርመራ ቃለ መጠይቁን የሰጡትን አቶ አበባው መሃሪን ለመክሰስ በበቀረብንበት ወቅት ጋዜጣውንስ ትከሳላችሁ? የሚል ጥያቄ ቀርቦልን የነበረ ቢሆንም ‹አንከስም፣ ይህ ጋዜጣውንም ሆነ ጋዜጠኛውን (ዋና አዘጋጁን) ሊያስከስሰው የሚችል ጉዳይ አይደለም፡፡ ስማችን ያጠፋው ቃለ መጠይቁን የሰጠው ሰው እንጅ ጋዜጣው ወይንም ጋዜጠኛው አይደለም› ብለን ጋዜጣውን ስለመክሰስ ቃል አልሰጠንም፣ መስካሪዎቹም ቃል አልሰጡም፡፡ ስለ አቶ አበባው እንጅ ስለ ኢትዮ ምህዳር ያወራነው ነገር የለም›› ሲሉ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
በሌላ በኩል የኢትዮ ምህዳር ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ጌታቸው ወርቁ ቃል ለመስጠት ወደ ማዕከላዊ ባቀናበት ወቅት አቶ ማሙሸት የከሰሱበት ሰነድ በዝርዝር እንደተነበበለት ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡ ጋዜጠኛው አክሎም ‹‹ፖሊስ ሊከሰኝ ሰበብ ከፈለገ በአቶ ማሙሸት በኩል ሊመጣ አይችልም፡፡ አቶ ማሙሸት ነው ዱላ ያቀበላቸው፡፡›› ሲል ገልጾአል፡፡
ጋዜጠኛው ‹‹አቶ ማሙሸት ልክ ጋዜጣው እንደወጣ ስሜን አስጠፍተሃል በማለቱ እኔ የሰራሁት ቃለ መጠይቅ መሆኑንና ይህም ስም ማጥፋት እንዳልሆነ ከማስረዳትም በተጨማሪ፣ እሱንም ጓደኞቹንም ሀሳባቸውን ቢሰጡ እንደማስተናግድ ነግሬው ነበር፡፡ ነገር ግን እሱ እኔ ያለሁበት ቦታ መጥተህ ቃለ መጠይቅ ስራ በማለቱ የጋዜጠኝነት ሙያን የሚጋፋ በመሆኑ በጽሁፍ አሊያም መጥቶ ቃለመጠይቅ እንዲሰጥ ስጠይቀው ዝቶብኛል፡፡›› ሲል አቶ ማሙሸት ከመጀመሪያው ጋዜጣው ስማቸውን እንዳጠፋ እንደሚያምኑና ሊከሱ የሚችሉበትን መነሻ አብራርቷል፡፡
አቶ ማሙሸት በበኩላቸው ‹‹ሰንደቅ ሳያናግረኝ እኔ እንደከሰስኩት አድርጎ ዜና ሰርቷል፡፡ የኢትዮ ምህዳር ጋዜጠኛም አልደወለልኝም፡፡ ይህ ራሱ ሌላ ስም ማጥፋት ነው፡፡ መጀመሪያ እኛም መጠየቅ ነበረበት፡፡ ጋዜጠኛው መጀመሪያም ለእሱም የሰጠነው ሰነድ እጁ እያለ የአንድ ሰው ሀሳብ አቅርቧል፡፡ የእኛን ሀሳብ ለማቅረብ አልሞከረም፡፡›› ሲሉ ይወቅሳሉ፡፡ ጌታቸው በበኩሉ ‹‹አቶ አበባውን ባናገርኩበት ወቅት አቶ ማሙሸት ምንም አይነት ሰነድም መረጃም አልሰጠኝም፡፡ ሀሳቡን በነጻ ሀሳብም ሆነ በሌላ መልኩ መግለጽ እንደሚችል ግን ገልጨለት ነበር፡፡ አሁን አልከሰስኩም የሚለው የሚዲያ ጫና ሲበዛበት ነው፡፡›› ሲል ‹‹አልከሰስኩም›› የሚለው የአቶ ማሙሸት ማስተባበያ መሰረተ ቢስ መሆኑን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡

