Monday, December 8, 2014

Yemen migrant boat carrying Ethiopians sinks killing 70

_75350095_107694068BBC

A boat carrying African migrants has sunk off Yemen’s western coast, killing 70 people, Yemeni officials say.
The boat, carrying mostly Ethiopian migrants, sank off Yemen’s al-Makha port due to strong winds and rough waves, security officials said.

  • 222
     
    Share
  • SHAREBAA boat carrying African migrants has sunk off Yemen’s western coast, killing 70 people, Yemeni officials say.The boat, carrying mostly Ethiopian migrants, sank off Yemen’s al-Makha port due to strong winds and rough waves, security officials said.

Tens of thousands attempt to cross the Red Sea into Yemen every year, often in rickety, overcrowded vessels. Hundreds have died making the journey.
Yemen is viewed by many migrants as a gateway to the Middle East or Europe.
The latest sinking occurred on Saturday, with reports of the incident emerging on Sunday.
The Red Sea crossing between the Horn of Africa and Yemen is one of the world’s major migration routes, BBC Arab affairs editor Alan Johnston says.
Migrants dream of finding jobs and better lives in rich places like Saudi Arabia – but they are in the hands of unscrupulous people smugglers and, too often, never reach the Yemeni shore, our correspondent adds.
_79573791_76604103
n October, the UN refugee agency said that more than 200 people had died at sea in 2014 while attempting to reach Yemen.
“There have been frequent reports of mistreatment, abuse, rape and torture, and the increasingly cruel measures being adopted by smuggling rings seem to account for the increase in deaths at sea,” the UN said at the time.
 Migrant Boat Was ‘deliberately Sunk’ In Mediterranean Sea, Killing 500
http://www.zehabesha.com/yemen-migrant-boat-carrying-ethiopians-sinks-killing-70/Video:


ብሄራዊ ብድር የዕድገታችን ምንጭ እንጂ የደኅንነታችን ስጋት ሊሆን አይገባም


