Thursday, June 20, 2013

የአሜሪካ ኮንግረስ አባላት በኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ውይይት አደረገ

ሰኔ ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:- የአፍሪካ ጉዳዮች ሃላፊ ዶናልድ ያማማቶ፣ በአፍሪካ የዩሴ አይ ዲ ዳይሬክተር ኤሪል ጋስት፣ በአፍሪካ  ጉዳዮች ተመራማሪ  ዶ/ር ፒተር ፓሀም፣ የግንቦት7 ሊቀመንበር ዶ.ር ብርሀኑ ነጋ ፣ ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዳይሬክተር  አቶ ኦባንግ ሜቶና የአምነስቲ ኢንተርናሽናል የአሜሪካ ተወካይ  ሚስተር አዶቲ አኪዌ እና ሌሎችም ታዋቂ ምሁራን ፖለቲከኞች የተሳተፉበት ውይይት የተካሄደ ሲሆን፣ አምባሳደር ያማማቶ እና ዶ/ር ጋስት ኢትዮጵያ በመስቀለኛ መንገድ ላይ እንድምትገኝ ገልጸዋል።
የኢህአዴግ መንግስት የኢኮኖሚ እድገት ማምጣቱን የገለጹት አምባሳደር ያማማቶና ሚስተር ጋስ፣  በሌላ በኩል ግን መንግስት ከፍተኛ የሆነ የሰብአዊ መብቶች ረገጣ በመፈጸሙ የአገሪቱን መጻኢ እድል አደጋ ላይ ጥሎታል ብለዋል።
ዶ/ር ብርሀኑ ነጋ፣ አቶ ኦባንግ ሜቶ እና ሚ/ር አክዌ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች በዝርዝር ያቀረቡ ሲሆን፣ ዶ/ር ብርሀኑ ከአቶ መለስ ሞት በሁዋላ ያለው የኢትዮጵያ ሁኔታ በመለስ ጊዜ እንደነበረው ምናልባትም ከዚያ በበሳ ሁኔታ አስከፊ እየሆነ መሄዱን ገልጸዋል። የኢህአዴግ ባለስልጣናት ከፍተኛ ገንዘብ የዘረፉ እና ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን የፈጸሙ በመሆናቸው እንጠየቃለን በሚል ፍርሀት ስልጣን በቀላሉ ለመልቀቅ እንደማይፈልጉ ዶ/ር ብርሀኑ አክለዋል።
ዶ/ር ብርሀኑ መንግስትን በሀይል ለማውረድ የሚንቀሳቀሱ ሀይሎች እየተጠናከሩ መሄዳቸውን፣ አገሪቱ ወደ አልተፈለገ ግጭት ከማምራቷ በፊት የአሜሪካ መንግስት አሁን የሚከተለውን ፖሊስ ቆም ብሎ እንዲፈትሽ አሳስበዋል።
አቶ ኦባንግ ሜቶ በበኩላቸው ኢትዮጵያውያን አሜሪካ ነጻ ታወጣናለች ብለው እንደማይጠብቁ፣ የራሳቸውን መብት በራሳቸው ለማስከበር እንደሚችሉ ገልጸው፣ አሜሪካ ከአምባገነኑና ዘረኛው የህወሀት መንግስት ጋር የምታደርገውን ግንኙነት እንደገና እንድትፈትሽ ጠይቀዋል።
የውይይቱ ሊቀመንበር የተከበሩ ሚስተር ክሪስ ስሚዝ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የሰብአዊ መብቶች ጥሰት በዝርዝር ለተሰብሳቢው አቅርበዋል።

ESAT Daily News - Amsterdam June 20, 2013 Ethiopia


Monday, June 17, 2013

ከእሁድ እስከ እሁድ

(የሳምንቱ አጫጭር ዜናዎች)