Speaking Truth to Power: Obang Metho’s Timely Letter to the TPLF

By Ferda Tulu
Ato Obang Metho, the Executive Director for the Solidarity Movement for a New Ethiopia (SMNE) and the well-known human rights advocate among Ethiopians and friends of Ethiopia, recently sent a historic and principled letter to the leaders of the TPLF (http://www.solidaritymovement.org/amharic/140904-Open-Letter-to-the-TPLF.pdf), highlighting the dangerous trajectory our country finds itself under the TPLF’s apartheid-like governance policy. It is a historic letter because no one has systematically documented a protest letter addressed to the leaders of the TPLF on the fundamentally flowed nature of their ethnic policy, the danger it poses for the future of our people, and the need to come-up with an all-encompassing alternative strategy. It is principled because the letter stems from a passion for fundamental freedom, human rights, and democracy for all Ethiopians and harbors no ill will or hatred toward anyone, including the TPLF leadership. In short, the letter is a clarion call for those responsible and their supporters to stop the ominous tumbling cascade and open-up to reform and reconciliation before things are out of hand and too late. It captures the agony of the present and the aspirations for the future. I see it as a challenge not only to the TPLF leadership and its members but to each one of us, regardless of our unique background, to take a critical look at the apartheid-like system foisted upon us and to adapt a principled position to seek a negotiated acceptable solution.
Save Ethiopian Meeting with Obang metho in Israel
Ato Obang’s letter is respectful but does not mince words at pointing the dangers of ethnic politics and the incalculable damages it has already inflicted on Ethiopia and its people, including what it has done to Obang’s own ethnic group – the suspected murder of over 420 innocent ethnic Anuakes under the TPLF in 2003. Despite these atrocities, he holds no grudges and displays remarkable love and forgiveness toward his political opponents for the sake of lasting peace. His letter argues that ethnic politics is an abomination that is devoid of morality, ethics, religion, logic or the rule of law, hence must be discarded. Most importantly, it argues that such a system is nihilistic and antithetical to peaceful co-existence and the pursuit of sustainable development in a multi-ethnic, multi-religious country like ours. Ato Obang urges the TPLF leaders and their supporters to overcome their suspicion and fear and embrace Ethiopia and all Ethiopians.
The Ethnic federation of the sort the TPLF is dogmatically pursuing is not a benign, misguided policy but a toxic prescription that is eating away the social, cultural, and historic fabric that holds the people and the country together. What is scary is that it inhibits the cultivation of a common heritage, assimilation, and destiny essential for the healthy survival and growth of the nation. It has created an unhealthy “them” and “us” mentality among Ethiopians of all hues and persuasions, laying a fertile ground for pitting citizens against each other at the slightest sign of misunderstanding or discord. The pitfalls of such a misguided policy are in the open for any rational and sane person to see. As the direct result of officially-sanctioned policies of the TPLF and by virtue of its total dominance of the Ethiopian government, discrimination is openly exercised in budget and resources allocation among the regions and in the provision of government services. Citizens face blatant discrimination in employment, business, and educational opportunities. The country’s key economic sectors from banking and finance to industry, from transportation to communications, from health services to pharmaceuticals, and from agriculture to food processing have been systematically misappropriated by the TPLF and turned into lucrative financial spigots for the party and its supporters. The country’s key public institutions from defense to foreign affairs, from intelligence to immigration, from law enforcement to the security forces have been brought under the total control of the TPLF. They are disproportionately staffed by TPLF party hacks and loyalists and turned into party instruments for the suppression of dissent. As such, there is no clear demarcation between the TPLF and the government. Governmental institutions have been stripped off their independence and the rule of law has been crippled, and therefore, there is no avenue for redress. Essentially, the government is there to serve and advance not the interests of the people but that of the TPLF. We should not be fooled by Ethiopia’s much talked about economic progress, because any current achievement in the sector should not be confused with a broad-based sustainable economic progress that has taken root for the benefit of the majority.
The independent media is obliterated, opposition politics is suppressed, civil society is stifled, and academic freedom is curtailed. The state media is co-opted into an instrument of propaganda to foster division, misinform and confuse, instill fear, and dehumanize critical voices. Religious and cultural institutions have been infiltrated and shamefully silenced from preaching the truth, justice, equality and freedom. As such, the TPLF has purposely closed off all possible avenues for constructive criticism, and in the proverbial sense, is dancing naked to its own discordant tune. In this type of stifling environment, brave gadflies emerge to tell the truth head-on and seek solutions. Ato Obang has become that sorely needed gadfly by courageously and publicly broaching the subject on everybody’s mind. His argument is that the blatant discriminatory policy of favoring TPLF members, who are exclusively from Tigray, over other citizens, is morally reprehensible, illegal, and should be rejected by all of us. That the party’s discriminatory policy is building resentment against the party and its political base and can no longer be ignored. That unless this injustice is remedied and the abhorrent policy reversed through dialogue and compromise, the accumulating grievance could nudge the nation into an ethnic conflict and undesirable outcomes. He sees it as our national duty to discuss the “elephant in the room” openly and candidly and seek a better model that would guarantee our common future and aspirations. In that sense, the letter carries our collective demand to end the subjugation of the multitude by the few and our yearning for a fair and equitable system.
Thanks to Ato Obang, no self-respecting person can hide any longer behind shenanigans and illogical arguments to prop-up or ignore this morally-bankrupt and illegal system. Despite past disappointments, I for one, hope the letter would not fall on deaf ears. I am optimistic because it also directly appeals to our Tigrayan brothers and sisters to serve as bridges for the change we so desperately and urgently need. One thinks of Ato Abreha Desta, a compatriot who is paying dear price in TPLF dungeons for encouraging dialogue and reform. A brighter Ethiopia lays in the uplifting visions and sacrifices of Obang, Abreha, and multitude of others. I hope and pray that many other Tigrayans quietly agonizing behind the scene would come out in the open and encourage needed reconciliation and reform. I am sure such compatriots would find principled, reliable and solid partners in Ato Obang and like-minded reformers from all corners of Ethiopia.
By the same token, it is disappointing, but not surprising, that some zealot TPLF hardliners and supporters have resorted to raw bigotry and foul language to attack Ato Obang for sending the historic and principled letter to their party and leaders. This attack is not just on Ato Obang but on each one of us. The TPLF and its supporters at minimum should apologize to Ato Obang, condemn the bigotry targeted at him in no uncertain terms, and take concrete action to expel such bigots from their party. Similarly, member and affiliate parties of the EPRDF should condemn this vile bigotry in the strongest terms possible and demand action from the TPLF, if they are indeed about equality and fairness and have a scintilla of independence.
THANK YOU, Ato Obang for being the voice of the voiceless and an inspiration to millions!!!
http://www.zehabesha.com/speaking-truth-power-obang-methos-timely-letter-tplf/

Thursday, October 9, 2014

የእርቅና የመግባባት ሂደት መመዘኛዎች

reconciliation

በኢትዮጵያ ፖለቲካ አዲስ ምእራፍ እንዲኖር መፍትኤው ምንድነው? ያልተሞከረው ብቸኛ መፍትኤ እርቅና መግባባት ነው። ለመሆኑ እርቅና መግባባትን እምቢ ባዩ ማን ይሆን? መንግስት ወይስ ተቃዋሚ? ወይስ ዝምተኛው አብዛኛው ሕዝብ? ወይስ ሁላችንም? ሁሉም ክሱን ትቶ ራሱን ይመርምር። ራሳችንን እንድንመረምርበት  የሚከተለውን ባለ 10 ነጥብ የእርቅና የመግባባት ሂደት መመዘኛዎች እንደ መንደርደሪያ አሳብ አድርገን እንውሰድ። ታዲያ በነዚህ ሚዛን ተመዝነን ቀለን እንዳንገኝ አምላክ የእሽታን መንፈስ ለሁላችንም ይስጠን።
መንግስትን በተመለከተ
1ኛ/ የፖለቲካ እስረኞችን በመፍታት ኢዮቤሊዩ (“Jubilee”) ማብሰር
2ኛ/ በፊታችን ያለውን ምርጫ ፍታዊ ማድረግ(በራስ መተማመንን ያሳያል)
3ኛ/ ተቃዋሚ የሚያቀርበውን መጥፎ አሳብ እያጋለጡ መልካም የሆነውን ግን በስራ ላይ ማዋል
ተቃዋሚን በተመለከተ
4ኛ/ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ከመከፋፈል ይልቅ አንድነትን እንዲፈጥሩ (አንድነት ሃይል ነውና)
5ኛ/ የሰላም ትግሉ ከጦርነትና ከአብዮት አመፅ የፀዳ መሆኑን ከልብ ማስመር
6ኛ/ መንግስት የሚሰራውን ስህተት እያጋለጡ መልካም ስራውን አለመካድ
መንግስትና ተቃዋሚ (ሁለቱንም) በተመለከተ
7ኛ/ የንግግር ቃላት በፀጋና በቅንነት የተሞላ ይሁን (ሰውዬውን ወዶ አሳቡን መጥላት እንማር)
ገለልተኛው አብዛኛው የኢትዮጵያ ሕዝብ በተመለከተ
8ኛ/ ዝምታውን አቁሞ ለእርቅና መግባባት ድምፁን እያሰማ መሟገት ይጀምር
ሁሉንም ኢትዮጵያዊና ትውልደ ኢትዮጵያዊን በተመለከተ
9ኛ/ ለኢትዮጵያ የጋራ በሆኑት ነገር ላይ አንድነትን መግለፅ (ኢትዮጵያ ከፖለቲካችን በላይ ናት)
10ኛ/ አምላክ ኢትዮጵያን እንዲባርካት እጆቻችንን ወደ ፈጣሪ መዘርጋት
ከሁሉም ወገን ልሰማ እወዳለሁና አሳባችሁን ፃፉልኝ:    Z@myEthiopia.com
http://www.goolgule.com/reconciliation-parameters/