እኛ ሰዎች ሁሌም ከምንፈራዉና ከምንጠላዉ አንዴ ከገባንበት ደግሞ የቱንም ያክል ብንጠላዉና ብንፈራዉ እየደጋገምን የምንዘፈቅበትና በቀላሉ የማንወጣዉ አዘቅት ቢኖር ብድር ወይም የብድር ልጅ የሆነዉ ዕዳ ነዉ። ብድር ግለሰቦች ብቻ ሳይሆኑ የንግድ ድርጅቶች፤ ማዘጋጃ ቤቶች፤ ትላልቅ ኮርፓሬሺኖችና አገሮች በአጭርና በሪጂም ግዜ የሚያጋጥማቸዉን የገንዘብ እጥረት የሚሸፍኑበት መንገድ ነዉ። ወይም ቀለል ባለ አማርኛ ብድር ወደፊት በምናገኘዉ ገቢ ዛሬን መኖር ማለት ነዉ። ብድር ግለሰቦች፤ ድርጅቶች ወይም አገሮች የመከፈል አቅማቸዉን እያዩ ቢበደሩና የተበደሩትን ገንዝብ ዉጤታማ በሆነ መንገድ ከተጠቀሙበት የእድገትና የብልጽግና መንገድ የሚከፍት አለዚያም የምንበደረዉ ብድር ከአቅም በላይ ከሆነና ዉጤታማ ባልሆነ መልኩ ከተጠቀምንበት ደግሞ በቀላሉ የማንወጣዉ መቀመቅ ዉስጥ ይዞን የሚገባና ጫናዉ ከትዉልድ ወደ ትዉልድ የሚተላለፍ ዕዳ ነዉ። ዕዳ ደግሞ በተለይ አገሮች የሚገቡበት ዕዳ ተከፍሎ ካላለቀ ወይም በምህረት ካልተሻረ በቀር ወለዱ ወለድ እየወለደ በተበዳሪ አገሮች የኤኮኖሚ እድገት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ የሚያደርግ የዕድገትና የብልፅግና ጠላት ነዉ። ዛሬ ሰፋ አድርገን የምንመለከተዉ ብድርና ዕዳን ቢሆንም ዋናዉ ትኩረታችን ግን አገራችን ኢትዮጵያን ጨምሮ በታዳጊ አገሮች የኤኮኖሚ ዕድገት ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ የሚያደርገዉን ብሄራዊ ብድርና ዕዳ ነዉ። ሁላችንም እንደምናዉቀዉ አገራችን ኢትዮጵያ ባለፉት ሃያ አመታት በብድር ላይ ብድር እየተበደረች አንዱንም ሳትከፍል በድጋሚ እየተበደረች ከድጡ ወደማጡ እየገባች ነዉ።
የኢትዮጵያ መንግስት መንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ የዉጭ አገር ምንጮች ብድር መበደር ከጀመረ ብዙ አመታት ተቆጥረዋል።ከቀዳማዊ ሚኒልክ በኋላ ኢትዮጵያን ለረጂም አመታት የመሩት ሦስቱ መንግስታት የብድር ጥማት ከፍተኛ ቢሆንም በብድር መጠኑም ሆነ በተከማቸ የዕዳ መጠኑ ዛሬ በስልጣን ላይ አንዳለዉ እንደ ወያኔ አገዛዝ የአገራችንን ብሄራዊ ደህንነት ለአደጋ ባጋለጠ መልኩ ብድር የተበደረና ዕዳ ዉስጥ የተዘፈቀ አገዛዝ ኢትዮጵያ አይታ አታዉቅም። የወያኔ አገዛዝ አገር ዉስጥ ቦንድ እየሸጠና ብሔራዊ ባንክን እያስገደ በተለያየ መልኩ የሚወስደዉ ብድር ከአለም ባንክ፤ ከአለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት፤ ከዉጭ አገር ባንኮችና አበዳሪ አገሮች በየአመቱ ከሚበደረዉ ብድር ጋር ተደምሮ የዛሬዉን ኢትዮጵያዊ ብቻ ሳይሆን የዛሬዉን ኢትዮጵያዊ የልጅ ልጆች ጭምር ባለዕዳ አድርጓቸዋል።
የወያኔ አገዛዝ ለህዳሴዉ ግድብና ለእድገትና ትራንስፎርሜሺን ዕቅድ ማስፈጸሚያ በሚል የአገሪቱን አመታዊ ገቢና የመክፈል አቅም በላገናዘበ መልኩ እጅግ በጣም ከፍተኛ ቁጥር ያለዉ ገንዝብ ከተለያዩ የአገር ዉስጥና የዉጭ አገር ምንጮች እየተበደረ ነዉ። ይህ መጠነ ሰፊ ብድር በረጂም አመት የሚከፈልና ከፍተኛ ወለድ የተሸከመ ሲሆን ወያኔ ይህ ብዙ ኢትዮጵያዉያንን ያሰጨነቀ ብሄራዊ ዕዳ አልበቃ ብሎት ከአቅም ዉጭ የጀመራቸዉን ፕሮጀክቶች ለማስጨረስ ነዉ በሚል ሰበብ አሁንም አገራችን ኢትዮጵያን ከዕዳ ወደ ዕዳ እየከተታት ይገኛል። በተለይ ወያኔ አበዳሪ አገሮች፤ የአለም ባንክና ወዳጆቹ የሆኑ መንግስታት ጭምር ተዉ ይቅርብህ ብለዉ እየመከሩት አልሰማ ብሎ በዚህ አመት ለመሸጥ ያሰበዉ ሉዓላዊ ቦንድ ወይም ፈረንጆቹ ሶቨርን ቦንድ ብለዉ የሚጠሩት ቦንድ ሽያጭ የጉዳዩ አሳሳቢነት የገባቸዉን ኢትዮጵያዉያንንና የኢትዮጵያ ወዳጆች ከወዲሁ እያሰጨነቀ ነዉ። በእርግጥም ሉዓላዊ ቦንድ ሽያጭ የሚያስጨንቅ ብቻ ሳይሆን አንደ ኢትዮጵያ አይነቶቹን ቀድሞዉኑም ዕዳ ዉስጥ የተዘፈቁ ደሃ አገሮች ህልዉና አደጋ ዉስጥ የሚከት የኤኮኖሚ ዕድገትን ብቻ ሳይሆን የአገር ደህንነትን ጭምር የሚፈታተን አደገኛ ጅምር ነዉ። ለመሆኑ ሉዓላዊ ቦንድ ምንድነዉ? አደገኛነቱስ ምኑ ላይ ነዉ?