post meles



ኢትዮጵያ ከመለስ ሞት በኋላ!!
አቶ መለስ ከሞቱ በኋላ ኢትዮጵያ ውስጥ ስላለው የፖለቲካ ሁኔታ የአሜሪካ ኮንግረስ የውጪ ጉዳዮች ኮሚቴ የተለያዩ ተናጋሪዎችን ጋብዟል። እኤአ ሰኔ 20፤2013 ቀን በሚካሄደው የኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ የሚሰማበት ውይይት ከኢትዮጵያ ሁለት ተናጋሪዎች ተጋብዘዋል።
ታዋቂው የመብት ተሟጋች፣ በከፍተኛ ደረጃ የኢትዮጵያዊያንን ድጋፍ እያገኙ ያሉትና   በውጭው ዓለም የዲፕሎማሲና የፖለቲካ መስመር ተሰሚነታቸው እያደገ የመጣው የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ ፣ እንዲሁም በበክኔል ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ ተባባሪ ፕሮፌሰር የሆኑት ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ በዕለቱ ተናጋሪ መሆናቸውን ስብሰባውን ያዘጋጁት ክፍሎች ይፋ አድርገዋል።
ከሁለቱ ኢትዮጵያዊያን በተጨማሪ  ቀደም ሲል በኢትዮጵያ የአሜሪካን አምባሳደር የነበሩትና በአሁኑ ወቅት የአሜሪካ የአፍሪካ ጉዳዮች ተጠባባቂ  ጸሐፊ ሆነው እየሰሩ ያሉት ዶናልድ ያማማቶ፣  የአሜሪካ የዓለምአቀፍ የልማት ተራድዖ የአፍሪካ ቢሮ ረዳት አስተዳዳሪ ኤሪል ጋስትና የማይክል አንሳሪ የአፍሪካ ተቋም ዳይሬክተር ዶ/ር ፒተር ፓሃም ንግግር ያቀርባሉ። ምክከሩ በቀጥታ ስርጭት የሚተላለፍ ሲሆን የውይይቱ ዋና ጉዳይ ስለ ኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታና ከመለስ ሞት በበኋላ በኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት አያያዝና የዲሞክራሲ አተገባበር ዙሪያ ጭብጥ የሚያዝበት ነው። (የጥሪው ደብዳቤ መሉ ቃል እንዲህ ይነበባል)
SUBCOMMITTEE HEARING NOTICE
COMMITTEE ON FOREIGN AFFAIRS
Subcommittee on Africa, Global Health, Global Human Rights, and International Organizations Christopher H. Smith (R-NJ), Chairman
TO: MEMBERS OF THE COMMITTEE ON FOREIGN AFFAIRS
You are respectfully requested to attend an OPEN hearing of the Committee on Foreign Affairs, to be held by the Subcommittee on Africa, Global Health, Global Human Rights, and International Organizations in Room 2172 of the
Rayburn House Office Building (and available live on the Committee website atwww.foreignaffairs.house.gov):
DATE: Thursday, June 20, 2013
TIME: 10:00 a.m.
SUBJECT: Ethiopia After Meles: The Future of Democracy and Human Rights
WITNESSES: Panel I
The Honorable Donald Y. Yamamoto
Acting Assistant Secretary of State
Bureau of African Affairs
U.S. Department of State
The Honorable Earl W. Gast
Assistant Administrator
Bureau for Africa
U.S. Agency for International Development
Panel II
 Berhanu Nega, Ph.D.
Associate Professor of Economics
Bucknell University
 J. Peter Pham, Ph.D.
Director
Michael S. Ansari Africa Center
Atlantic Council
Mr. Obang Metho
Executive Director
Solidarity Movement for a New Ethiopia
ግብፅ የያዘችው አቋም ተቀባይነት የለውም
ግብፅ የታላቁ የህዳሴ ግድብ ጉዳይ ለውስጥ የፖለቲካ ችግሯ መፍቻነት እያዋለችው መሆኑን የመንግስት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ሚኒስትር  በረከት ስምኦን ገለፁ፡፡ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ አቶ አለማየሁ ተገኑ በበኩላቸው ግብፅ የግድቡን የሃይል ማመንጨት አቅም መቀነስ እንደመፍትሔ ማቅረቧ ተቀባይነት የለውም ብለዋል፡፡
abay1የመንግስት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ሚኒስትርና የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የህዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሔራዊ ምክር ቤት ፅ/ቤት ዳይሬክተር አቶ በረከት ስሞኦን ግብፅ ለውስጥ የፖለቲካ ችግሯ መፍቻነት እያዋለችው መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የግንባታ ሂደቱ 22 ነጥብ 5 በመቶ የደረሰውና በተያዘው ዓመት 26 በመቶ ስራው እንደሚጠናቀቅ የሚጠበቀው የህዳሴው ግድብን አስመልክቶ አንዳንድ የተቃዋሚ ፓርቲዎች የያዙት አቋም ትክክል አለመሆኑንም ሚኒስትር በረከት ተናግረዋል፡፡
ሚኒስትር በረከት አያይዘው እንደገለፁት ግብፅ ጉዳዩን የውስጥ የፖለቲካ ችግሯን ለማርገብ እየተጠቀመችበት መሆኑን ጠቅሰው ሀገሪቱ የጦርነት አማራጭ የተዘጋ አይደለም ትበል እንጂ ወደዚህ ተግባር ትገባለች ተብሎ አይጠበቅም ብለዋል፡፡
የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር አለማየሁ ተገኑ በበኩላቸው የጦርነት አማራጭ እንደማያዋጣ የተገነዘበ የሚመስለው የግብፅ መንግስት የህዳሴን ግድብ የማመንጨት አቅም፣ የሚይዘውን የውሃ መጠንና ከፍታ እንዲቀንስ የሚያነሳው የመፍትሔ ሃሳብ ተቀባይነት የለውም ብለዋል፡፡
የመንግስት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ሚኒስትርና የታላቁ ህዳሴ ግድብ የህዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሔራዊ ምክር ቤት ፅ/ቤት ዳይሬክተር በረከት ስሞኦን እና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር አለማየሁ ተገኑ በተገኙበት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ሬድዮና በ ኤፍ ኤም አዲስ 97.1 በህዳሴው ግድብ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙርያ ባተኮረው  የቀጥታ ውይይት ላይ በአገር ውስጥና ውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እያሳዩት ያሉትን ግድቡን የመገንባት ቁርጠኝነትና ድጋፍ አጠናክረው እንዲቀጥሉ ሃላፊዎቹ ጥሪ አቀርበዋል፡፡ (ምንጭ፤ ኢሬቴድ)
ፓርላማው የቅኝ ግዛት ዘመን ውል የሚተካ አዲስ ህግ አፀደቀ