Local Ethiopian Community Offers $10,000.00 Reward for Clues on Missing Texas Woman

By CATHERINE ROSS
Almaz
Almaz Gebremedhin, 42
Family members are still searching for any clues to the whereabouts of Almaz Gebremedhin, 42, a Collin County woman who has been missing since last week.
The local Ethiopian community is also rallying support and has raised money for a reward, which will be offered to anyone offering a significant tip to police that brings Gebremedhin home.
The Wylie Police Department said Gebremedhin has not been seen since Thursday at 5 a.m. as she left her home in the 1500 block of Windward Lane in Wylie to head to her job at a nursing home.
“Four days, no sign of her car — we are in the dark. I am in the dark,” Gebremedhin’s husband Sisay Zelelew said Monday.
The two have been married for 16 years and have two children, ages 10 and 8.
Zelelew says he’s known his wife since she was 16 when the two were living in their native Ethiopia.
“She’s a near perfect person,” he added.
Zelelew said he knew something was very wrong when his children’s school called him, informing him his wife had not picked up the children.
When he called the nursing home to see if she was busy at work, co-workers told him she’d never shown up for her shift.
She is 5 feet tall, 134 pounds, and has black hair and brown eyes. She was wearing scrubs when she disappeared.
Her vehicle — a silver 2004 Chevrolet Ventura van with the license plate CVZ-8041 — is also still missing, according to Wylie police.
Anyone with information should call Wylie Police Department at 972-442-8171.


 http://www.zehabesha.com/local-ethiopian-community-offers-10000-00-reward-clues-missing-texas-woman/

Wednesday, October 8, 2014

ዛሬም ሆነ ነገ ፕሮፌሠር አሥራት ወልደዬስ የተለሙልን ፈለግ የትውልዳችን ቃልኪዳን ይሁን!

ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት ለምን እና እንዴት ተመሠረተ?
Moreshልክ የዛሬ ፪(ሁለት) ዓመት መስከረም ፳፯ ቀን ፪ሺህ፭ ዓ.ም.፣ ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት በዋሽንግተን ዲሲ ከተማ ተመሠረተ። ለድርጅቱ መመሥረት ዋና መሠረታዊ ምክንያቱ ኢትዮጵያዊነቱን በምንም ዓይነት ጥርጥር ውስጥ አስገብቶ የማያውቀው ዐማራ የተጋረጠበት የኅልውና መጥፋት አደጋ እንደሆነ አያጠራጥርም። በተለይም ደግሞ የዐማራው ታሪካዊ ጠላቶች በትግሬ-ወያኔ አገዛዝ አሰባሣቢነት ተቧድነው ባለፉት ፵(አርባ) ዓመታት ያደረጉበት የዘር ማጽዳት እና የዘር ማጥፋት ዘመቻ ሲሆን፣ የጥፋቱ እና የግፉ ብዛትም ሆነ ግዝፈት በዮዲት ጉዲት እና በግራኝ አሕመድ የጥፋት ዘመኖች በዐማራው ላይ ከተፈፀሙት ጭፍጨፋዎች ቢበልጥ እንጂ የማያንስ ነው። ስለሆነም ለሞረሽ-ወገኔ መመሥረት ቆስቋሽ የሆነው ምክንያት፣ ከየካቲት እስከ ሰኔ ፪ሺህ፬ ዓ.ም. በደቡብ ኢትዮጵያ ጉራፈርዳ ወረዳ ይኖሩ በነበሩ ከ፸፰(ሰባ ስምንት) ሺህ የሚልቁ የዐማራ ወገኖቻችን ላይ የትግሬ-ወያኔ አገዛዝ ያካሄደው የዘር ማጽዳት ዘመቻ ነበር።
የትግሬ-ወያኔ አገዛዝ ድርጊት በሁሉም የዓለም ክፍሎች ተበትነው በሚኖሩ የዐማራ ነገድ ተወላጅ ኢትዮጵያውያን ላይ ከፍተኛ የሆነ የመጠቃት ስሜትን መጫሩ እይታበልም። በመሆኑም ናዚያዊው አገዛዝ በሥልጣን ላይ ከተቆናጠጠበት ጊዜ ጀምሮ በዐማራው ነገድ ተወላጅ ኢትዮጵያውያን ላይ የሚያካሂደውን የዘር ማጽዳት እና የዘር ማጥፋት ዘመቻ ለማስቆም፣ የዐማራው ልጆች ያላቸው ብቸኛው አማራጭ መንገድ ተደራጅቶ መታገል መሆኑን ከዘገየም በኋላ ለመገንዘብ በቅተዋል። ይህንን ነባራዊ ሁኔታ የተገነዘቡ እና ለችግሩም ተግባራዊ ምላሽ ለመስጠት ቁርጠኛ የሆኑ፣ በዓለም ዙሪያ የሚኖሩ ከሠላሣ የማይበልጡ የዐማራው ልጆች ከያሉበት ተጠራርተው አንድ ለዐማራው መብት መጠበቅ የሚታገል ድርጅት ማቋቋም ስለሚቻልበት መንገድ መምከር ያዙ። በምክር ብቻ አልተገቱም፤ ከ፭(አምሥት) ወራት ያላሠለሰ ጥረት በኋላ በመስከረም ፳፮ እና ፳፯ ቀን ፪ሺህ፭ ዓ.ም. መሥራች ጉባኤ አካሂደው በጉባኤያቸው ማብቂያ ለዐማራው ኅልውና መጠበቅ ቋሚ ጠበቃ የሆነ ድርጅት መመሥረታቸውን ለዓለም ይፋ አደረጉ። ለድርጅቱም መጠሪያ ዐማራው ለችግር ጊዜ «የድረሱልኝ» ጥሪ ማሠሚያ ባደረገው ቃል «ሞረሽ» የሚል ቅፅል እንዲጨመርበት ሙሉ ስምምነት ላይ ደረሱ። እነሆ ዛሬ ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት ፪(ሁለት) ዓመት ያስቆጠረ በሁለት እግሩ የቆመ ጨቅላ ለመሆን በቅቷል።
በኢትዮጵያ በ፲፱፻፶ዎቹ(1950ዎቹ) ከተጠነሰሰው የተማሪዎች የለውጥ እንቅስቃሴ ጀምሮ አንድ በሕግ መልክ ተረቅቆ ያልወጣ፣ ግን ዐማራው በዐማራነቱ ተደራጅቶ ለነገዱ እና ለአገሩ ለኢትዮጵያም ዘላቂ ኅልውና መጠበቅ እንዳይታገል ታሪካዊ ጠላቶቹ የሸበቡበት የተንኮል አሽክላ ነበር። እርሱም «ዐማራው በኢትዮጵያዊነቱ ብቻ እንጂ በዐማራነቱ አይደራጅም።» የሚል አጉል ሽንገላን ያዘለ ክፉ የማደንዘዣ አዚም። የሞረሽ-ወገኔ የዐማራ ድርጅት መመሥረት በ፲፱፻፹፬ ዓ.ም. በታላቁ የሕክምና ባለሙያ ፕሮፌሠር አሥራት ወልደየስ ኢትዮጵያ ውስጥ የመላው ዐማራ ሕዝብ ድርጅት (መዐሕድ) ከተቋቋመ ወዲህ በውጭ አገሮች የሚኖሩ ዐማራ ኢትዮጵያውያን ለነገዳቸው እና ለአገራቸው ኅልውና መጠበቅ ሲሉ ያከናወኑት ትልቅ የዕመርታ እርምጃ ሆኖ ሊወሰድ ይችላል።
ድርጅቱ ኅልውናውን ከተቀዳጀ በኋላ ምን፣ ምን ተግባሮችን አከናወነ?
ሞረሽ-ወገኔ ተመሥርቶ በይፋ እንቅስቃሴውን ማካሄድ ከጀመረበት ከመስከረም ፳፯ ቀን ፪ሺህ፭ ዓ.ም. ጀምሮ ቀዳሚ ተግባሩ አድርጎ የወሰደው፣ በሁሉም የዓለም ክፍሎች ተበትነው የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ዐማሮችን ማንቃት እና በድርጅቱ ጥላ ሥር ማደራጀትን ነው። ድርጅቱ በዓለም ዙሪያ ያሉ ዐማሮችን ለመቀስቀስ ከ፷(ስድሳ) የማያንሱ ወቅታዊ መግለጫዎችን፣ በጥናት ላይ የተመሠረቱ ታሪካዊ ዳራ ያላቸው ጽሑፎችን፣ እንዲሁም በድምፅ እና በምሥል የታጀቡ ቅንብሮችን፣ የዘመኑን የኢትተርኔት ቴክኖሎጂን ጨምሮ በተገኙት አጋጣሚዎች ሁሉ በመጠቀም አሠራጭቷል። እንዲሁም በሁሉም የዓለማችን ክፍሎች ስለድርጅቱ እንቅስቃሴ የሚያስተዋውቁ ከ፳(ሃያ) የማያንሱ ሕዝባዊ ስብሰባዎችን አካሂዷል። በእንቅስቃሴውም ገና ከጅምሩ መልካም ፍሬን አፍርቶ፣ በሁሉም የዓለማችን አኅጉሮች የሚኖሩ ዐማራ ኢትዮጵያውያንን ለማሰባሰብ እና የድርጅቱን አካሎች ለማቋቋም ተችሏል። በአውሮፓ እና በአውስትራሊያ ከመሠረታዊ እስከ አኅጉር-አቀፍ ቅርንጫፎች ተዋቅረዋል። በካናዳ እና በተባበሩት የአሜሪካ ግዛቶችም ከመሠረታዊ ማኅበር እስከ አገር-አቀፍ ቅርንጫፎች ድረስ ደረጃ ደረጃ የማዋቀር ተግባሩ ቀጥሏል። መደራጀት በራሱ ብቻውን የትግሉ ግብ ባይሆንም ለዐማራው ነገድ ኅልውና፣ ብሎም ለኢትዮጵያ ዘለቄታዊነት መቀጠል ይህ የመጀመሪያው ወሣኝ ተግባር መሆኑ ግን አያወላውልም።