ሉዓላዊ ቦንድ አገራቸዉ ዉስጥ ዝቅተኛ ቁጠባ የሚታይባቸዉ ብሔራዊ መንግስታት አገራቸዉ ዉስጥ ከአቅማቸዉ በላይ የሆነ የገንዘብ እጥረት ሲያጋጥማቸዉ የሽያጭ ዋጋዉ በአገራቸዉ ገንዘብ ሳይሆን ያወጣናል ብለዉ በሚያምኑት በሌላ አገር ገንዘብ ለምሳሌ በዶላር ወይም በዩሮ የተተመነ ቦንድ እየሸጡ ገንዝብ የሚበደሩበት መንገድ ነዉ። የየአገሩ መንግስታት ቦንድ አየሸጡ ገንዘብ መበደራቸዉ አዲስ ክስተት አይደለም፤ ሆኖም መንግስታት በተለይ የታዳጊ አገሮች መንግስታት ቦንድ የሚሸጡት አገራቸዉ ዉስጥ በአገራቸዉ ገንዘብ ነዉ። ሉዓላዊ ቦንድን ልዩ የሚያደርገዉ ቦንዱ የሚሸጠዉ በአለም አቀፍ ደረጃ ሆኖ ሽያጩ የሚከናወነዉ ደግሞ በዉጭ ምንዛሪ መሆኑ ነዉ። ሉዓላዊ ቦንድ ሽያጭን ከመደበኛ ቦንድ ሽያጭ የሚለዩት ብዙ ነገሮች አሉ።
ሉዓላዊ ቦንድ ከሌሎች መደበኛ ቦንዶች ጋር ሲነፃፀር ብዙ ዉስብስብ ችግሮች አሉበት። ለምሳሌ ሉዓላዊ ቦንድ የሚገዙ አገሮች ወይም ድርጅቶች ቦንዱን የሚገዙት በዉጭ ምንዛሪ ነዉ፤ ሁለተኛ ሻጩ አገር ለቦንዱ የሚከፍለዉ ወለድ እጅግ በጣም ከፍተኛ ነዉ። በሦስተኛ ደረጃ ደግሞ ብዙዉን ግዜ ሉዓላዊ ቦንድ የሚሸጥ አገር ከቦንዱ ሽያጭ የሚያገኘዉ ገንዘብ ወለዱ የተቀነሰለት ገንዝብ ነዉ። ለምሳሌ በ10 በመቶ ወለድ የአንድ መቶ ሚሊዮን ዶላር ሉዓላዊ ቦንድ የሚሸጥ አገር እጁ ላይ የሚገባዉ ዘጠና ሚሊዮን ዶላር ሲሆን ብድሩን መልሶ ሲከፍል የሚከፍለዉ ደግሞ አንድ መቶ ሚሊዮን ዶላር ነዉ። ይህ ማለት ደግሞ ቦንድ ሻጩ አገር ወለዱን የሚከፍለዉ በተበደረዉ ገንዝብ ተጠቅሞበት ሳይሆን የተበደረዉ ገንዘብ ገና እጁ ላይ ሳይገባ ነዉ ወለዱን የሚከፍለዉ። ለሉዓላዊ ቦንድ የሚከፈለዉ ወለድ እጅግ በጣም ከፍተኛ ስለሆን ብዙ አገሮች በተለይ ታዳጊ አገሮች ሉዓላዊ ቦንድ መሸጥ የማይፈልጉት ይህንኑ ለብድሩ የሚከፈለዉን ከፍተኛ ወለድ ሰለሚፈሩ ነዉ።
የወያኔ አገዛዝ እንደተራ ወረቀት እየፈበረከ ገበያ ዉስጥ የሚበትነዉ ገንዘብና ከአገር ዉስጥ ባንኮች ከአቅሙ በላይ የሚበደረዉ ገንዝብ ኢትዮጵያ ዉስጥ የዋጋ ንረቱን ምን ያህል ሰማይ ላይ እንደሰቀለዉና የኢትዮጵያን ህዝብ ምን ያክል እንዳደኸየ ሁላችንም በግልጽ የምናዉቀዉ ሀቅ ነዉ። በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንዲሉ የአገራችን ገበሬና ሠራተኛ የወያኔ ብልሹ የኤኮኖሚ ፖሊሲ ለአመታት ከፈጠረዉ የዋጋ ንረት በሽታ ሳይድን ነዉ ሌላ ሉዓላዊ ቦንድ የሚባል በቀላሉ የማይድን አደገኛ በሽታ ፊቱ ላይ የተደቀነበት።