አሥራ አንዱ የአባይ ተፋሰስ ሃገሮች ሩዋንዳ፣ ቡሩንዲ፣ ኮንጎ ፣ ታንዛኒያ፣ ኬንያ፣ ዩጋንዳ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሱዳን፣ ኢትዮጵያ፣ ኤርትራ፣ ግብፅ ናቸው፡፡ የተፋሰሱ አገራት በተመለከቱበት ካርታ ላይ ደቡብ ሱዳን አልተካተተችም። ካርታው ሲሰራ ደ/ሱዳን በወቅቱ ነጻ አገር አልነበረችም ነበር።
nile_basin_countries
የኢትዮጵያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ33ተኛው መደበኛ ስብሰባው ከመከረባቸው አምስት ጉዳዮች አንዱ የሆነውን የአባይ ተፋሰስ የትብብር ስምምነት ረቂቅ አዋጅ እንዳፀደቀ የምክር ቤቱ የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ አያና ከበደ ለቪኦኤ ገልፀዋል።
ስምምነቱ አባይን በጋራና በፍትሃዊ መንገድ ለመጠቀም በተፋሰሱ አባላት አገሮች ካሁን ቀደም ኢንቴቤ-ዩጋንዳ ውስጥ የተፈረመ መሆኑ ይታወቃል።
ከኢትዮጵያ በስተቀር አምስቱ አገሮች ማለትም የርዋንዳ፣ የታንዛኒያ፣ የዩጋንዳ፣ የኬንያና የቡሩንዲ ፓርላማዎች ቀደም ብለው ውሉን ያፀደቁት መሆኑን የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያው ተናግረዋል።
የኢንቴቤ ስምምነት እየተባለ የሚጠራው ውል ቅኝ ገዢ በነበረችው ታላቋ ብሪታኒያ በአውሮፓ የዘመን አቆጣጠር በ1929 ዓ.ም የተረቀቀና በናይል ወንዝ አጠቃቀም ላይ ከተፋሰስ አገሮች ይልቅ ለግብፅ ሙሉ መብት የሚሰጠውን ውል የሚተካ መሆኑ ይታወቃል።
ውሉ ዛሬ በኢትዮጵያ የተወካዮች ምክር ቤት መፅደቁ ሰሞኑን በግብፅና በኢትዮጵያ መካከል በአባይ ወንዝ አጠቃቀም ዙሪያ ከሚካሄደው ውዝግብ ጋር ግንኙነት እንደሌለው የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያው ተናግረዋል፡፡(ምንጭ የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ)
በአባይ ግድብ ዙሪያ ከፍተኛ ጥበቃ ማድረግ ተጀመረ
ለኢሳት የደረሰው የደህንነት መረጃ እንዳመለከተው ከፍተኛ ወጪ የወጣባቸው ቻይና እና ሩሲያ ሰራሽ ራዳሮች ሰሞኑን በአካባቢው ተተክለዋል።
radarመንግስት ማንኛውንም አይነት ድንገተኛ የአየር ወይም የሰርጎ ገቦች ጥቃት ለመከላከል ዘመናዊ ራዳሮችን ከመትከል በተጨማሪ የተወሰኑ የአጋዚ ክፍለ ጦር አባላት በአስችኳይ ወደ አካባቢው እንዲንቀሳቀሱ አድርጓል። በፌደራል ፖሊስ ሲደረግ የነበረው ጥበቃ በመከላከያ ሰራዊት አባላት እንዲጠናከር ያደረገው መንግስት ፣ በሻለቃ አበራ ወረታው አዛዥነት የሚመራው የምእራብ እዝ የ44ኛ ዳሎል ክፍለ ጦር አራተኛ ሪጂመንት በቤንሻንጉል እንዲቀመጥ ተወስኗል።
በደቡብ ሱዳን ያለው ጦር የአቅም ግንባታ ስልጠና እንዲያገኝም አብዩታዊ ዴሞክራሲ እና ወታደራዊ አመራር የሚል ርእስ ያዘለ የመወያያ ጽሁፍ ተዘጋጅቶ በ ስልጠና ዋና መምሪያ ሌ/ጄኔራል ታደሰ ወረደ የሚመራ ቡድን ወደ አብየ አቅንቷል፡፡
ኢሳት የደረሱትን ሙሉ ወታደራዊ የደህንነት መረጃዎች ለአገር ደህንነት ሲባል ይፋ ከማውጣት መቆጠቡን ለመግለጽ ይወዳል። የኮሚኒኬሽን ሚኒስትሩ አቶ በረከት ስምኦን ኢትዮጵያ ምንም አይነት ወታደራዊ ዝግጅት እያደረገች አይደለም በማለት ሰሞኑን መግለጫ ቢሰጡም፣ ለኢሳት የደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው ከሆነ ግን ኢትዮጵያ ግድቡን ከጥቃት ለመከላከል እንቅስቃሴዎችን ጀምራለች።
በሌላ ዜና ደግሞ የግብጽ መንግስት ኢትዮጵያ በግድቡ ላይ የማሸሻያ እርምጃ እንድታደርግ መጠየቁ ታውቋል። የግብጽ መንግስት ያቀረበው ጥያቄ የግድቡ ከፍታ ከነበረበት 145 ሜትር ወደ 100 ሜትር ዝቅ እንዲል፣ 74 ቢሊዩን ሜትር ኩብ ውሃ እንደሚይዝ የሚጠበቀው አዲሱ ሀይቅ   ከ 32 እስከ   40 ቢሊዩን ሜትር ኩብ ውሀ እንዲቀንስ መጠየቁን የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡ የሀይል አቅርቦቱም ወደ 3000 ሜጋ ዋት እንዲቀንስ የግብጽ መንግስት ጥያቄ አቅርቧል። (ምንጭ፤ ሰኔ ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና)
ለአማራው መፈናቀል ተጠያቂ የተባሉ 2 የቤኒሻንጉል ም/ቤት አባላት ያለመከሰስ መብት ተነሳ
የቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ምክር ቤት ትናት ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ በክልሉ ነባር የአማራ ብሄረሰብ ተወላጆች መፈናቀል ምክንያት ናቸው ያላቸውን 2 የምክር ቤት አባላትን ያለ መከሰስ መብት አነሳ።
benishangulያለ መከሰስ መብታቸው ተነስቶ በቁጥጥር ስር ውለው በህግ እንዲጠየቁ የተደረገው በክልሉ ከማሺ ዞን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መለተጊ ቦጋለና የመንግስት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ሃላፊው አቶ ገርቢ በጊዜው ናቸው።
እነዚህ አመራሮች የክልሉ መንግስትና ፓርቲው በማያውቀው ሁኔታ በዞኑ ያሶ ወረዳ ነባር የአማራ ብሄረሰብ ተወላጆችን እንዲፈናቀሉ ማድረጋቸው በመረጃ በመረጋገጡ ነው እርምጃው የተወሰደባቸው።
በዚህ የማፈናቀሉ ተግባር ተሰማርተዋል ተብለው የተጠረጠሩ 18 የሚደርሱ ከቀበሌ እስከ ዞን የሚገኙ አመራሮች ጉዳያቸው እየተጣራም ይገኛል።
የቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ሃላፊ አቶ ይስሀቅ አብዱልቃድር ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንዳሉት ፥ የክልሉ መንግስት ጉዳዩን በማጣራት ባአሁኑ ጊዜ ተፈናቃዮች ተረጋግተው ወደቀያቸው ተመልሰው መደበኛ ኑሮዋቸውን እያከናወኑ ነው። አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 8 ፣ 2005 (ኤፍ.ቢ.ሲ)
“ዋነኛው የእንግልት ሰለባ አህያው ነው”
ፖሊስና እርምጃው በግንቦት 30 እትሙ በምስራቅ ሸዋ መቂ ከተማ ውስጥ አንድ ግለሰብ ጅብ አጥምዶ ፤ ከማጥመዱም በአህያ በሚጎተት ጋሪ ጭኖ ሲዘዋወር በመገኘቱ ‹‹እንሰሳትን በማንገላታት›› ክስ መታሰሩን ነግሮናል፡፡
donkeyሰውየው ‹‹ጅቡን ከነነፍሱ ያጠመድኩት እየተፋፋመ ያለውን የፀረ ሙስና ትግል መቀላቀሌን ለማሳየት ነው›› ካላለ በስተቀር ትንሽ በቁጥጥር ስር ሳይቆይ አይቀርም፡፡
‹‹እንሰሳትን በማንገላታት›› የሚለው ክስ እንግልቱ በየትኛው እንሰሳ ላይ እንደተፈፀመ አጥርቶ ባይገልፅም፤ እንደኔ በዚህ ጉዳይ ዋነኛው የእንግልት ሰለባ አህያው ነው፡፡
መደበኛ የሸክም እንግልቱን ተዉት፡፡ ይህ አህያ ታሪካዊ አዳኙን/ ጠላቱን ከነነፍሱ ተሸክሞ ሲዞር ‹‹ካሁን አሁን ዘነጠለኝ›› እያለ መሳቀቁ ብቻ ከባድ የስነልቦና እንግልት አይደለም?
ይህን ጅቦችን ተሸክመው ሲሄዱ የኖሩ ምስኪን አህዮች ሁሉ ጠንቅቀው ያውቃሉ፡፡
ወጣም ወረደ፤ ክሱ ጅቡን የእንግልቱ ተጠቂ አድርጎ ያቀረበ መሆኑን ከሰማን ‹፣ድሮም የኛ ሕግ ለጅቦች ያዳላል›› ማለታችን የማይቀር ነው፡፡
(ምንጭ፤ ነቆራ እና ሌሎችም ወጎች ከሕይወት እምሻው ጋር – Hiwot Emishaw)