በዚህ አጭር ዕድሜው ሞረሽ-ወገኔ ካከናወናቸው ታላላቅ ብሔራዊ ግዳጅን የሚመለከቱ ተግባሮች አንዱ የታላቁን የኢትዮጵያ ንጉሠ-ነገሥት የዳግማዊ አፄ ምኒልክን ታሪካዊ አስተዋፅዖ በአዲሱ ትውልድ እንዲዘከር ማድረጉ ነው። እንደሚታወቀው ዳግማዊ አፄ ምኒልክ የዘመናዊት ኢትዮጵያ መሥራች አባት፣ የጥቁር ሕዝብ መኩሪያ የሆነው የታሪካዊው የአድዋ ጦርነት ድል አድራጊ መሪ፣ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻቸውም ከዘመናዊ ቴክኖሎጂ ጋር እንዲተዋወቁ መሠረታዊ በሆነ የለውጥ ሂደት እንዲያልፉ ያደረጉ ብልህ እና ጀግና መሪያችን ነበሩ። ሆኖም «የእሣት ልጅ አመድ» ሆኖ ተከታዩ ትውልድ እንኳን የእርሣቸውን የአገር ግንባታ ትልም ሊከተል ቀርቶ ባንዶች እና የባንዳ ልጆች የኢትዮጵያን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ ሕይወት እስከመምራት ደርሰዋል። እኒያ የአድዋን ድል ያስገኙ ጀግኖች አያቶቻችን እና ቅድመ-አያቶቻችን ዛሬ በሕይዎት ኖረው ቢሆን ኖሮ ምን ይሉ ይሆን? ስለዚህም ከታሪክ እና ከትውልድ ተወቃሽነት ለመዳን፣ ሞረሽ-ወገኔ የኢትዮጵያን የረዥም ዘመን ታሪክ ሣያዛባ በኢትዮጵያውያን ሁሉ እንዲዘከር ጥረቱን አጠናክሮ ይቀጥላል።
ሞረሽ-ወገኔ ለወደፊት ምን ዓይነት ተልዕኮዎችን ለመወጣት ተሠናድቷል?
ከከ፵(አርባ) ዓመታት በፊት በመላ ኢትዮጵያ በዐማራው ላይ የታወጀው የዕልቂት ዘመቻ፣ ከዘመን ዘመን እየተሸጋገረ ዛሬ ያለንበት እጅግ አስከፊው ደረጃ ላይ ደርሷል። በተለይም የትግሬ-ወያኔ ናዚያዊ ቡድን በ፲፱፻፸፪ ዓ.ም. በወልቃይት-ጠገዴ በሚኖሩ ዐማራ ኢትዮጵያውያን የጀመረውን የዘር ማጥፋት እና የዘር ማፅዳት ዘመቻ አስፋፍቶ በአሁኑ ወቅት በሁሉም የአገሪቱ ማዕዘኖች በሚኖሩ ዐማሮች ላይ አዳርሶታል። ሰሞኑንም በጋምቤላ ክልል፣ መዠንግር ዞን፣ በሜጢ ከተማ እና በአካባቢው በዐማራ ነገድ ተወላጅ ኢትዮጵያውያን ላይ የሚፈፀመው ድርጊት የዚያው የመጀመሪያው የትግሬ-ወያኔ ፖሊሲ ውጤት መሆኑ አያጠያይቅም። ስለዚህ ዐማራው ዘለቄታዊ ኅልውናውን ለማስጠበቅ ምን ማድረግ አለበት?
በመጀመሪያ የችግሩን መኖር መቀበል ይገባል፥ ኢትዮጵያውያን ዐማሮች የዘር ማፅዳት እና የዘር ማጥፋት ዘመቻ ተከፍቶብን እያለቅን ነው።
ተከታታዩ እርምጃ፥ መደራጀት፣ መደራጀት፣ መደራጀት። በምን መልክ? ዐማራው ኢትዮጵያዊነቱን ሣይለቅ በዐማራነቱ መደራጀት አለበት። ሞረሽ-ወገኔም ዘወትር ጥሪውን የሚያቀርበው ዐማራው በዙሪያው እንዲደራጅ ነው።
ትግል ካሉበት አካባቢ ይጀምራል። በተለይ በስደት የሚኖረው ዐማራ በሚኖርበት አካባቢ የሚገኙ አብያተ-ክርስቲያን፣ መስጊዶችን፣ የኢትዮጵያውያን የሆኑ የተለያዩ የማኅበረሰብ ተቋሞችን እና ድርጅቶች በግዴለሽነት ወይም በቸልተኝነት ለትግሬ-ወያኔዎች እና ለሌሎች ፀረ-ኢትዮጵያ ኃይሎች እያስረከበ፤ በተቃራኒው ግን የኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያውያን መሠረታዊ ጠላት በሆነው «በሻቢያ ጥላ ከለላነት ወያኔን በትጥቅ ትግል ተፋልመን ኢትዮጵያን ነፃ እናወጣለን» ከሚለው የጅሎች የቀን ቅዠት ሊነቃ ይገባዋል። ስለሆነም በመጀመሪያ የዕምነት ተቋሞቹን ማስከበር፤ የማኅበረሰብ መሰባሰቢያ መድረኮችን ከሻቢያ፣ ከትግሬ-ወያኔ እና ከመሠል ፀረ-ኢትዮጵያ ኃይሎች መንጋጋ የማላቀቅ ኃላፊነቱ የእርሱው መሆኑን ተገንዝቦ ለተግባራዊ ምላሽ መንቀሳቀስ ይገባዋል። ከዚያ ወደሚቀጥለው የተግባር ምዕራፍ መሸጋገር ይቻላል።
በአገሩ በኢትዮጵያ የዜግነት መብቱን ነፍገው፣ ፍትኅ አሳጥተው፣ ለአስከፊው እና መራሩ የስደት ሕይዎት የዳረጉት የትግሬ-ወያኔ ቀንደኛ ባለሥልጣኖች፣ በውጪ አገሮች እንደርሱው ስደተኛ መስለው መጥተው አፉን ሊሸብቡት አይገባም። ባለፉት ፳፫(ሃያ ሦሥት) ዓመታት አያሌ የትግሬ-ወያኔ ቀንደኛ ነፍሰገዳዮች ወደውጪ አገሮች በ«ስደት» ስም ወጥተዋል። ሆኖም በኢትዮጵያውያን ላይ ለፈፀሟቸው ኢሰብአዊ ግፎች አንዳቸውም እንኳን በፍርድ ችሎት ቀርበው አያውቁም። ይህ ሁኔታ ሊያበቃ ይገባዋል።
ለማጠቃለል፥ ዐማራ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን፦ አባቶቻችን፣ እናቶቻችን፣ አያቶቻችን፣ ቅድመ-አያቶቻችንም ሆነ የቀደሙት ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን ነፃነታቸውን አስከብረው፣ ሙሉ አገር ያስረከቡን ከማንም ባገኙት ችሮታ አይደለም። ስለዚህ በዐማራነታችን ተደራጅተን የነገዳችንን ዘለቄታዊ ኅልውና እናስከብር፤ ይህንንም በማድረግ የውዲቷን አገራችንን የኢትዮጵያን ዳግም ትንሣኤ እናፋጥን።

