Tuesday, April 2, 2013

ሰበር ዜና) አርቲስት ቲዎድሮስ ካሳሁን ለጊዜው ምንነቱ ባልታወቀ አለመግባባት ምክንያት ከባለቤቱ መፋታቱ ተነገረ


The recently married artist Tewodros Kassahun aka Tedy Afro has reportedly been divorced, sources closer to the artist Told EthiopianObserver. The divorce comes after a continuous argument between the two. According to the sources Amleset Muche has already left him and now she is with her parents. Our effort to reach Tedy Afro via phone is not successful yet. Read More on EthiopianObserver
በቅርቡ ጋብቻቸውን የፈፀሙት አርቲስት ቲዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) እና ባለቤቱ መፋታታቸው እየተነገረ ነው፡፡ ለአርቲስቱ ቅርብ የሆኑ ሰዎች ትናንት ምሽት አካባቢ ለኢትዮጵያን ኦብሰርቨር እንደጠቆሙት ጥንዶቹ የተፋቱት ለቀናት በዘለቀ አለግባባት ምክንያት ነው፡፡ ለጊዜው አለመግባባት የተፈጠረበት ምክንያት ግልፅ ባይሆንም ጉዳዩን አጣርተን እንደደረሰን እናቀርባለለን፡፡ የቴዲ ባለቤት በአሁን ሰዓት በቤተሰቦቿ ቤት እንደምትገኝ ተረጋግጧል፡፡
ጉዳዩ እንዲህ ነው
ያለፉት 13 ቀናት ለአርቲስት ቲዎድሮስ ካሳሁን እና ባለቤቱ አምለሰት ሙጬ ጥሩ አልነበሩም፡፡ ቴዲ በህይወቱ ለመጀመሪያ ጊዜ ጮክ ብሎ ማውራት ጀምሯል፡፡ አምለሰት ባሌቤቷ ቅናት ብጤ እንደጀማመረው እርግጠኛ ሆናለች፡፡ ሁኔታው ቢያስቃትም እየተደጋገመ ሲሄድ ግን ትግስቷ ያለቀ ይመስላል፡፡
“ቢያንስ ቀስ ብለህ አውራ ጎረቤት እስኪሰማ ድረስ ለምን ትጮሃለህ” ስትለው እንደነበርም ግድግዳ ተደግፈው ሲያዳምጡ እንደነበር የሚገልፁ የአርቲስቱ ጎረቤቶች ለኢትዮጵያን ኦብዘርቨር ተናግረዋል፡፡ የመረጃ ምንጮቻችን አያይዘውም ቴዲ ሰሞኑን የማንንም ስልክ እያልመለሰ መሆኑን ነው የጠቆሙት፡፡
አርቲስቱ በቅርቡ “ትዳር” የተሰኘ አልበም ለማውጣት በእንቅስቃሴ ላይ ነው ያሉት እንዚሁ ምንጮቻችን አሁን ከተፈጠረው ሁኔታ አንፃር የዘፈኖቹ ይዘት ምን ሊሆን እንደሚችል መገመት አያዳግትም ባይ ናቸው፡፡
ይህን መረጃ እያጠናከርን ባለlበት ሰዓት አርቲስቱ ቤቱን ቆልፎ ከአዲስ አበባ ራቅ ወዳለ ቦታ ሳይሄድ እንዳልቀረም የሚጠቁሙ መረጃዎች እየደረሱን ነው፡፡ ምናልባትም በአሁን ሰዓት አርቲስቱ ራቅ ወዳለ ቦታ የሄደው ለአዲሱ አልበሙ መጠሪያ ይሆናል ተብሎ የሚጠበቀውን “ትዳር” የተሰኘ ዜማ ለመለማመድ ሳይሆን እንደማይቀር ይህን አፕሪል ዘ ፉል አስቀድመው ነቄ ያሉ ሁላ ይደርሱበታል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡
እወነታው ይሄ ነው፡፡ ቴዲ አፍሮና ና ተወዳጇ ሚስቱ አሁንም ትዳራቸውን በፍቅር እየመሩ ነው፡፡ የአብርሃምና የሳራ እንዲሆንላቸውም እንመኛለን፡፡
Read More on EthiopianObserver