ESAT Daily News - Amsterdam June 17, 2013 Ethiopia


ከውስጥ በአምባገነን ስርዓት የታፈነችና ከውጭ ዙሪያዋን በጠላት የተከበበች አገር



“ወንዝም ገነትን ያጠጣ ዘንድ ከዔድን ይወጣ ነበር፤ ከዚያም ለአራት ክፍል ይከፈል ነበር፡፡
የአንደኛው ወንዝ ስም ፊሶን ነው፤ እርሱም ወርቅ የሚገኝበትን የኤውላጥ ምድርን ይከብባል፤ የዚያም ምድር ወርቅ ጥሩ ነው፤
ከዚያም ሉልና የከበረ ድንጋይ ይገኛል፡፡
የሁለተኛው ወንዝ ስም ግዮን ነው እርሱም የኢትዮጵያን ምድር ሁሉ ይከብባል…” ይላል መጽሓፍ ቅዱስ በኦሪት ዘፍጥረት 2፡10-13፡፡
ግዮን የተባለው አባይ ነው፤ የአባይ ምንጭ ደግሞ ኢትዮጵያ ናት፡፡ ብዙ ሰዎች የአባይ መነሻ ጣና ሐይቅ እንደሆነ ያምናሉ፡፡ ነገር ግን የአባይ ትክክለኛ መነሻ በምዕራብ ጎጃም ሰከላ ወረዳ ውስጥ የመትገኘው ፈለገ ግዮን ናት፡፡ አባይ ፈልቆ ከምንጭነት ወደ ጎርፍነት በመቀየር ከዚያም ነብስ ዘርቶ ወደ ጅረትነት ከፍ የሚልበትን የተቀነበበ አነስተኛ ጉድጓድ ለአንድ የኃይማኖት አባት ለማሳየት “አባ እይ” ከሚል የሌላ ሰው ንግግር አባይ የሚለውን ስያሜም እንዳገኘ በአፈ ታሪክ በሰፊው ይነገራል፡፡ የአባይን ምንጭ አስሶ ለመጀመሪያ ጊዜ ያገኘው ጀምስ ብሩስ የተባለ አውሮፓዊ እንደሆነ ይታመናል፡፡
አባይ ዘይት ሆኖ በጣና ላይ ጋልቦበት ኢትዮጵያን ልክ እንደ መቀነት ወገቧን ዞሮ ድንበሯን በመበጠስ ከድቷት ከምድሯ በመውጣት ዜግነቱንም ስሙንም ይቀይራል፡፡ ብሉ ናይል ተብሎ ከቪክቶሪያ ሐይቅ ከሚነሳው ነጭ አባይ ጋር ካርቱም ላይ በመደባለቅ አስር አገራትን አቆራርጦ በርዝመቱ በዓለም አንደኛ በመሆን ሜዲትራኒያን ባህር ይገባል፡፡
ከሰማንያ በመቶ በላይ የሚሆነውን የውሃ መጠን ከኢትዮጵያ የሚያገኘው ናይል ከሚያልፍባቸው አገሮች ግብፅና ሱዳን ይገኙባቸዋል፡፡ እነዚህ ሁለት አገሮች ኢትዮጵያ ወደ እነሱ ምድር የሚፈስ ወንዝ መነሻ ሆና በመፈጠሯ ምክንያት ብቻ በጠላትነት ፈርጀዋት ለረጅም ዘመናት ኖረዋል፡፡ በተለይም ግብፅ ይህችን ስልጣኔን ከዓለም ሁሉ ቀድማ ጀምራ ኃያል የነበረችና ዛሬ ጭራ የሆነች የድሆችና የመከረኞች ምድር ኢትዮጵያ የወደፊት የመኖርና ያለመኖር ህልውናዋ ጠንቅና ስጋቷ ምንጭ እንደሆነች አድርጋ ስትመለከታት አያሌ ዘመናት ነጉደዋል፡፡ ግብፅ ኢትዮጵያን ያለኃጥያቷ በጠላትነት ዓይን ትከታተላት ብቻ አልነበረም፡፡ ከኢትዮጵያ በምታገኘው ውሃ ከተሞላው ናስር ሐይቋ ወደ ሰማየ ሰማያት በምትለቀው የመሰርይነትና የበቀል ትነት በኢትዮጵያ አድማስ ላይ ያጠላውን ጥቁር ደመና በመበከል በኢትዮጵያ ምድር ላይ አሲድ እያዘነበች ህዝቦቿን ስታነፍራቸው፣ ቡቃያዎቿን አቀጭጫ ስታጠፋቸው፣ ወንዞቿንና ሐይቆቿን ወደ መርዝ ፈሳሽነት ስትቀይራቸው ከተፈጠረች ጀምሮ እስካሁን ድረስ አለች፡፡ አባይን ከነምንጩ በቁጥጥር ስር በማዋል በምስራቅ አፍሪካ ብቸኛዋ ኃያል አገር ለመሆን ካላት ቅዠት የተነሳ በተደጋጋሚ ኢትዮጵያን ወርራለች፡፡ ነገር ግን ክብር ለቀደሙት ጀግኖች አባቶቻችን ይሁንና ህልሟ እንደ ጉም በንኖ ቀርቷል፡፡
አፄ ዮሃንስ ግብፅ የምትፈፅመው ማባሪያ የሌለው ግፍና በደል ሲያንገፈግፋቸው ለእንግሊዝ ንግስት ለንግስት ቪክቶሪያ በፃፉት ምሬትን ያዘለ ደብዳቤ ውስጥ “…በአገሬ ምድር ሰላምን አምጥቼ ከህዝቤ ጋር ወደ ልማት ልዞር ባሰብኩበት ወቅት መሃመድ ባሻ ሳልደርስበት ጠብ እየጫረ አላስቀምጠኝ ብሏል፤ እኔ ጦርነት መግጠም አልፈለግም እባክዎን ንግስት ሆይ ተው ይበሉልኝ…” የሚል ሀሳብ ይገኝበታል፡፡
ከመሃመድ ፓሻ እስከ ከዲቭ ኢስማኤል ፓሻ፣ ከጀማል አብደልናስር እስከ አንዋር ሳዳት፣ ከሙባረክ እስከ አሁኑ ሙርሲ የሚገኙት የግብፅ መሪዎች በጠቅላላ ኢትዮጵያን አንድም ቀን ተኝተውላት አያውቁም፡፡ ጉልበቷን ቄጠማ አድርገው በማሽመድመድ እንዲህ አቅም እንዳጠራት ቀጭጫ እንድትቀር አድርገዋታል፡፡ ከገዛ ምድሯ የሚመነጨውን የአባይ ውሃ “በእፍኝሽ እንኳን ጨልፈሽ ብትጎነጭ እናጠፋሻለን” እያሉ ሲያስፈራሯት ኖረዋል፡፡
ግብፅ ዋነኛዋ የኢትዮጵያ የውስጥ ሰላም እባጭ ህመም ነቀርሳ ናት፡፡ ለዚህ ማስረጃ ወደ ኋላ ተጉዞ ዘመናትን መሻገር አያስፈልግም፤ ወያኔና ሻዕብያ በእሷ የጦር መሳሪያ እየታጠቁ የገዛ አገራቸውን ሲወጉ እንደነበር ብቻ መጥቀሱ በቂ ነው፡፡ በዚህ ኢትዮጵያ ከእርስበርስ ጦርነት ተላቅቃ የሰላም አየር እንዳትተነፍስና ፊቷን ወደ ልማት እንዳታዞር በማድረጉ ሴራ ሱዳንም አለችበት፡፡ በደርግ ጊዜ ህወሓት ካርቱም ውስጥ ጽህፈት ቤት ነበረው፡፡ ዋና መግቢያና መውጫ በሩም ሱዳን ነበረች፡፡ ጀብሃን ያደራጀችው ግብፅ ናት፡፡
ግብፅም ሆነች ሱዳን በየጊዜው የኢትዮጵያን ጨቋኝ የአገዛዝ ስርዓት የሚቃወሙትን ቡድኖች የሚያስታጥቁት የኢትዮጵያን ህዝብ ነፃ ለማውጣት አይደለም አገሪቱን በጦርነት ለማዳከምና የኢኮኖሚ አቅም ለማሳጣት እንጂ፡፡ ምክንያቱም ኢትዮጵያ ከጦርነት ወጥታ እፎይ የምትልበት እድል ካገኘች በማንኛውም ጊዜ አባይን ገድባ ለልማት እንደምታውለው ጠንቅቀው ያውቃሉና፡፡