ዐማራን ከፈፅሞ ጥፋት እንታደጋለን!
ፈለገ-አሥራት የትውልዳችን ቃልኪዳን ነው!
ኢትዮጵያ በቆራጥ እና ታማኝ ልጆቿ መስዋዕትነት ለዘለዓለም ታፍራና ተከብራ ትኖራለች!
http://www.zehabesha.com/amharic/archives/35200

ወያኔ ሲያስር አሜን….ሲገድልም አሜን – በኤፍሬም ማዴቦ


  • 604
     
    Share
police ethiopia
ወያኔ ሲያስር አሜን….ሲገድልም አሜን
በኤፍሬም ማዴቦ
ብዕር የያዘ ማንም ሰዉ በዘመናችን ደግሞ የኮምፒተር መክተቢያ ፊቱ ላይ የደቀነ ሁሉ ከሱ ዉጭ ያለዉን ማንንም ሰዉ “ሌባ”፤ “ባንዳ” ወይም “ከሃዲ” እያለ እንዳሰኘዉ መጻፍ ይችላል። በተለይ በእንደኛ አይነቱ ሀላፊነትም ተጠያቂነትም በሌለበት ህብረተሰብ ዉስጥ ደግሞ የጓደኛዉ ሀሳብ ያልተስማማዉ ሁሉ እየተነሳ የገዛ ጓደኛዉን ባንዳና ከሃዲ አድርጎ ስለሚስለዉ የላይ የላዩን ብቻ ለሚመለከት ሰዉ አገራችን በባንዳና በአገር ወዳድ መሳ ለመሳ ለሁለት የተከፈለች ትመስላለች።  እግዝአብሄር ይመሰገን እዉነቱ ግን ከዚህ እጅግ በጣም የተለየ ነዉ። ርዕሴን የጀመርኩት አሜን ብዬ ነዉና እስኪ አንባቢዉ አንተም አሜን በል። ባንዳነትና ከሃዲነት ኃብታምና በእድገት ወደፊት የገፉ አገሮችን እየዘለለ ደሃና ኋላ ቀር አገሮችን ብቻ የሚጠናወት ተራ በሽታ አይደለም። ብዙዎቻችን አምባገነን መሪዎቻችንን ሸሽተን የተጠለልንባት አገር አሜሪካ እነ ሄንሪ ቤስትንና ጆን ብራዉንን የመሳሰሉ ከሃዲዎችን እንዳበቀለች ሁሉ ኢትዮጵያችንም ትናንት እነ ኃ/ሥላሤ ጉግሳን ዛሬ ደግሞ የኃ/ሥላሤ ጉግሳ የልጅ ልጆች የሆኑትን እነ መለስ ዜናዊን፤ አባይ ፀሐዬንና ሰብሃት ነጋን የመሳሰሉ የለየላቸዉ ከሀዲዎችን አፍርታለች። በነገራችን ላይ ሙስሊሙ በዱአዉ፤ ክርስቲያኑ በፀሎት፤ ጠቢብ በጥበቡ ፤ፀሐፊ በምናቡ የባንዳዉንና የከሃዲዉን ብዛት ለመቀነስ ካልተባበሩ በቀር “ወላድ በድባብ ትሂድ” ብለን ባንመርቃቸዉም የባንዳ አባትና አናት አስካሉ ድረስ ባንዳም መወለዱ አይቀርም።
ደጅአዝማች ኃ/ሥላሤ ጉግሳ ማንም ሳያስገድደዉ ወድዶና ፈቅዶ ለወራሪዉ የጣሊያን ጦር ካደረ በኋላ ከጄኔራል ደቦኖ ጋር ሆኖ እናት አገሩን ኢትዮጵያን ወግቷል። ጣሊያኖች ኃ/ሥላሤ ጉግሳ ከነተከታዮቹ ከጎናቸዉ ተሰልፎ አገሩን ሲወጋ ያደረጉት የመጀመሪያዉ ነገር ይህ ከሃዲ ሰዉ ከጎናቸዉ መሰለፉን የሚያሳዩ ፎቶግራፎች ለዓለም ህዝብ ማሰራጨት ነበር። ታሪክ እራሱን ይደግማል ሲባል አይኑ አላይ እያለዉ በጆሮዉ ብቻ ለሰማ ሰዉ ዛሬ ማረጋገጫዉ እነሆ በግልጽ ቀርቦለታል። ትናንት ማክሰኞ መሰከረም 27 ቀን የወያኔ ቴሌቭዥንና ሬድዮ ኢትዮጵያ ዉስጥ በጋዜጠኞች ላይ የሚፈፀመዉን እስርና ስደት፤ ወያኔ በወገኖቻቸን ላይ የሚፈጽመዉን የዕለት ከዕለት ሰቆቃና እንዲሁም በቅርቡ አምቦና ኦጋዴን ዉስጥ የተካሄዱትን የጅምላ ግድያዎች የሚደግፉ የዚህ ዘመን ኃ/ሥላሤ ጉግሳዎች ዋሺንግተን ዲሲ ዉስጥ ያካሄዱትን የክህደት ሰለማዊ ሠልፍ በተደጋጋሚ ለህዝብ አቅርበዋል። እነዚህ ትናንት ክቡር ባንዲራችን በአለባሌ ሰዉ አንደበት “ጨርቅ” ተብላ ስትሰደብ ከተሳዳቢዉ ሰዉ ጎን ቆመዉ የሳቁና የተሳለቁ ከሃዲ ሆድ አምላኪዎች ዛሬ “ባንዲራችን ተደፈረ” ብለዉ የአዞ እምባ ያነቡብናል። የትኛዉ ባንዲራ?  ለመሆኑ እነዚህ “እናቴን ያገባ ሁሉ አባቴ ነዉ” ባዮች ጀግናዉ ዘርዐይ ደረስ ጣሊያኖችን በራሳቸዉ አደባባዮች አንገታቸዉን በጎራዴ የቀላዉ ለዬትኛዉ ባንዲራ እንደሆነ ያዉቃሉ? እነ አብዲሳ አጋ፤ በላይ ዘለቀ፤ ባልቻ አባ ነብሶና እልፍ  አዕላፋት የኢትዮጵያ ልጆች ምትክ የሌላትን ህይወታቸዉን የሰጡት ለዬትኛዉ ባንዲራ አንደሆነ ያዉቃሉ?
እነዚህ ወያኔ አዲስ አበባ ዉስጥ የገዛ ወገኖቻዉን ሲያስርና ሲገድል አሜን ብለዉ ዋሺንግተን ዲሲ ዉስጥ ሠላማዊ ሠልፍ የሚወጡ የለየላቸዉ ከሃዲዎች ባንዲራ አዲስ መንግስት በመጣ ቁጥር እንደ ፖሊሲና እንደ ካቢኔ ሚኒስቴር የማይቀያየር ቋሚ የአገር ማንነትና የትዉልድ ትስስር መታወቂያ መሆኑን ሊገነዙ ይገባል። ባንዲራ ምክንያታዊ በሆነ መልኩ ሊቀየር ይችላል ብለን ብናስብ እንኳን ምን አይነት ሰዎች ብንሆን ነዉ ባንዲራን የመሰለ ህዝብና አገር ማስተሳሰሪያ ማተብ ኢትዮጵያንና ታሪኳን ከልቡ ለሚጠላዉ መለስ ዜናዊና   የትግራይ ሪፓብሊክ ካላቋቋምኩ ብሎ ይታገል ለነበረዉ ለከሃዲዉ  ስብሀት ነጋ የምንተዉላቸዉ? ደግሞም  እነዚህ ምናምንቴዎች አንደሚሉት ባንዲራችን ላይ ባዕድ አካል ሆኖ የተለጠፈዉና የኢትዮጵያ ህዝብ በተለምዶ “ባላ አምባሻዉ” እያለ የሚጠራዉ የወያኔ ጨርቅ እዉነትም ኢትዮጵያ ዉስጥ የብሄር ብሄረሰቦችን እኩልነት አረጋግጦ ቢሆን ኖሮ ዛሬ አገራችን  በየቀኑ ብሄር ብሄረሰቦች ዉጣልኝ አልወጣም እየተባባሉ የሚተላለቁባት አገር አትሆንም ነበር።  