ሉዓላዊ ቦንድ ደሃ አገሮች የሚሸጡትና ኃብታም አገሮች የሚሸጡት እየተባለ በሁለት ይከፈላል። ኃብታም አገሮች የሚሸጡትን ቦንድ ከነወለዱ ከፍለዉ ይጨርሳሉ ተብሎ በቦንድ ገዢ አገሮችና ድርጅቶችና ስለሚታመን እነዚህ አገሮች ለሚሸጡት ሉዓላዊ ቦንድ የሚከፍሉት ወለድ ዝቅተኛ ነዉ። ኢትዮጵያን መሰል ደሃ አገሮች ግን ብድር የመክፈል ችሎታቸዉ አስተማማኝ ስላልሆነ ሉዓላዊ ቦንድ ሲሸጡ ለቦንድ ገዢዉ የሚከፍሉት ወለድ እጅግ በጣም ከፍተኛ ነዉ። ስለሆነም ደሃ አገሮች በተለይም እንደ ኢትዮጵያ አይነቶቹ ለመጀመሪያ ግዜ ሉዓላዊ ቦንድ ለሚሸጡ አገሮች ቦንድ ለመሸጥ ከመወሰናቸዉ በፊት ማስተካከል ያለባቸዉ ብዙ ነገሮች አሉ። በነገራችን ላይ ሉዓላዊ ቦንድ መሸጥ በራሱ ምንም ጥፋት የለበትም። እንዲያዉም ህዝባዊና አገራዊ ሃላፊነት የሚሰማቸዉ መንግስታት ሉዓላዊ ቦንድ በመሸጥ የፋይናንስ ጉድለታቸዉን በመሸፈን የአገራቸዉን እድገት አቅጣጫ ቀይሰዉ ጠንካራ ኤኮኖሚ የመገንባት አቅም ማግኘት ይችላሉ። በኛም አገር ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎቸ አንደኛ አገራዊ ሃላፊነት ቢሰማቸዉ፤ ሁለተኛ በአቅማቸዉ ቢኖሩ፤ ሦስተኛ በአገር ስም የተበደሩትን ገንዘብ መዝረፍ አቁመዉ ሁሉንም ለአገር ጥቅም ቢያዉሉትና ተበድረዉ በሚሰሯቸዉ ፕሮጀክቶች ሁሉም ኢትዮጵያዊ እኩል ተጠቃሚ ቢሆን አገራችን መደበኛ ቦንድም ሆነ ሉዓላዊ ቦንድ በመሸጥ የምትበደረዉ ገንዘብ ብሄራዊ አቅም ስለሚገነባ ዕዳዉ ብዙም አያስፈራንም። ችግሩ ያለዉ ሉዓላዊ ቦንድ መሸጡ ላይ ሳይሆን እዚህ ዉሳኔ ላይ ከመደረሱ በፊት መወሰድ ያለባቸዉን እርምጃዎች በጥንቃቄ መዉሰዱ ላይ ነዉ። የወያኔም ትልቁ ችግር ያለዉ እዚህ ላይ ነዉ። የቦንዱ ሽያጭ ይዞት የሚመጣዉን ጣጣና ፈንጣጣ ግምት ዉስጥ ሳያስገባ ነዉ ሉዓላዊ ቦንድ እሸጣለሁ ብሎ ያወጀዉ።
የወያኔ አገዛዝ የበጀት ዲሲፕሊን የሌለዉ፤ በአቅሙ የማይኖር፤ እመራዋለሁ የሚለዉን አገር ኃብት የሚዘርፍና በሚያደርጋቸዉ ነገሮች ሁሉ ኢትዮጵያን የማያስቀድም የአገርና የህዘብ ጠንቅ የሆነ ክፉ አገዛዝ ነዉ።