Thursday, October 9, 2014

የእርቅና የመግባባት ሂደት መመዘኛዎች

reconciliation

በኢትዮጵያ ፖለቲካ አዲስ ምእራፍ እንዲኖር መፍትኤው ምንድነው? ያልተሞከረው ብቸኛ መፍትኤ እርቅና መግባባት ነው። ለመሆኑ እርቅና መግባባትን እምቢ ባዩ ማን ይሆን? መንግስት ወይስ ተቃዋሚ? ወይስ ዝምተኛው አብዛኛው ሕዝብ? ወይስ ሁላችንም? ሁሉም ክሱን ትቶ ራሱን ይመርምር። ራሳችንን እንድንመረምርበት  የሚከተለውን ባለ 10 ነጥብ የእርቅና የመግባባት ሂደት መመዘኛዎች እንደ መንደርደሪያ አሳብ አድርገን እንውሰድ። ታዲያ በነዚህ ሚዛን ተመዝነን ቀለን እንዳንገኝ አምላክ የእሽታን መንፈስ ለሁላችንም ይስጠን።
መንግስትን በተመለከተ
1ኛ/ የፖለቲካ እስረኞችን በመፍታት ኢዮቤሊዩ (“Jubilee”) ማብሰር
2ኛ/ በፊታችን ያለውን ምርጫ ፍታዊ ማድረግ(በራስ መተማመንን ያሳያል)
3ኛ/ ተቃዋሚ የሚያቀርበውን መጥፎ አሳብ እያጋለጡ መልካም የሆነውን ግን በስራ ላይ ማዋል
ተቃዋሚን በተመለከተ
4ኛ/ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ከመከፋፈል ይልቅ አንድነትን እንዲፈጥሩ (አንድነት ሃይል ነውና)
5ኛ/ የሰላም ትግሉ ከጦርነትና ከአብዮት አመፅ የፀዳ መሆኑን ከልብ ማስመር
6ኛ/ መንግስት የሚሰራውን ስህተት እያጋለጡ መልካም ስራውን አለመካድ
መንግስትና ተቃዋሚ (ሁለቱንም) በተመለከተ
7ኛ/ የንግግር ቃላት በፀጋና በቅንነት የተሞላ ይሁን (ሰውዬውን ወዶ አሳቡን መጥላት እንማር)
ገለልተኛው አብዛኛው የኢትዮጵያ ሕዝብ በተመለከተ
8ኛ/ ዝምታውን አቁሞ ለእርቅና መግባባት ድምፁን እያሰማ መሟገት ይጀምር
ሁሉንም ኢትዮጵያዊና ትውልደ ኢትዮጵያዊን በተመለከተ
9ኛ/ ለኢትዮጵያ የጋራ በሆኑት ነገር ላይ አንድነትን መግለፅ (ኢትዮጵያ ከፖለቲካችን በላይ ናት)
10ኛ/ አምላክ ኢትዮጵያን እንዲባርካት እጆቻችንን ወደ ፈጣሪ መዘርጋት
ከሁሉም ወገን ልሰማ እወዳለሁና አሳባችሁን ፃፉልኝ:    Z@myEthiopia.com
http://www.goolgule.com/reconciliation-parameters/

No comments:

Post a Comment