ከእሁድ እስከ እሁድ


(የሳምንቱ አጫጭር ዜናዎች)
map of eritrea


በኤርትራ “ውስጣዊ ትርምስ” ያሰጋል ተባለ
በኤርትራ እየጎላ የሄደው ያለመረጋጋት፣ እየተገለለች የሄደችውን አነስተኛ ሀገር በውስጣዊ ትርምስ ውስጥ ሊከት ይችላል እንደሚችል የዓለም አቀፍ የቀውስ ቡድን International Crisis Group የተባለው ድርጅት ባወጣው ዘገባ ገለጸ። ለሰላማዊ የስልጣን ሽግግር የሚያመች ስርአት ባለመኖሩም ወታደራዊው ሀይል የመሪነት ሚና ሊጫወት እንደሚችል ስጋቱን አስታውቋል። ጎልጉል በኤርትራ መፈንቅለ መንግስት ይገመታል ሲል መዘገቡ ይታወሳል።
ባለፈው ዓመት የኢትዮጵያ ወታደሮች ሁለት ጊዜ ወደ ኤርትራ ለመግባት መቻላቸውና በያዝነው ዓመት ቀደም ሲል በሁኔታዎች ያልተደሰቱ ወታደሮች ለማመጽ መሞከራቸው ራሱ የኤርትራ ወታደራዊ ሃይል ያለበትን “ደካማ ሁኔታ” እንዳጋላጠው የቡድኑ የአፍሪቃ ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ ሴድሪክ ባርነስ መናገራቸውን ቪኦኤ አመልክቷል።
የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የፖለቲካ አማካሪ አቶ የማነ ገብረአብ እንደተለመደው ሪፖርቱን “ከእውነታው ጋር የሚያገናኘው ነገር የለም” ሲሉ አጣጥለውታል። ኤርትራ ላለፉት ለአራት ተከታታይ ዓመታት በአካባቢው ኢኮኖሚያቸው እጅግ እያደገ በመሄድ ላይ ካሉት ሀገሮች መካከል እንደምትፈረጅ፣ በማህበራዊ ዘርፍም የሚደነቅ ስኬት ማስመዝገቧንና በአሁኑ ወቅት ሀገሪቱ የተረጋጋች እንደሆነች አመልክተዋል። እሳቸው ይህንን ቢሉም ዳቦ ለመግዛት በሌሊት ሰልፍ እንደሚያዝና ከቤተሰብ ቁጥር በላይ መግዛት እንደማይቻል፣ የኑሮ ውድነት፣ የወታደራዊ ግዳጅና አፈና ህዝቡን እንዳማረረው በስፋት አገሪቱን እየለቀቁ የሚወጡ ተወላጆች እየመሰከሩ ነው።
አዲስ አበባ በነዋሪነት የማታውቃቸው ድምጽ ሊሰጧት ነው