በእንድ አገር ላይ የተንሰራፋን አፋኝ ስርዓት ለማስወገድ ከሌላ አገር መንግስት እርዳታ መለመን በየትኛውም አለም ካሁን በፊት የነበረና ወደፊትም የሚኖር ነው፤ ለዚያች የአፈና አገዛዝ ለነገሰባት አገር ጠላቶች በመሳሪያነት ማገልገል ግን አገርንና ወገንን መካድ ነው፡፡ ግብፅ ደደቢት በረሃ ክሳድ ግመል ለሸፈተው አስገንጣይ ወንበዴ ህወሓት የደርግን ስርዓት እንዲፋለም ላዩ በማር የተቀባ የሬት ስንቅ ስታቀብለው ኖረች፡፡ ወያኔ ማሩን እየላሰ ኃይልና ሙቀት አግኝቶ ለ17 ዓመታት በመዋጋት አሸንፎ ኢትዮጵያን መልሶ በጠመንጃ አፍኖ ለ22 ዓመታት ለመግዛት በቃ፡፡ ይኸውና አሁን ደደቢት በረሃ ውስጥ እያለ ጀምሮ ይልሰው የነበረው ማሩ አልቆበት ሬቱ ብቻ ቀርቶት እሱን እየላሰ ይጎመዝዘው ይዟል፡፡
ወያኔ የደቂቃ የደስታ እሸትን ከሴት ብልት ማሳ ላይ ለመቅጠፍ ብሎ ከኤች.አይ.ቪ ህመምተኛ ጋር ልቅ የሆነ ግብረ ስጋ በመፈፀም የዓመታት ህይወቱን እንደሚቀጥፍ ስሜቱን ፈፅሞ መግራት የማይቻለው ቅንዝራም ጎረምሳ አይነት ነው፡፡ ዛሬ አንድ ተግባር ሲፈፅም ነገ ሊያስከትል የሚችለው ውጤት ምን ሊሆን እንደሚችል አያጤንም፡፡ ሳህል በረሃ ውስጥ የመሸገው የሻዕብያ ገንጣይ ወንበዴ ቡድን በአብዮታዊ ህዝባዊ ሰራዊት አከርካሪው ተሰብሮ እስከመጨረሻው ለመክሰም ሲቃረብ በአፉና ባፍንጫው ኦክስጂን ሰጥቶ የመጀመሪያ እርዳታ በማድረግ እስትንፋስ የሆነው ወያኔ ነው፡፡ ከዚያም አውራው መለስ ዜናዊ አገሬን ገንጥሉልኝ ብሎ ለተባበሩት መንግስታት በፃፈው ደብዳቤ ኤርትራ ከኢትዮጵያ ተቆርሳ ራሷን የቻለች በሻዕብያ የምትገዛ አገር ሆነች፡፡ በኋላ ሻዕብያ ለራሱ ለወያኔ የቂጥ እከክ ሆነበት፡፡ በእርግጥ ምንጊዜም ቢሆን የችግሩ ገፈት ቀማሽ የኢትዮጵያ ህዝብ ነው፡፡ በጦርነቱ በድህነት ቤቱ ያሳደጋቸውን መቶ ሺህ ልጆቹን በከንቱ የገበረው እሱ እንጂ ወያኔ ኢህአዴግ ምንም የጎደለበት ነገር የለም፡፡ በጦርነቱ ጊዜ ሰራዊቱ ኤርትራን እስከ ቀይ ባህር የመቆጣጠር ፍላጎት ነበረው፡፡ በመረብ በኩል ለፍልሚያ የተሰለፈው ሰራዊት ተሰኔ ገብቶ ከአስመራ የሚያገናኘውን አውራ ጎዳና ይዞ በታላቅ ወኔና ጉጉት ወደ ፊት መገሰገስ ሲጀምር ቁምና ቀኝ ኋላ ዙር ተባለ፡፡ በቡሬ ግንባር በኩል የተሰማራው ጦርም አንዲሁ የአሰብን መብራት አሻግሮ እያየ ያለፍላጎቱ ተመለሰ፡፡ ይህ ሁሉ የሆነው እንግዲህ ከኢትዮጵያ ይልቅ ለኤርትራ በሚቆረቆረውና “ባለራዕይ” በሚባለው መለስ ዜናዊ ብቻ ቀጭን ትዕዛዝ ነው፡፡ ይኸውና ዛሬ ኤርትራ ግብፅ ኢትዮጵያን ለማጥቃት የምትጠቀምባት ስትራቴጂክ ቦታ እንደሆነች በሰፊው እየተነገረ ነው፡፡ የመለስ ወንድም ኢሳያስ ደግሞ ይህን ከማድረግ ወደ ኋላ የሚል አይመስልም፡፡ ሻዕብያ አሰብና ምጽዋን ሲይዝ አንድ የኢትዮጵያ ጦር ጄነራል “ከእንግዲህ ወዲህ አገሬ ኢትዮጵያ የሬሳ ሳጥን ሆነች” ብሎ ነበር፡፡ ጀነራሉ ልክ ነበር እናት ኢትዮጵያ ባሁኑ ጊዜ ከሬሳ ሳጥን ውስጥ ገብታ የተጋደመች አሳዛኝ አገር ናት፡፡ የሬሳ ሳጥን በርና መስኮት የለውም፡፡ ይህን ያደረገው ደግሞ ወያኔ ነው፡፡
እናም ይሄ ለጠላት አገር በመሳሪያነት የማገልገሉ ጉዳይ መቼ ነው የሚቆመው? የግብፅ መሪዎች እኮ ኢትዮጵያን በማተራመስ የግድቡን ስራ እናስተጓጉለዋለን እያሉ ባደባባይ የሚናገሩት የኢትዮጵያን ጠመንጃ ያነሱ ተቃዋሚ ቡድኖች ላዩ ማር የተቀባ ሬት የመቀበልን የቆየ ባህል ከህወሓት ስለሚያውቁት ነው፡፡ ከንጉሱ ስርዓት ጋር የተኳረፉ መኳንቶችና ግለሰቦች ከጣልያን ጋር አብረው ወገናቸው የሆነውን የኢትዮጵያን አርበኛ አንደወጉት፤ ከደርግ ጋር የተጣሉት ኢህአፓዎችና ሻዕብያዎች ከሶማሊያ ጎን ተሰልፈው የእናታቸውን ልጅ እንደገደሉት፤ ዛሬም ቢሆን የግብፅን ላዩ ማር የተቀባ ሬት ተመፅውተው እየላሱ በመሳሪያነት ሊያገለግሉ የሚችሉ ከወያኔ ኢህአዴግ ጋር ተኳርፈው ጫካ የገቡ ቡድኖች ሊኖሩ አይችሉም ብሎ ለመደምደም ያዳግታል፡፡
ግብፅ ኢትዮጵያን ነፃ እናወጣለን በማለት ጠመንጃ ታጥቀው ጫካ ለገቡ “ነፃነትን የማያውቁ ነፃ አውጪዎች” ላዩ ማር የተቀባ ሬት ስንቅ ከማቀበሏ በተጓዳኝ የየብስ የባህርና የአየር ተዋጊ ሠራዊቷን በሚገባ ስትገነባ፣ ጡንቻውን ስታፈረጥም፣ በትጥቅ ስታዘምንና ስታገዝፍ ነው የኖረችው፡፡ የኢትዮጵያ ገዥዎች ግን በተቃራኒው ትራሳቸውን ከፍ አድርገው ተኝተው ነበር፡፡ በተለይ ወያኔ ኢህአዴግ ከንጉሱ ዘመን ጀምሮ ስንትና ስንት አንጡራ ሀብት ፈሶበት የተገነባውን የኢትዮጵያ ሠራዊት የደርግ ኢሠፓ በማለት በትኖ የአገሪቱን ወታደራዊ መሰረት በማፈራረስ ያለአለኝታ እርቃኗን አስቀራት፡፡ የአገሪቱን በጠላት ቀለበት ውስጥ የመገኘት ጉዳይ ወደ ጎን በመተው የራሱን ስልጣን ብቻ ለማራዘም ሲል ራሱ ያደራጀውን ሰራዊትም የትግርኛ ቋንቋ የማይናገሩትን በመመንጠር ባብዛኛው የአንድ ብሄር ጦር ብቻ አድርጎታል፡፡