አባቶቻችን የሞቱት ለአረንጓዴ፤ ብጫና ቀይ ባንዲራ ነዉ፤ እኛም ዛሬ በየተሰደድንበት አገር አገሬን እያሰኘ የሚያስጮኸን ይሄዉ አረንጓዴ፤ ብጫ ቀይ ባንዲራችን ነዉ። አገር ቤት ያለዉ ኢትዮጵያዊም አንዱን “ባላአምባሻዉ” ሌላዉን ደግሞ ባንድራዬ እያለ የሚጠራዉ ይህንኑ አረንጓዴ፤ ብጫና ቀይ ባንዲራዉን ነዉ። በአንዲት አገራችን ኢትዮጵያ ዉስጥ እነሱም እኛም ለየቅላችን  የኛ የምንለዉ ባንዲራ ሊኖር በፍጹም አይችልም። ይልቅ ወያኔዎች ሲጠፉ እነሱ ይዘዉብን የመጡት ኮተቶ ሁሉ አብሯቸዉ መጥፋቱ አይቀርምና ዛሬ “ባንዲራችን ተደፈረ” ብላችሁ የምታቅራሩ እዉሮች ነገ ከወያኔ በጸዳችዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ ጭራሽ ባንዲራ ላይኖራችሁ ይችላልና መጀመሪያ ከራሳችሁ ጋር ቀጥሎም ከአገራችሁ ከኢትዮጵያ ጋር እንድትታረቁ አጥብቄ እማጸናችኋለሁ።
የወያኔን ቂልነትና ባዶነት በሰብኩ ቁጥር ትዝ የምትለኝ አንዲት ቀልድ ብጤ አለችና እስኪ ለፈገግታ ትሆናለችና አዳምጡኝ። ሁለት አመት የፈጀዉ የኤርትራና የኢትዮጵያ አላስፈላጊ ጦርነት እንዳለቀ በጦርነቱ ወቅት ስንቅና ትጥቅ በማመላለስ ትልቅ ዉለታ የዋለች ኣንዲት አህያ ጦርነቱ አብቅቶ የድል በዐል ሲከበር መስቀል አደባባይ ተጋብዛ መለስ ዜናዊ ፊት ትቀርባለች፤ በቋንቋ ይግባቡ ነበርና መለስ ጎንበስ ብሎ በጆሮዋ አንድ ነገር ሹክ ሲላት አህይት በደስታ እየፈነጠዘች አደባባዩን መዞር ጀመረች። በልማታዊ አህይት ዝላይና ፍንጠዛ ግራ የተጋቡት የወያኔ ጋዜጠኞች ዜና ያገኙ መስሏቸዉ “ታላቁ መሪ” ምን አለሽ ብለዉ አህይትን ጠየቋት። የዕድሜ ልክ የህወሓት አባል ሆነሻል ተብያለሁ ብላ አህይት ዝላይዋንና ፍንጠዛዋን ቀጠለች።
ትናንት እዚህ ዋሺንግተን ዲሲ ዉስጥ የወያኔን ጭፍጨፋ፤ እስርና በዘር መድሎ የተጨማለቀ ስርዐት አበጀህ ቀጥልበት ብለዉ አደባባይ የወጡ ጥቂት ህሊና ቢሶችና እነሱን አመስግኖ የነጻነት አርበኞችን “ዱሪዬዎች” ብሎ የዘለፈዉ የአድር ባዮች ሁሉ አድርባይ የሆነዉ  ግርማ ብሩ ከዚያች ባድመ ላይ ብዙ ስንቅና ትጥቅ ካመላለሰችዉ ጎበዝ አህያ የሚለዩበት መንገድ ቢኖር አህያዋ ማሰብ ስለማትችል አለማሰቧ እነሱ ግን ማሰብ እየቻሉ አለማሰባቸዉ ብቻ ነዉ። በተረፈ እነሱም አህያዋም የወያኔ አባልነታቸዉ ያስደስታቸዋል፤ ምክንያቱም ሁለቱም አያስቡም። መቼም የገዛ ወንድሙና እህቱ ሲታሰሩ፤ ሲደበደቡና  ሲገደሉ አሜን ብሎ ተቀብሎ ነብሰ ገዳዮችን ደግፎ ሰላማዊ ሠልፍ የሚሰለፍ የሰዉ ዘር ያለዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ ብቻ መሆን አለበት። ለዚያዉም በወያኔ ዘመን ብቻ!
እነዚህን ሆዳሞች ደግሜ ደጋግሜ እዉሮች እያልኩ የምጠራቸዉ አለምክንያት አይደለም። በእርግጥም ስለማያዩ ነዉ። ባለፈዉ ወር አዚህ አሜሪካ ሚዙሪ ግዛት ፈርግሰን የሚባል ከተማ ዉስጥ ከባድ መሳሪያ የታጠቁ ፖሊሶች መሳሪያቸዉን ሰላማዊ ሰልፈኛዉ ላይ ስላዞሩ (ልብ በሉ ስላዞሩ ነዉ ያልኩት እንጂ ስለተኮሱ አላለኩም እነሱም አላደረጉትም) የአሜሪካ ህዝብ፤ መሪዎችና የህዝብ ተወካዮች ምን ያህል እንደተንጫጩ ሁላችንም ተመልክተናል። እነዚያ እዉሮች ያልኳቸዉ ወንድሞቻችንም  እኛ የተመለከትነዉን ተመልክተዉት ይሆናል፤ ግን እነሱ የአዕምሮ እዉራን ናቸዉና ስዕሉን ብቻ ነዉ እንጂ ቁም ነገሩን አላዩትም። ስለዚህም ነዉ የነሱ ድፕሎማት ተብዬዉ  ድንጋይ ራስ (ርዕስ እምኒ) አዲስ አበባ ዉስጥ ያለ መስሎት ሠላማዊ ሠልፈኛ ለመግደል ደጋግሞ ሲተኩስ አበጀህ ብለዉ ሠላማዊ ሠልፍ የወጡለት።  እግዚአብሄር ከዚህ አይነቱ የአዕምሮ እዉርነት ያድነን! እባካችሁ አሁንም አሜን በሉ። እኔ እያረረ የሚስቅ ማሽላ ብቻ ይመስለኝ ነበር . . . .  ለካስ የገዛ ወገኖቹ ሲገደሉ ደስ ብሎት የሚስቅ ሰዉም አለ። አቤት እግዚኦ!!!!