(ፎቶ: Guardian)
በሚያዚያ ወር ለሚካሄደው የአዲስ አበባና የወረዳ ምርጫዎች የተመዘገበው መራጭ ቁጥር ከተጠበቀው በታች መውረዱ ያሰጋው መንግስት፣ ከክልል ከተሞች የራሱ ደጋፊ አባላትን በማምጣት በምርጫው እንዲሳተፉ ለማድረግ ስልጠና እንደሰጠ ኢሳት መጋቢት 21 ቀን 2005 ዓ ም ባወጣው ዜና አስታወቀ።
ከክልል የመጡት ሰዎች በተለያዩ ወረዳዎች በሚገኙ የስልጠና ጣቢያዎች በመጪው ምርጫ እንዴት ድምጽ እንደሚሰጡ ስልጠና እየተሰጣቸው ነው። በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ በነጻነት ትምህርት ቤት 600 ሰልጣኞች ዜናው በተዘገበበት ቀን ስልጠና የተሰጣቸው ሲሆን፣ አብዛኞቹ ሰልጣኞች ቴክኒካዊ የሆኑ ነገሮችን ሲማሩ መዋላቸውንና በምርጫው እለት ወደ አዲስ አበባ ሲመጡ ግር እንዳይላቸው አስፈላጊውን የሲሙሌሽን ትምህርት ሲማሩ መዋላቸውን በስልጠናው የተሳተፈ የድርጅት አባልን በመጥቀስ ኢሳት ዘግቧል። በስልጠናው በጥቅሉ ከ5 ሺህ በላይ በአዲስ አበባ ያልተመዘገቡ የኢህአዴግ አባላት እንደሚካተቱ ከዜናው ለመረዳት ተችሏል።
“ጸልዩ” ባራክ ኦባማ ለማንዴላ “ጸሎት” አደረጉ
እርጅና የተጫናቸው የአፍሪካ ምርጥ ልጅ ኔልሰን ማንዴላ ሆስፒታል መግባታቸውን ተከትሎ ሁሉም ያገራቸው ህዝብ መልካም ዜናቸውን ይናፍቃል። የነጻነት ታጋዩና አስተዋይነታቸው ጎልቶ የሚታየው ማንዴላ ለውጥ ማሳየታቸው ቢነገርም አሁንም ሆስፒታል ናቸው።
ያንን አሰቃቂ የአፓርታይድ ስርዓት ከተገላገሉ በኋላ ስልጣን በያዙ ማግስት ቂም በቀልን አራግፎ በመጣል፣ ለበደሏቸው ጭምር “አገር እናልማ” የሚል መልክት ያስታለለፉት ማንዴላ የደቡብ አፍሪካ ብቻ ሳይሆን የሁሉም አፍሪካ እንቁ ናቸው።
የአሜሪካ ሬዲዮ አማርኛው ክፍል እንደዘገበው የፕሬዚዳንት ጃኮብ ዙማ ቃል አቀባይ ማክ ማሃራጅ የማንዴላን ጤንነት አስመልክቶ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ደቡብ አፍሪካዊያን ለማዲባ እንዲፀልዩ መጠየቃቸውን ካበሰረ በኋላ፣ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማና የቤተ መንግሥታቸው ባልደረቦች ለኔልሰን ማንዴላ ደህንነት ፀሎት ማድረጋቸውን አመልክቷል።
አንደበት
“ሙስሊሙ ሽብርተኛ አይደለም። ባገሬ ላይ ሙስሊም ሆኜ ጺሜን አስረዝሜ፣ ሱሪዬን አሳጥሬ፣ ሴቷም ጸጉሬን ተሸፋፍኜ፣ ገላዬን ሸፍኜ፣ ሀገሬን ወድጄ፣ ህጌን አክብሬ የምትኖርባትን ኢትዮጵያ፤ ማንም ክርስቲያኑም እምነቱን በነጻነት ባገሩ ላይ አውጆ፣ ዋቄፈታም ቢሆን እምነቱን እንደልብ ባገሩ ላይ አውጆ፣ ማናችንም ብንሆን ከህግ በምንወጣበት ጊዜ በህግ የምንጠየቅባትን ኢትዮጵያን እንፈልጋለን …”
ሼኽ ኢማን ካሊድ ኦማር/ Sheik Khaled Omar በሲያትል ከተማ ዋሺንግተን ጠቅላይግዛት ካደረጉት ንግግር የተወሰደ

“… ሱሪ ማሳጠር፣ ጺም ማሳደግ ይቻላል፡፡ መብታቸው ነው፡፡ ጺሙ ግን ቅጫም ካለበት ለራሱም ሆነ ለሌላው ጤና ስለማይሰጥ እንቆርጠዋለን፤ እናቃጥለዋለን … ”
አቶ መለስ በጋዜጣዊ መግለጫና በፓርላማ ከተናገሩት ለንጽጽር የተወሰደ፡፡

የመለስ አረንጓዴ ዘመቻ ተጠናቀቀ፤
“የኮበለሉ የዱር እንስሳቶች ተመለሱ”
ከአምስት ዓመት በፊት በአካባቢው ልምላሜ ብሎ ነገር አይታይም። በገጠር ቀበሌያችን የነበረውን የተፈጥሮ ደን አላግባብ መጠቀማችን በግልፅ ያመለክታል። የአካባቢያችን ደን ለማገዶና ለቤት መስሪያ ሲባል በእጅጉ አውድመነዋል። እንደ ጅብ፤ ነብር፤ ቆቅ፤ ከርከሮ የመሳሰሉትን የዱር አራዊቶች በአካል ቀርቶ ድምፃቸው ከጠፉ ቆይቷል። ከተራራማው ስፍራ የሚወርደው የክረምት ጎርፍ የእርሻ መሬታችን አፈርም ጭምር ሸርሽሮ ቁልቁል ስለሚወስደው የምናምርተው ሰብል እምባዛም ነበር በማለት በትግራይ ክልል ደቡባዊ ዞን የመለስ አረንጓዴ ዘመቻ ተጠቃሚዎች መናገራቸውን ኢዜአ ዘገበ።