ወያኔ ኢህአዴግ የኢትዮጵያን ህዝብ ረግጦ በጠመንጃ የሚገዛበትን ወታደር /አንደ አግአዚ ኮማንዶና ፌደራል ፖሊስ ዓይነት/ በደንብ ሲገነባና በትጥቅ ሲያደራጅ የአገሪቱን የውጭ ጠላቶች ችላ ብሏቸው ቆይቷል፡፡ ኢትዮጵያ ዙሪያዋን በጠላት የታጠረች አገር መሆኗን ግጥም አድርጎ እያወቀ 22 ዓመታትን በስልጣን ሲያሳልፍ በወታደራዊ ሳይንስ መስኩ አንድ እርምጃ እንኳን አልተራመደም፡፡ አንዴውም የአገሪቱ መከላከያ ተቋም በንግድ ስራ ላይ ተሰማርቶ ይገኛል፡፡
በተጨማሪም ወያኔ ኢህአዴግ የተራቀቀ ወታደራዊ የእድገት ደረጃ እንደደረሰ ሁሉ የአገሪቱ የመከላከያ ኃይል ገና እንጭጭና የግብፅን የመጠቀ የጦር ቴክኖሎጂ የታጠቀ የየብስ፣ የባህርና የአየር ተዋጊ ሠራዊት ሙሉ በሙሉ መመከት የማይችል ሆኖ እያለ ርካሽ የፖለቲካ ትርፍ ማግበስበሻ ፕሮፓጋንዳ በሰፊው እያናፈሰ ይገኛል፡፡ “አባይን ልገድብ ነው” ጩኸት፤ “የህዳሴ ግድብ የመሰረት ድንጋይ ጣልኩ” ሌላ ጩኸት፤ “ አጨብጫቢዎቹ ሰልፍ ወጥተው በጩኸት ላይ ጩኸት፤ “ቦንድ ግዙ” ተጨማሪ ጩኸት፤ የህዳሴው ግድብ ልደት ክብረ በዓል ጩኸት፤ “አባይን ተፈጥሯዊ የመፍሰሻ አቅጣጫውን አስቀየርነው” ጩኸት… የማያባራ ጩኸት፡፡ በቃ አገሪቱን የጫጫታ ምድር አደረጋት፡፡ ግብፅ እኮ አስዋንና ናስርን ስትገድብ በዝምታ ነው የልቧን የፈፀመችው፡፡ የወያኔ ኢህአዴግን ጫጫታ ምንአመጣው? የሚጮህ ውሻ እኮ አይናከስም፡፡ ደግሞም ወጡ ሳይወጠወጥ ወስከምቢያው ምንአለ ነው የሚባለው፡፡ ባለፈው ጊዜ የተከበረው የመከላከያ ሰራዊት ቀንም ከባዶ የጉራ ፕሮፓጋንዳ ተለይቶ አይታይም፡፡ ሲሉ ሰምታ ዶሮ ሞተች ከጭስ ገብታ፡፡ ወያኔ ኢህአዴግ እንደለመደው ቆስቁሶ ሊያነደው የፈለገው የጦርት እሳት ያለ ይመስላል፡፡
ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም “ኢትዮጵያ ከየት ወደየት” በሚል ርዕስ በ1986 ዓ.ም በጻፉት መጽሓፍ ውስጥ “የኢትዮጵያ ታሪክ የጦርነት ታሪክ ነው…” የሚል ጠንከር ያለሀሳብ ሰፍሮ ይገኛል፡፡ እውነትም የጦርነትን ገፈት ያልጨለጡ የኢትዮጵያ ትውልዶች ከቶ ሊገኙ አይችሉም፡፡ ስለሆነም ኢትዮጵያ ከእንግዲህ ወዲህ በምንም መልኩ ከጦርነት እሳት ውስጥ ገብታ መንደድ የለባትም፡፡ የሰላም አንጂ የጦርነት አሸናፊ የለውም፡፡
ዓለም ከአንደኛው እጅግ ዘግናኝ የሆነና ምንም መፍትሄ ያላመጣ የዓለም ጦርነት ምንም ሳትማር ወደ ሁለተኛው የዓለም ጦርነት ሰተት ብላ ገባች፡፡ በጀርመኑ የናዚ ሰራዊትና በሶቭዬቱ ቀይ ጦር መካከል በተደረገ ከባድ ፍልሚያ ስታሊን ግራድ ነደደች፤ ለንደንና በርሊን በቦምብ ተቀጠቀጡ፤ ፓሪስ በሞርታር ታረሰች፤ ፒርል ሀርቦር በሚግ ተወገረች፤ ሂሮሽማና እና ናጋሳኪ በ“little boy” እና “fat man” አተሚክ ቦምቦች ተመትተው እንደ ሰም በመቅለጥ ከምድረ ገፅ ጠፉ… በቃ ምድር በጠቅላላ ተናጠች፤ በሰው ልጆች በድን ተሞላች፤ ሚሊዮኖች አለቁ፤ የመጨረሻ ድምር ውጤቱ ግን ዜሮ ነበር፡፡ በዓለም ታሪክ ከጦርነት ያተረፈ ማንም አገርና ህዝብ የለም፡፡ ሰላም ለማምጣት በጎተራ የሞላ ትዕግስት ሰንቆ መንቀሳቀስ ያስፈልጋል፡፡ ከጦርነት ይልቅ ለኢትዮጵያም ሆነ ለግብፅ ህዝብ የሚበጀው ይህና ይህ ብቻ ስለሆነ፡፡ በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት እኮ ያሁሉ ወጣት ከረገፈ በኋላ መሪዎች በቀጥታ ለሰላም ድርድር ወደ አልጀርስ ነው የሄዱት፡፡ ምናለበት ያ የሰላም ድርድር ከጦርነቱ በፊት በሆነ ኖሮ መቶ ሺህ የድሃ ልጆቸ ባልሞቱ ነበር፡፡
የግብፅ መሪዎች ማንገራገር ዛሬ የተጀመረ አዲስ አይደለም፤ የተለመደና ለሺህዎች ዓመታት የዘለቀ ነው፡፡ ማንገራገርን እንደ “psychological warfare” እየተጠቀሙበት ነው፡፡ ነገር ግን ኢትዮጵያ ልክ እንደወትሮው መዘናጋት የለባትም፡፡ ወያኔ ኢህአዴግም ምንም አንኳን ቢረፍድበትም ከእንቅልፉ መንቃት አለበት፡፡
Egypt is a gift of Nile” የሚለውን የሄሮደተስ አባባል “Nile is only a gift of Egypt” በማለት ገልብጠው የተረዱት የሚመስሉት የልበ ደንዳናው ፈርኦን ሽንቶች ከማንገራገር አልፈው እንደለመዱት ከመጡብን ግን ምን እናደርጋለን አንደ ቀደሙት ጀግኖች አባቶቻችን ደማችንን ገብረን የዚህችን ያልታደለች ድሃ ምድር ዳር ድንበር ከማስከበር ውጪ ሌላ ምን አማራጭ አለን፡፡ አንድ የግብፅ ገበሬ ከአረንጓዴ ማሳው መሃል በኩራት ቆሞ “የውሃችንን ምንጭ ለማቆም የሚሞክር ማንም አካል ቢኖር ያለምንም ድርድር በቀጥታ እንፋለመዋለን” በማለት እየተናገረ “Struggle over the Nile” በሚል ርዕስ በተሰራ ዶክሜንታሪ በአልጀዚራ ቴሌቪዥን ታይቷል፡፡
ምናልባት ኤርትራ የግብፅ ተባባሪ ከሆነች ከሻዕብያ ጋርም በድጋሚ ጦርነት መግጠማችን የማይቀር ጉዳይ ነው፡፡ ይህ ከሆነ ወያኔ ኢህአዴግ የተገኘውን አጋጣሚ ተጠቅሞ አስመራ ድረስ በመግባት ሻዕቢያን እስከመጨረሻው ደምስሶ ድንበራችንን መልሶ ቀይ ባህር በማድረግና ወደባችንን በማስመለስ አገሪቱን ከሬሳ ሳጥን ውስጥ አውጥቶ የተበላሸውን ታሪኩን ያድሳል እንጂ ለሁለተኛ ጊዜ አይሸወድም የሚል የበርካቶች እምነት አለ፡፡
ደግነቱ ዘውዱ