ሌላዉ የገረመኝ ነገር ቢኖር እነዚህ የአዕምሮ እዉራን ትናንት ረፋዱ ላይ ለአሜሪካዉ ዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጆን ኬሪ በጻፉት ደብዳቤ ግንቦት 7 ያ እንቅልፋም ፓርላማቸዉ “ሽብርተኛ” ብሎ የፈረጀዉ ድርጀት ነዉና ምነዉ ዝም ብላችሁ ታያላችሁ ብለዉ ኬሪን መወትወታቸዉ ነዉ። ኬሪ እንደነሱ ጨካኝና አምባገነን መሪዎች የማይወደዉንና የሚጠላዉን ሁሉ አይንህ አላማረኝም እያለ ማሰር የሚችል መስሏቸዋል። እነዚህ ሆዳቸዉ ልባቸዉን የሸፈነ ከሃዲዎች አይገባቸዉም አንጂ የነሱን “ግንቦት ሰባቶችን” እሰሩልን ብሎ ጥያቄ እንኳን ኬሪ የአለማችን ሀይለኛዉ መሪ አባማም ማስተናገድ አይችልም።  እኛስ ብንሆን የምንታገላቸዉ ለዚሁ ነዉኮ – ኢትዮጵያን የሚመራ ሁሉ ሀሳባችን ከሀሳቡ በተጋጨ ቁጥር አንዳያስረንና እንዳይደገድለን። እኔኮ ምን ይሻለኛል . . . . በአንድ በኩል ኢትዮጵያዉያን የወገኖቻቸዉን መገደል ተቃዉመዉ ሠላማዊ ሠልፍ ሲወጡ የወያኔዉ ተላላኪ ግርማ ብሩ የኤርትራን መንግስት ይከስሳል፤ የአይጥ ምስክር ድንቢጥ እንዲሉ የግርማ ብሩ ተላላኪዎች ደግሞ (የተላላኪ ተላላኪ ማለት ነዉ) ግንቦት ሰባት የሚረዳዉ በኤርትራ መንግስት ነዉና ስጋታችንን እዩልን እያሉ ኬሪን ይለማመጡታል። መቼም አዉቆ የተኛን ቢቀሰቅሱት አይነቃም ነዉና የወያኔ ደጋፊዎች አይገባቸዉም አንጂ ለሻዕቢያ ጎንበስ ቀና እያሉና የሻዕቢያን መሪዎች እንደ ታቦት እየተሳለሙ ለዚህ ዛሬ ላሉበት ደረጃ የበቁት የወያኔ መሪዎች ናቸዉኮ። ዛሬ በባነኑ ቁጥር አንዴ ግንቦት ሰባት አንዴ ሻዕቢያ እያሉ ዛር እንደያዘዉ ሰዉ የሚያጓሩትም ተደምስሰዉ ከታሪክ ምዕራፍ የሚፋቁት በዚሁ እንደ ህጻን ልጅ እጃቸዉን ይዞ ለታሪክ ባበቃቸዉ በሻዕቢያ በኩል መሆኑን በሚገባ ስለሚያዉቁት ብቻ ነዉ። ምድረ የወያኔ አጎብጋቢዎች  ዛሬ እቅጩን ልንገራችሁ፤ ወደዳችሁም ጠላችሁ ይህ “ልማታዊ” ብላችሁ የምትጠሩት ነብሰ ገዳይ አገዛዝ ይደመሰሳል- ስጋታችሁ ትክክለኛ ስጋት ነዉ። ግን ከዚህ ስጋት የሚያድናችሁ ኬሪ ሳይሆን የራሳችሁ ሂሊና ብቻ ነዉና ሳይዉል ሳያድር ዛሬዉኑ ኑና ከህዝብ ጎን ተሰለፉ፤ አለዚያ ዕድላችሁ ከኑግ የተገኘህ ሰሊጥ አብረህ ተወቀጥ ይሆናል። መቼም እንደኔዉ የዚያች ምስኪን አገር ልጆች ናችሁና በተረት ብነግራችሁ ይገባችኋል ብዬ ነዉ እንጂ በእናንተና መወቀጥ በሚገባዉ ኑግ መካከል ምንም ልዩነት የለም።
የዘረኞቹ የወያኔ መሪዎችና እንደ ችግኝ ኮትኩተዉ ያሳደጓቸዉ ቡችሎቻቸዉ አስቂኝ ታሪክ በዚህ ብቻ አያበቃም፤ እነዚህ ጣምራ ጉደኞች ብዙ ተነግሮ የማያልቅ ጉድ አላቸዉ።  ወያኔዎች ጋዜጠኛ እያሰሩና ከአገር እንዲሰደድ እያደረጉ ተዉ ያላቸዉን ፀረ አገርና ፀረ ልማት ይሉታል፤ በየሰላማዊ ሠልፉ ላይ ንጹህ ዜጎችን በጅምላ ሲጨፈጭፉ ምነዉ ያላቸዉን ደግሞ ሽብርተኛ ብለዉ ያስሩታል። እነዚህ አረመኔዎች  ይህንን የመሰለ ለጆሮ የሚቀፍ ወንጀል በህዝብና በአገር ላይ ፈጽመዉ ሰዎች በነጻነት ወደሚኖሩበት አገር ሰዉ መስለዉ ሲመጡና ስንቃወማቸዉ ደግሞ እዚህ ዉጭ አገር ያስቀመጧቸዉ ተናካሽ ዉሾቻቸዉ “ኢትዮጵያዊ ጨዋነት” የጎደላቸዉ ብለዉ ይዘልፉናል። ለመሆኑ ለእነዚህ እንደ ዉሻ ቁራሽ ስጋ በተወረወረላቸዉ ቁጥር ለሚያላዝኑ ምናምንቴዎች ማነዉ ኢትዮጵያዊ ጨዋነት እንደነሱ ነዉርን አሜን ብሎ መቀበል ብሎ የነገራቸዉ? ዜጎችን አንደ እንስሳ አየጎተቱ ገድለዉ አስከሬኑን በሟቹ ወንድም እያስጎቱና ይህንን ነዉር በቪድዮ እየቀረጹ መሳቅና መሳለቅ ነዉ ኢትዮጵያዊ ጨዋነት ወይስ  ይህንን ኔሮና ሂትለር ምን አደረጉ የሚያሰኝ ጭካኔና አረመኔነት መቃወም ነዉ ኢትዮጵያዊ ጨዋነት? አዲስ አበባ ዉስጥና እዚህ ዋሺንግተን ዲሲ ዉስጥ ተቃዋሚ ኃይሎችን “ኢትዮጵያዊ ጨዋነት” የጎደላቸዉ ብለዉ የዘለፉት ሬድዋን ሁሴንና ግርማ ብሩ የዉኃ ጠብታን ያክል ኢትዮጵያዊ ጨዋነት በደማቸዉ ዉስጥ ቢኖር ኖሮ “ኢትዮጵያዊ ጨዋነት” የኢትዮጵያዉያንን ህይወት በየአደባባዩ መቀማት አይደለምና እናከብራቸዉ ነበር እንጂ በወጡና በገቡ ቁጥር ስማቸዉን እየጠራን ሌባና ከሃዲ እያልን አናሸማቅቃቸዉም ነበር። ኢትዮጵያዊ ጨዋነት ስንታሰርና ስንዋረድ እልል፤ ስንገደል ደግሞ አሜን ብለን እንደ በሬ አንገታችንን ለቢለዋ መስጠት ማለት አይደለም። ኢትዮጵያዊ ጨዋነት ለወገን ማዘን ነዉ፤ ኢትዮጵያዊ ጨዋነት ወገን ሲጎዳና ሲጠቃ ከለላ መሆን ነዉ። ከሁሉም በላይ ደግሞ ኢትዮጵያዊ ጨዋነት ዜጎች ሰቆቃ ሲፈጸምባቸዉና ሲገደሉ ቆሞ ከመመልከት ይልቅ ወይም የገዳዮች ጠበቃ ከመሆን ባጭር ታጥቆ  ነብሰ ገዳዮችንና የጭካኔ ምልክቶችን ከአገር አናትና ከህዝብ ጀርባ ላይ ማስወገድ ነዉ – ወላድ በድባብ ትሂድ – ይህንን የሚያደርጉ የቁርጥ ቀን ልጆች እናት ኢትዮጵያ ትናንንት ነበሯት፤ ዛሬ አሏት ነገም ይኖሯታል።
ebini23@yahoo.com