(ፎቶ: ONE)
የሰብል ምርታችን በየዓመቱ እየቀነሰም የመንግስት እርዳታ እንድንጠብቅ ዳርጎን ነበር። በዚህ የተነሳ አብዛኛው የአካባቢያችን ሰው በሕገ ወጥ መንገድ የተሻለ ነገር ፍለጋ ወደ ጂዳ የመሳሰሉት የአረብ አገሮች መሰደድ እየተለመደ መጥቷል። ካለፉት አምስት ዓመታት ወዲህ መንግስታችን በቀየሰው የአካባቢ ጥበቃና ተፋሰስ ልማት አቅጣጫ በመሰለፋችን በገጠር ቀበሌያችን ከፍተኛ ለውጥ ማምጣት ችለናል። በእነዚህ ዓመታት ያከናወነውን የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ ሁለት ጥቅሞችን አግኝተንበታል።
አንደኛ በአፈርና ውሃ ጥበቃው ሥራ ፀዳቂ ተክሎች እየተከልንበት በመሆኑ የአካባቢው ደን መልሶ እንዲያገግም አድርገናል። የምንተክላቸው እጽዋቶችና ዛፎች ከሰውና እንስሳት ንኪኪ ነፃ ሆኖ ስለምንከልለው የገጠር ቀበሌው የደን ሽፋን በአጭር ግዜ እንደለወጥ አግዞታል። በዚህ ምክንያት ካሁን በፊት መጠለያ አሳጥተናቸው ከአካባቢው ርቀው የነበሩትን የዱር እንስሳት ተመልሰው መስፈር ጀምረዋል። አሁን አሁን የዱር አራዊቶቹ በድምፃቸው ብቻ ሳይሆን በአካል ልናያቸው ችለናል። ዛሬ እንደ ጅብ፤ አቦ ሸማኔ፤ ቆቅ፤ ከርከሮ ቁጥራቸው እየተበራከተ ነው። የአካባቢው አርሶአደሮችም ለዱር እንስሳቱ ተገቢው ጥበቃና ከለላ እያደረጉላቸው እንደሆነ ተጠቃሚዎቹን ጠቅሶ ኢዜአ ዘግቧል።
ተገኝወርቅ በተመድ ከፍተኛ ሹመት አገኙ
የተባበሩት መንግስታት ዋና ጸሐፊ ባን ኪ ሙን ኢትዮጵያዊውን ተገኝወርቅ ጌቱን የጠቅላላ ጉባኤና የጉባዔዎች አስተዳደር ረዳት ዋና ጸሃፊ አድርገው መሾማቸው ባለፈው ሳምንት ከተዘገቡት ኢትዮጵያ ነክ ጉዳዮች በበጎ መልኩ ቀዳሚው ነው። በሹመቱ መሰረት አቶ ተገኝወርቅ የመንግሥታ ድርጅት በስሩ የሚያስተዳድርራቸውን 1200 ሰራተኞች ይመራሉ።
የተባበሩት መንግስታት ሹመቱን አስመልክቶ ያሰራጨው ዜና እንደሚያመለክተው አቶ ተገኝወርቅ ባሳዩት ብቃትና ባላቸው እውቀት እንደሆነ አመልክቷል። ላለፉት ሰላሳ ዓመታት በብሄራዊና በዓለም አቀፍ ደረጃዎች በልማት መስክ በመሰማራት ያስመዘገቡት ውጤት እንዲሁም በትምህርት፣ በመንግሥትና በግል ዘርፎች ያከናወኗቸው ሥራዎች ተመራጭ እንዳደረጋቸውም ታውቋል። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም የአፍሪካ ቢሮ ረዳት ዋና ፀሐፊ ሆነው ካለፉት አራት ዓመታት ወዲህ በመሥራት ላይ የነበሩት አቶ ተገኝወርቅ፣ የፕሮግራሙ ሥራ አስፈጻሚ ጽህፈት ቤት ዳይሬክተርና በናይጄሪያ የፕሮግራሙ ተጠሪ ሆነውም ሰርተዋል። በኮሎምቢያ፣ በሮቸስተርና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲዎችና በሃንተር ኮሌጆች በመምህርነት ማገልገላቸውን በመጥቀስ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ለሹመቱ እንደሚመጥኑ ዘግቧል።
የአባይ ግድብ ሁለተኛ ዓመት ተከበረ
“የአባይ ግድብ እዳ አለብን ጠጋ ጠጋ በሉ”
“በራሳችን ሃብትና ጉልበት እንገነበዋለን” የተባለው የአባይ ግድብ ተሰርቶ እስኪጠናቀቅ በቁርጠኛነት አስፈላጊውን ሁሉ ለማድረግ አርቲስቶች ቃል መግባታቸውን ኢቲቪ አስታወቀ። የውሃ ሚኒስትሩ አቶ አለማሁ ተገኑ በማናቸውም የውጪ ተጽዕኖ ግንባታው እንደማይስተጓጎልና በተያዘለት ጊዜ እንደሚጠናቀቅ አስታውቀዋል።
በሌላ ወገን ደግሞ ለግድቡ ግንባታ ሰራተኞች ሳያወቁ ደሞዛቸው እንዲቆረጥባቸው መደረጉ ቅሬታ ፈጥሯል። ከተለያዩ ወገኖች እንደሚሰማው የኑሮ ውድነት ያስቸገራቸው ዜጎች ግድቡ እንዲገነባ ፍላጎት ቢኖራቸውም ከምኞት ማለፍ አይችሉም። የጀርመን ድምጽ ሬዲዮ ዘጋቢ በግድ ደሞዝ አምጡ የተባሉትን ካነጋገረ በኋላ “በድሬዳዋ የባጃጅ ታክሲ አሽከርካሪዎች ‘የአባይ ግድብ እዳ አለብን ጠጋ ጠጋ በሉ’ የሚል ማስታወቂያ ለጥፈው ማየቴ ታወሰኝ ያለው ትዝ አለኝ” በማለት ትዝብቱን አክሏል።