የምእራብ ጎንደር ወይና ደጋው ክፍል በር የሌላቸው የወያኔ እስርቤቶች ስለመሆናቸው፤


ከመካከለኛው ምስራቅ የሚነሱ ጠላቶች ሁልጊዜም ኢትዮጵያን ሲአጠቁ መረማመጃ ያደረጉት ዋና ከከሰላ እስከ ኦሜድላ (ጎጃም) ያለው አካባቢ ነበር። የነዚህ ተጋፊ የኢትዮጵያ ጠላቶችን የመጀመሪያ ገፈታ ቀማሽ የምእራብ ጎንደር ህዝብ ነበር። ለአጼ ተዌድሮስ መነሳት ለአጼ ዮሃንስም መሰዋእትነት ምክንያት የሆኑት በዚሁ አካባቢ የኢትዮጵያን ልእልና ለመድፈር የተደረጉ ሙከራዎችና ጦርነቶች ናቸው። የምእራብ ጎንደር ህዝብም ድንበሩን ለመከላከል ሲል ያልተቋረጠ መስዋእትነትን ከፍልበታል።
በአስራ አምስተኛዉ ምዕተ አመት (ከግራኝ መሃመድ ወረራ) ጀምሮ የአርማጭሆ፣ የወልቃይት፣ የጠገደ፣ የጫቆና የቋራ ህዝብ ‘ድንበር ጠባቂ’ ተብሎ ስያሜ ተሰጥቶት በማህል ኢትዮጵያ በሚነሳ ጦርነት እንዲይሳተፍ በአዋጅ የተከለከለ ነበር። በዚህም ምክንያት የወልቃይት፣ ጠገደ፣ የአርማጭሆ፣ የጭልጋና የቋራ ህዝብ ቤተሰቡን ያሰፈረው ከጠላት ለመመከት የተሻለ ከሆነው ከወይና ደጋው ነው። የምእራብ ጎንደር ወይና ደጋዎች፤ አዲረመጥ የተባለውን የወልቃይት ከተማና አካባቢውን፣ ቀራቅር የተባለውን የጠገደ ከተማና አካባቢውን፣ የአርማጭሆ የጭልጋና የቋራ ወይና ደጋ መሬቶችን ያጠቃልላል። ይሁንና የወይና ደጋው አፈር በውሀ የተሸረሸረ፣ መሬቱም በህዝብ ሰፈራ የተሰላቸና የተጣበበ በመሆኑ በቆሎና ድንች ከመሰለ አነስተኛ ምርቶች በስተቀር የወይና ደጋው ህዝብ የሚተዳደረው በቆላው መሬት በሚያመርተው ምርትና ከብት እርባታ ነው። ለአለፉት ሁለት መቶ አመታት ደግሞ የወይና ደጋው ህዝብ እርሻውንና ከብት ርቢውን በመከተል በቆላዎች ሰፈራዎችን አስፋፍቶ፤ በወልቃይት መዘጋ (አዲጎሹ፣መጉእ፣ቃሌማ፣እጣኖ፣ማይሃርገጽ)፣ የሁመራ፣ የዳንሻ፣ የአብደራፊ፣ የመተማና በቋራ እንደ ዮሀንስ የመሳሰለትን ከተሞችን ቆረቆረ። ይህ ደግሞ የድንበር
ጥበቃውን በይበልጥ አጠናከረው። በዚህም ምክንያት ነበር ጣሊያን በወልቃይት፣ በጠገደ፣ በአርማጭሆና በመተማ አካባቢ ከፍተኛ ሽንፈት የደረሰበትና አካባቢውም ከየትም ለመጣ የኢትዮጵያ አርበኛ ቡድን ከፍተኛ ምሽግ ሆኖ የቆየው። የወያኔ መሪዎች ግን ገና ሀ ብለው እንቅስቃሴ ሲጀምሩ ዋና ተልእኮ አድርገው የያዙት የዚህን ዳር ድንበር ጠባቂ ህዝብ የጀርባ አጥንት መስበር ነው።ይህንንም ህዝብ ነው ትግሬ ባለመሆኑና በተለይም አማራ በመሆኑ ከምድር ገጽ ለማጥፋት በወያኔ እቅድ የወጣለት።
ዛሬ የወልቃይት፣ የጠገደ፣ የአርማጭሆ፣ ጫቆና ቋራ ህዝብ አማራ በመሆኑ ብቻ ለዘመናት ከሞተለት መሬት ተፈናቅሎ በተጨናነቁ በምእራብ ጎንደር ወይና ደጋዎች ታጉሯል። የተጣበበው ህዝብ እንደ አባቶቹ ወደ ቆላ መሬቶቹ ወርዶ ከብት አርብቶና አርሶ እንዳይበላ የትግራይ ክልል አስተዳደር እስክ አፍንጫቸው ባስታጠቋቸው የትግራይ ሰዎች ይጠበቃሉ፤ ይህ አልበቃ ብሎ ደግሞ በወይና ደጋዎቹ ላይ በማንአለብኝነት የተደራጁት የወያኔ አስተዳዳሪዎች በሰበብ አስባቡ (መሳሪያ አሽገሀል ወዘተ) በማለት ሁለንም ቤተሰብ ያንገላቱታል፣ያስሩታል። በተለይ ወጣት ወንዶች ከፍተኛ ያፈና በደልም ይፈጸምባቸዋል።
በዘላቂ መንገድም የወይና ደጋው ህዝብ የሽንፈትና የወኔ መፍሰስ ስሜት እንዲያድርበት ወያኔ ከህዝቡ አብራክ የወጡትን ልጃገረዶችን በትግራይ ጎረምሳ ኮርማዎች ግብረ ስጋዊ አመጽ ያስፈጽምባቸዋል። ይህ በተለይ በወልቃይትና ጠገደ ወይና ደጋዎች በሰፊው የሚካሄድ ወንጀል ነው።
በአጠቃላይ ዛሬ የምእራብ ጎንደር ወይና ደጋዎች በር የማያስፈልጋቸው የወያኔ እስር ቤቶች ሆነዋል።
የመተማ ከተማና አካባቢው፤
ወያኔ በመተማ ከተማና በአካባቢው ያሉትን ገበሬዎችና የከተማው ነዋሪ ህዝብ ሰብስቦ ‚…አካባቢው ለጦር ክምችትና ለጦር ማእከላዊነት እንድሆን ስለተወሰነ ወደ ምስራቅ ባለው የወይና ደጋው ጥግ ለመስፈር ዝግጅት እንድታደርጉ…‛ የሚል ትዕዛዝ ተሰጣቸዉ። በ2009 (እ።አ።አ) ነብስ ገቢያ በሚባለው የቋራ ቆላ ክፍል የሱዳን ወታደር አርሻ አቃጥሎ፣ ንብረት ዘርፎና ወገኖቻችንን ማርኮ ወደ ሱዳን ሲወስድ መተማ የተከማቸው የወያኔ ወታደር አንድት ጥይት እንኳን አለመተኮሱን የኢትዮጵያ የድንበር ኮሚቴ በማያወላዳ ማስረጃ መመዝገቡ የሚታወስ ነው። ስለዚህም መተማ የተከማቸው የወያኔ ወታደር ዋና ተግባሩ የኢትዮጵያኖችን ድህንነት ለማስጠበቅ እንዳልሆነ ግልጽ ነው። ወታደሩ እስካሁን ድረስ ያሳየው ታሪክ ቢኖርም የአማራውን ገበሬ ማፈናቀል፤ ማሰር፣ መግደልና ሃብት ማቃጠል ነው። ወደፊትም ከዚህ
የተለየ አይጠበቅበትም። ይልቅስ በመተማ አቅጣጫ ያገረሸው የወያኔ መልቲ ዘመቻ ግልጽ ያደረገው ነገር፤
፩ .የትግራይ መስፋፋት በአብደራፊና በአካባቢው እንደማይቆም፤
፪. የትግራይን ግዛት ከጣና ባህርና ከተቻለም ባሁኑ ወቅት አባይን እገድባለሁ እያለ ከበሮ ከሚደልቅበት ቦታ ለማድረስ ለሚደረገው የመጨረሻው ዘመቻ የመጀመሪያው መስተንግዶ (አፒታይዘር) መሆኑ ነው።
አደፍርስ ደመላሽ