ጋዜጠኛ ርዮት አለሙ በቃሊቲዎች ክስ ቀረበባት!


መምህርት እና ጋዜጠኛ ርዮት አለሙ በቃሊቲ እስር ቤት የሚገኙትን የአስተዳደር እና የጥበቃ ሰራተኞች ትንቂያለሽ፣ትሰደቢያለሽ እንዲሁም “የምትሰሩትን በሚዲያ እና ድረ ገፆች አጋልጣለሁ” ብለሽ ትዝቺያለሽ በሚል ክስ ቀርቦባት መጋቢት 25 /2005 ዓ.ም ቃሏን መስጠቷ ተሰማ፡፡
ጋዜጠኛይቱ ክሱን አስመልክቶ ቃሏን እንድተሰጥ የተጠየቀቸችው መጋቢት 19 /2005 ዓ.ም ምሽት ከመኝታዋ ተቀስቅሳ የነበረ ቢሆንም ከጠበቃዬ ጋር ሳልነጋገር ምንም የምሰጠው ቃል የለኝም በማለቷ እስከ መጋቢት 25 ሊዘገይላት ችሏል፡፡
ርዮት የተከሰሰችው በፌደራል ታራሚዎች አያያዝ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 139/1999 አንቀፅ 36 መ እና ሠ ላይ በተቀመጠው መሰረት ሲሆን ይህ አንቀፅ “ከባድ የዲሲፒሊን ቅጣት የሚያስከትሉ ድርጊቶች” ተብሎ የተዘረዘረ ነው፡፡
ርዮት ቅጣቱ ተግባራዊ ከተደረገባት፤
ከአንድ ወር እስከ አራት ወር ለሚደርስ ጊዜ በወዳጅ ዘመዶቿ እንዳትጎበኝ፤ ደብዳቤ እንዳትልክ እና እንዳትቀበል (ይሄ እንኳ አሁንም ተግባራዊ ተደርጎባታል) የእስር ቤቱን ቤተ መጻህፍት እንዳትጠቀም፣ በእስር ቤቱ በሚደረግ የጋራ ዝግጅት እና መዝናኛ ላይ እንዳትሳተፍ እንዲሁም ከአንድ ወር እስከ ሁለት ወር ለሚደርስ ጊዜ ለብቻ እስር ትዳረጋለች፡፡
እንዲህ ከሆነ ደግሞ ያቺ በቃሊቲዊቹ ውቃቢ ትፈቀድ የነበረች አመክሮም ልትከለከል ነው ማለት ነው፡፡
በነገራችን ላይ ወጣቱ ፖለቲከኛ ናትናኤልም በእስር ቤቱ እየደረሰበት ያለውን አበሳ በመቃወም የርሃብ አድማ ላይ መሆኑ ተሰምቷል፡፡ የሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ አባላትም ቅጥ ያጣውን የእስር ስርዓት ሃይ ለማለት የርሃብ አድማ ላይ ናቸው፡፡
ወይ ጣጣ… ብዬ የራሴን አስተያየት በአዲስ መስመር አቀርባለሁ…
እኔ የምለው ግን ኢህአዴግ ምነው እንዲህ መካሪ አጣ…? እርሱ እኛን በስንቱ መከራ እንዳልመከረን እርሱን የሚመክረው ማጣቱ የሚገርም ነው፡፡
እስቲ አሁን በእስር ላይ የሚገኙ ሰዎችን እስሩ አንሶ አሳር የሚያበላው ምን ይሁነኝ ብሎ ነው? እንደሰማነው በርካታ የህሊና እስረኞች በታመሙ ጊዜ የሚያክሟቸው የእስር ቤቱ ሀኪሞች “መግደል ነበር አንተን” “መጨረስ ነበር አንቺን” እያሉ ያስፈራራሉ፡፡ እውነቱን ለመናገር ይሄ የመጨረሻው ዘመን ምልክት ነውና ነቅታችሁ ጠብቁ፡፡ መንግስታችን “ባትሪ ሎው” እያለ ይመስለኛል!

Monday, April 1, 2013

መንግስት የክልል ነዋሪዎችን በአዲስ አበባ ምርጫ ሊያሳትፍ ነው


መጋቢት ፳፩ (ሀያ አንድ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም 

ኢሳት ዜና:-በመጪው ሚያዚያ ለሚካሄደው የአዲስ አበባና የወረዳ ምርጫዎች የተመዘገበው መራጭ ቁጥር ከተጠበቀው በታች መውረዱ ያሰጋው መንግስት ፣ ከክልል ከተሞች የራሱ ደጋፊ አባላትን በማምጣት በምርጫው እንዲሳተፉ ዛሬ ስልጠና ሲሰጥ ውሎአል።
ከክልል የመጡት ሰዎች በተለያዩ ወረዳዎች በሚገኙ የስልጠና ጣቢያዎች በመጪው ምርጫ እንዴት ድምጽ እንደሚሰጡ ስልጠና እየተሰጣቸው ነው። በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ በነጻነት ትምህርት ቤት  600 ሰልጣኖች ዛሬ ስልጠና የተሰጣቸው ሲሆን፣ አብዛኞቹ ሰልጣኖች ቴክኒካዊ የሆኑ ነገሮችን ሲማሩ መዋላቸውን እና በምርጫው እለት ወደ አዲስ አበባ ሲመጡ ግር እንዳይላቸው አስፈላጊውን የሲሙሌሽን ትምህርት ሲማሩ መዋላቸውን በስልጠናው የተሳተፈ አንድ የድርጅት አባል ለኢሳት ገልጿል።
ዛሬ በተሰጠው ስልጠና ከ5 ሺ ያለነሱ ከየክፍለሀገራቱ ተውጣጠው የመጡ የገዢው ፓርቲ አባላት ተሳትፈዋል። በተከታታይ ዙር ስልጠናዎች ሌሎች አዳዲስ አባል መራጮች እንደሚሳተፉ ለማወቅ ተችሎአል።
ኢህአዴግ ያለማንም ተፎካካሪ ፓርቲ በአዲስ አበባ እንደሚያሸንፍ ቢያውቅም ፣ የመራጩ ቁጥር መቀነስ ፖለቲካዊ ገጽታ ያበላሻል በሚል ስሌት መራጮችን ከክፍለሀገር ማስመጣት ብቻ ሳይሆን፣ የጎዳና ተዳዳሪዎችን ሳይቀር እንዴት እንደሚመርጡ እያሰለጠነ እንደሚገኝ መዘገባችን ይታወሳል።