Friday, June 14, 2013

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋን እኔ እንደማውቀው

ስመኝ ከፒያሣ የኢትዮጵያ ፕሬስ የሚታወሰው ወይም የሚነሳበት ዘመን ቢኖር ከ1985 ዓ.ም ጀምሮ ነው፡፡ ኢህአዴግ መላ ሀገሪቱን ከተቆጣጠረበት ከግንቦት 20/1983 ዓ.ም እስከ 1985 ዓ.ም ድረስ ምንም ያደረገው ነገር አልነበረም፡፡ ፀጥታ የነገሰበት ጊዜ ነበር፡፡ በዚህ ጊዜ ውስጥ ደግሞ ማለትም 1985 ዓ.ም ላይ የኤርትራ ሪፈረንደም የተፈቀደበት ጊዜ ነበር፡፡ ከዛ በኋላ ደግሞ በሙሉ ነፃነት ነገሮችን መግለፅ ተጀመረ፡፡ታዲያ በነዚህ ጊዜያት ከወጡትና ስለኢትዮጵያ የፕሬስ ነፃነት አለን ብለው መፃፍ ከጀመሩት መካከል ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ አንዱ ነው፡፡ እስክንድር ነጋ በምድረ አሜሪካ ይኖር የነበረ ሲሆን ወደ ኢትዮጵያ የተመለሰው ከደርግ ውድቀት በኋላ ነው፡፡ በቤተሰቦቹ ላይም ሆነ በእሱ ላይ ከፍተኛ እንግልት፣ ስቃይና በርካታ የንብረት ውድመት በደርግ መንግስት ደርሶባቸዋል፡፡ እሱና እናቱ በቀይ ሽብር ወቅት ከፍተኛ ጭፍጨፋ ፈፅመዋል ከሚባሉት አንዱ በሆነው ” ግርማ ከበደ” ከፍተኛ እንግልትና የንብረት ውድመት ሲያደርስባቸው ወደ አሜሪካ ተሰደዱ፡፡  እስክንድር በአሜሪካ በነበረበት ወቅት ደርግ ይፈፅማቸው ለነበሩ ያልተገቡ ተግባራት በሙሉ በአሜሪካ ይገኙ የነበሩ ኢትዮጵያዊያን በደርግ መንግስት ላይ ጫና ይደረግ የሚል መርህ ባነገቡ ሰላማዊ ሰልፎች ላይ ቀርተው አያውቁም፡፡ ሁሌም ስለሀገሩ ያስብም ነበር፡፡ የእስክንድር ፍላጐት ሀብት ንብረትና ገንዘብ ሣይሆን የኢትዮጵያ እድገትና ለውጥ ማየት ነው፡፡ ኢትዮጵያ ከሌላው ሀገር በተሻለ ለውጥ ማምጣት የምትችል ሀገር በመሆኗ ይህ ለምን መሆን አልቻለም ብሎ የሚናገር ጋዜጠኛም ነበር፡፡ ወደ ኢትዮጵያ ከመጣም በኋላ “ኢትዮጲስ” የተባለ ጋዜጣን ከሟች ጋዜጠኛ ተፈራ አስማረ ጋር በመሆን አቋቋመ፡፡ በወቅቱ በኢትዮጵያ ኢህአዴግ ዴሞክራሲን አስፍኛለሁ ያለበት ጊዜ ነበር፡፡ ዴሞክራሲ ያለገደብም ተብሎ ነበር፡፡ ከዚህ በመነሣት በርካታ ዜናዎች ማቅረብ ጀመሩ፡፡ በወቅቱ እነሱ የጀመሩት ጋዜጣ ዋጋ 75 ሳንቲም ቢሆንም ይዘውት የሚወጡት ዘገባ ከባድነት “ኢትዮጲስ” ጋዜጣ ሰባት ብር ድረስ ትሸጥ ነበር፡፡ የዛሬ 20 አመት ሰባት ብር የነበረውን ጥቅም ማንም ቢሆን የሚዘነጋው አይደለም፡፡ ታዲያ በዚህ ሁኔታ ላይ እያለ ኢትዮጲስ ተቋረጠች፡፡ እነ እስክንድርም ታስረው ወጡ፡፡ ከዛ “ሀበሻ” የተባለ ጋዜጣ በአማርኛና በእንግሊዘኛ ማሣተም ጀመረ፡፡ ይሁንና ግን ብዙም ሣይራመድ “ጐበዝ አምስት አመት ሞላ” የሚለው ዘገባ ችግር ፈጠረ፡፡ እስክንድር መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ያነበው ዘንድ ሀበሻን ይጠብቋት ብሎ የጋዜጣውን ማስታወቂያ በካርቶን ይዘው የሚዞሮ ወጣቶችን መድቦ ነበር፡፡ ይሁንና እስከ እነሱ ጭምር በድጋሚ ታሰረ፡፡ ወጣቶቹ ሲፈቱ እስክንድር ግን በማረሚያ ቤት ቀረ፡፡ የእስክንድር ቀኝ እጅ የተሰበረውም በዛ ጊዜ ነበር፡፡ እስክንድር ከተፈታ በኋላም ዳግም ታስሯል፡፡ እንደውም በ1987 አብሯቸው ከታሰራቸው መካከል የግብፁን ፕሬዝዳንት ሁሴኒ ሙባረክን ለመግደል ሙከራ ያደረጉና በቁጥጥር ስር ከዋሉ አሸባሪዎች ጋር ነበር፡፡ እዚህ ላይ የምገልፀው ነገር ቢኖሩ እስክንድር ነጋን እኔ እንደማውቀው ነው፡፡ ከዛ በኋላ ወይም ከረጅም ጊዜ እስር በኋላ ግን ተፈቶ እስክንድር ነጋ ወደ ጋዜጣ ሕትመት ሲመለስ “ምኒልክ” የተባለውን ጋዜጣ ይዞ ብቅ አለ፡፡ ምኒልክ ጋዜጣ መቼም በሀገሪቱ እስከተቋረጠበት ጊዜ ድረስ በህትመት ግንባር ቀደም የነበረ ጋዜጣ ነበር፡፡ እስክንድር ነጋ የተለየ ነገር ወይም ባህሪ አለው፡፡ ይህ ባህሪው ደግሞ ስለገንዘብና ጥቅም የሚያስብ ሰው አልነበረም፡፡ በወቅቱ ጋዜጦች በኪሳራ ከጨዋታ ሊወጡ ሲሉ የሚደጉም የለኝም ብሎ ለመጣ ሁሉ የሚሰጥ ሰው ነበር፡፡ እኔ እስክንድርን ከተዋወኩበት ጊዜ ጀምሮ ሁሌም እሱን ማወቅ ያጓጓኛል፡፡ ምክንያቱም ከእሱ የሚወጡት ሀሣቦችና ቃላት የተለዩና በውስጣቸው እውነትነት ያላቸው ነበሩና፡፡ እስክንድር ስለገንዘብ ጥቅም ወይም ተንደላቆ ስለመኖር የሚያስብ ሰው ፈፅሞ አይደለም፡፡ የየትኛውንም ሰው ሀሣብ ይቀበላል በፅሞናም ያዳምጣል፡፡ የትልቅነት መለኪያው ደግሞ ምንም ሣይሆን ሰዎችን ማዳመጥና መስማት መቻል ነው፡፡ እስክንድር በጋዜጦቹ ላይ በርካታ ነገር ይፅፋል፡፡ አንድም ጊዜ ቢሆን ግን ምስሉን ለጥፎ እኔ እስክንድር ነጋ ነኝ ብሎ አያውቅም፡፡ ከዛ ባለፈ ደግሞ “ሀበሻ” ጋዜጣ ከታገደበት በኋላ በስሙ ያወጣው ጋዜጣ የለም፡፡ ፎቶውን ሣይሆን ስሙን አውጥቶ የፃፋቸው ፅሁፎች ቢኖር የማስታውሰው የደርግ ባለስልጣናትን በሚመለከት በሚወጡ ፅሁፎች ላይ ነበር፡፡ ከዛ ውጭ ግን በሰራው ስራ በሕዝብ እንዲወደዱ እወቁኝ እወቁኝ እያለ በአደባባይ የወጣ ወይም ደረቱን ነፍቶ ይህ ይሁን ያለ ሰው አይደለም፡፡ እስክንድር የተለየ ቦታ ያለው ሰው ነው፡፡ አንድ ታሪክ ልንገራችሁ ይህን ታሪክ ግን ስም ሣልጠቅስ ባወራው እመርጣለሁ፡፡እስክንድር አሁንም በስራ ላይ ላለ ጋዜጣ ባለቤት እባክህ እከሌ የተባለን ባለሰልጣን ለማነጋገር ፈልጌ ሪፖርተሬን መላክ ፈለኩ እናም አስጨርስልኝ አለው፡፡ ይህ ሰውም ባለስልጣኑን ሲያናግር ባለስልጣኑ ሪፖርተሩ ሣይሆን ራሱ እስክንድር ነጋከመጣ ቃለመጠይቁን እሰጠዋለሁ አሉ፡፡ በዚህ ምክንያት እስከንድር ሣይሄድ ቀረ፡፡ እኚህ ባለስልጣን ታዲያ አሉ ወይም ተናገሩ በተባለው ቃል “እስክንድር የገንዘብ ችግር እንደሌለበት አውቃለሁ የሚሰራው ለጥቅም ወይም ለፖለቲካ ፓርቲ አይደለም፡፡ አላማው ምን እንደሆነ እሱን አግኝቼ ማናገር እፈልጋለሁ” ሲሉ ገለፁ፡፡ የእስክንድርን መንፈስ ስናስበው ታዲያ በዚህች ሀገር ላይ እውነተኛው ዴሞክራሲ መስፈን አለበት ከሚል አንፃር በመነጨ የሚሰራ እንጂ አትራፊ ጋዜጠኛ ወይም የሕዝቡ የልብ ትርታ ይሄ ነው ብሎ ምስሉን ለጥፎ የሚነግድ አይደለም፡፡ ርግጠኛ ሆኜ የምነግራችሁ በሀገሪቱ ከታተሙ ነፃ ጋዜጦች እስክንድር ነጋ የሚሰራባቸውን ጋዜጦችን በቁጥርና በጥራት የሚደርስ አልነበረም፡፡ይህ ሁሉ ሲሆን ታዲያ እስከንድር ሻይ እንጠጣ ብሎ ኪሱ ሲገባ ገንዘብ ሣይዝ ረስቶ የሚወጣ ሰው ነው፡፡ ስለገንዘብና ስለዝና አይኖርም፡፡ በእሱ ስር የሚሰሩ ሰራተኞች ግን የበለጠ እንዲጠቀሙ ያደርጋል፡፡ እስክንድር ተቸገርኩ ላለው ሰው ሆዱ የማይጨክንና የሚራራ ደግ የሚባል ጋዜጠኛም ጭምር ነው፡፡ የእስክንድር ጋዜጣ ነው ከተባለ ጋዜጣ አዙሪዎች ለማውጣት አይፈሩም፡፡ ምክንያቱም እስክንድር ጋዜጣ አደረብኝ የሚል አዙዋሪ በሙሉ ይመለስለታል፡፡ ጋዜጣ አዙዋሪ የሌላውን ለማውጣት መጠን ያበጃል በእስክንድር ጋዜጣ ላይ ግን ቢመለስብኝስ ብሎ አይፈራም፡፡ 12 ሰአት ካለፈ በኋላ እድሜ ለእስክንድር ብሎ ቤቱ ይገባል፡፡ ጠዋት አምጥቶ ይመልሳል፡፡ አዟሪ በሙሉ ሌላ አሣታሚ አልመልስ ካለው እስክንድር እንኳን እየመለሰ ሲል ሁሉም ለእሱ ክብር ሲል መመለስ ጀመረ፡፡ እስክንድር የየትኛውም ተቃዋሚ ፓርቲ አባል አይደለም፡፡ አልነበረምም፡፡ ሁሌም ተቃዋሚ ፓርቲዎችን ይወቅሳል፡፡ ይናገራል፡፡ ምኒልክ ጋዜጣ በነበረበት ጊዜ በመጀመሪያ የተጋጨው ከኢ/ር ኃይሉ ሻወል ጋር ነበር፡፡ የግጭቱ መንስኤ ደግሞ የፓርቲያችሁ አቋም ይሄ ነው ለምን ሆነ በሚል ነው፡፡ እውነት እንነጋገር ከተባለ ለኢህአዴግ ስጋት ፈጥሮ የነበረው ፓርቲ “ቅንጅት” በሚሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እስክንድር አንድም ቀን ተገኝቶ አያውቅም፡፡ በእነሱ አሰራር ወይም አካሄድ ላይ ቅሬታ ካለው ግን ይናገራል፡፡ ኢ/ር ኃይሉ ሻወል በልጃቸው አማካይነት ተቃውሞውት ወደ ክስ አመራለሁ ብለው ያውቃሉ፡፡ የፖለቲካ ፓርቲዎቹ በውስጣቸው ያለውን ችግር ይገልፃል፡፡ ሌላው ይቅርና አቶ ልደቱ አያሌውን ማንዴላ በተባሉበት ወቅት ሣይቀር የእሣቸው አካሄድ ላይ በድፍረት ቅሬታውን የገለፀ ሰው ቢኖር እስክንድር ነጋ ነው፡፡
ዘመን ሲቀየር ሕዝብ ሊቀየር ወዳጅም ሊከዳና ሊርቅ ይችላል፡፡ እስክንድር ነጋ ግን ዛሬ አብጠው ሲሰሩ ከማያቸው አንዳንድ ጋዜጠኞች የእሱ ምክርና ድጐማ የሌለባቸው አሉ ብሎ ለመናገር ይከብዳል፡፡ ይህቺ ሀገር ጋዜጠኛ አፈራች እስክንድር ነጋን ብል የማፍርበት ሰው አይደለም፡፡ ሁሌም የምኮራበት ሰው ነው፡፡ ከላይ እንደገለፅኩት እስክንድር የማንም የፖለቲካ ፓርቲ አባል አይደለም፡፡ ሁሌም “ምርጫ 97″ የሚለውን መፅሐፍ ሣስበው አለም የእሱን የእውቀት ደረጃ እንዲለካ እፈልጋለሁ፡፡ ከእሱ በኋላ እሱን አጣጥመው የማያውቁት ተነስተው ታሪክ ለመስራት ቢሞክሩ እነሱን በወንፊት አጥልሎ ማንነታቸውን ለማወቅ ይከብዳልና፡፡ የማያውቁት አገር አይናፍቅም እንደሚለው ዘፈን እስክንድር ነጋን ያየ ዛሬ በሌሎች ያልተጣራና ያልተረጋገጠ ተግባር ሊደመም አይችልም፡፡ የፅሁፌ ሳጠቃልል እስክንድር ነጋ በኢትዮጵያ የነፃ ፕሬስ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ቦታ ያለውና ስለእውነት ብቻ የሚናገር ምርጥ ጋዜጠኛ መሆኑን ምስክርነቴን በመስጠት ነው፡፡

http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/06/eskindir.jpg