ሰበር ዜና! በረከት ስምኦን ለቅሶ ላይ ናቸው


በረከት ስምኦን ለቅሶ ላይ ናቸው
ባህር ዳር ላይ በብአዴንና በኢህአዴግ ጠቅላላ ጉባኤ ተጠምደው የሰነበቱት አቶ በረከት ስምኦን የመኢአድ ቢሮ ከሚገኝበት ቴዎድሮስ አደባባይ አካባቢ የሚኖሩት ወላጅ እናታቸው የመሞታቸውን ዜና አድምጠዋል ፡፡ እንደመረጃው ከሆነ የበረከት እናት የቀብር ስርዓት በጎንደር ገብርኤል ቤተክርስቲያን ዛሬ ተፈጽሟል፡፡ ኤርትራዊ ስለመሆናቸው የሚነገርላቸው ወ/ሮዋ በፌደራል ማርሽ ታጅበው መቀበራቸው ብዙዎቹን የአካባቢ ሰዎች አስገርሟል፡፡ከጠዋቱ 3፡00 እሰከ 6፡00 የከተማው መንገድም ተዘግቶ መቆየቱ ተነግሯል፡፡
Mesay Mekonnen

UN FINDS IMPRISONMENT OF ETHIOPIAN JOURNALIST ESKINDER NEGA ARBITRARY UNDER INTERNATIONAL LAW AND CALLS FOR IMMEDIATE RELEASE


Washington, D.C.: In an opinion released today by Freedom Now, the UN Working Group on Arbitrary Detention found the Government of Ethiopia’s continued detention of independent Ethiopian journalist and blogger Eskinder Nega a violation of international law. The panel of five independent experts from four continents held that the government violated Mr. Nega’s rights to free expression and due process. The UN Working Group called for his immediate release.
Mr. Nega is serving an 18-year prison sentence on terror and treason charges in response to his online articles and public speeches about the Arab Spring and the possible impact of such movements on the political situation in Ethiopia. Arrested in September 2011, Mr. Nega was held without charge or access to an attorney for nearly two months before authorities charged him under Ethiopia’s widely criticized anti-terror laws. This is the eighth time during his 20-year career as an independent journalist and publisher that the Ethiopian government has detained Mr. Nega. His appeal has been repeatedly postponed, most recently on March 27, 2013.
In the attached opinion, released in conjunction with an op-ed by the renowned Ethiopian opposition leader and former prisoner of conscience Birtukan Mideksa, the UN Working Group found that the application of overly broad anti-terror laws against Mr. Nega constituted an “unjustified restriction” on his right to freedom of expression. The UN Working Group’s opinion also recognized “several breaches of Mr. Nega’s fair trial rights,” further rendering his continued detention arbitrary under international law.
“The Ethiopian government cannot continue to use anti-terrorism legislation to muzzle the work of independent journalists, even when it does not like what is being reported,” said Freedom Now Executive Director Maran Turner. “The targeting of journalists by resorting to overly broad anti-terror laws, just like the use of anti-state charges in the pre-9/11 era, is a violation of the internationally protected right to free expression and undermines international efforts to address real security threats.”
Freedom Now represents Mr. Nega as his international pro bono counsel.
Contact:    Patrick Griffith
pgriffith@freedom-now.org
+1 (202) 223-3733

በፌስ ቡክ አስተያየት የፃፈ የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ታሰሩ !


በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሙስና ይፈፀማል ብሎ የማኅበራዊ መገናኛ መድረክ በመሆነዉ ፌስ ቡክ የፃፈ የዩኒቨርሲቲ ተማሪ መታሰሩ ተሰምቷል።
በአዲሱ የአዲስ አበባ ቴክኒዎሎጂ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ የሆነዉ ወጣት በዚሁ ምክንያት ታስሮ ወደአርባምንጭ መወሰዱን ወኪላችን የላከልን ዘገባ ያመለክታል። የአርባ ምንጭ ፖሊስ የሰዎች ስም የሚያጎድፍ በማዉጣቱ በፍርድ ቤት ትዕዛዝ ከአዲስ አበባ ወስደን ለፍርድ ለማቅረብ ጉዳዩን እያጣራሁ ነዉ ማለቱንም ዮሐንስ ገብረእግዚአብሔር በዘገባዉ ጠቅሷል።
ዮሐንስ ገብረእግዚአብሔር  audio here http://www.dw.de/popups/mediaplayer/mediaId_16712823
ሸዋዬ ለገሠ
አርያም ተክሌ
dw.de