ኢትዮጵያን ጨምሮ በመላዉ አለም የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን የወያኔ ፓርላማ የሉዓላዊ ቦንድ ሽያጭ ረቂቅ ህግ አፀደቀ ሲባል ቀልባቸዉ የረገፈዉ ከላይ የተጠቀሱትን የወያኔ ጠባዮች በሚገባ ሰለሚያዉቁ ነዉ። ወያኔ ከአገር ዉስጥም ሆነ ከአገር ዉጭ የብድር ምንጮች በሚበደረዉ ገንዘብ መንገድ፤ ህንፃና ግድብ ሊሰራ ይችላል። እነዚህ ነገሮች በመሰራታቸዉ የሚከፋ ኢትዮጵያዊ ያለ አይመስለንም። ብዙ ኢትዮጵያዉያንን የሚከፋቸዉ ወያኔ በነሱ ስም በተበደረዉ ብድር በጀመራቸዉ ፕሮጀክቶች ሁሉ መጠቀም አለመቻላቸዉና በገዛ አገራቸዉ የበይ ተመልካች መሆናቸዉ ነዉ። እዚህ ላይ የህዳሴዉን ግድብ አንደ ምሳሌ ወስደን መመልከት እንችላለን። የህዳሴዉን ግድብ የእንጂኔሪንግ ኮንትራት ያለምንም ጨረታ አሸንፎ ከፍተኛ ትርፍ የሚያጋብሰዉ መስፍን ኢንጂኔሪንግ የተባለ የወያኔ ድርጅት ነዉ። ለህዳሴዉ ግድብ ማሰሪያ ሲሚንቶ የሚያቀርበዉ የወያኔዉ መሶብ ሲሚንቶ ፋብሪካ ነዉ። ለግድቡ ፕሮጀክት የትራንስፖርትና ማጓጓዣ አገልግሎት የሚሰጡት የአዜብ መስፍን ዘመዶች ናቸዉ;፡ ለህዳሴዉ ግድብ ሰራተኞች የምግብ አገልግሎት የሚሰጡት የወያኔ ኩባንያዎች ናቸዉ። የህዳሴዉን ግድብ እንደምሳሌ ወሰድነዉ እንጂ ኢትዮጵያ ዉስጥ በብድርም ሆነ በእርዳታ ገንዘብ በሚሰሩ ፕሮጀክቶች ሁሉ ተጠቃሚዉ ወያኔና ባለ ሟሎቹ ናቸዉ። ወያኔ እንደ ተራራ የቆለለዉን ብድር እስከነወለዱ የሚከፍለዉ ግን የኢትዮጵያ ህዝብ ነዉ።
የአለም ባንክንና አለም አቀፉን የገንዝብ ድርጅት ጨምሮ ብዙ የኤኮኖሚ ሳይንስ ጠበብቶች አገሮች በተለይ የዉጭ ዕርዳታ ጥገኛ የሆኑ ደሃ አገሮች ሉዓላዊ ቦንድን አገር ዉስጥ ለሚያጋጥማቸዉ የገንዘብ ጉድለት ማሟያ አድረገዉ እንዳይጠቀሙ በተከታታይ ያስጠነቅቃሉ። የወያኔ አገዛዝም ይህ ማስጠንቀቂያ በተከታታይ ከደረሳቸዉ መንግስታት አንዱ ነዉ። ሆኖም የማንንም ምክር የማይሰማዉ ወያኔ ጆሮ ዳባ ልበስ ብሎ ሉዓላዊ ቦንድ በመሸጥ መዘዙ ከትዉልድ ወደ ትዉልድ የሚተላለፍ ክፉ በሽታ እየዘራ ይገኛል። ወያኔ እስከዛሬ የተበደረዉ ብድር ምኑም ሳይከፈል ሉዓላዊ ቦንድ ከጀመረ በእናት አገራችን ላይ እንደ ትልቅ ተራራ የሚቆለለዉን ብሄራዊ ዕዳ የምንከፍለዉ እኛ የዚህ ዘመን ኢትዮጵያዉያን ብቻ ሳንሆን ገና ያልተወለዱ የልጅ ልጆቻችን ጭምር ናቸዉ።
ኢትዮጵያ ኤኮኖሚዋ ያልዳበረ ደሃ አገር በመሆኗ አበዳሪ አገሮችን ብድር ሰርዙልኝ ብላ ሳትወተዉት፤ የብድር ክፊያ ግዜዋን ሳታራዝም፤ ወይም የብድር ዉል ማሻሻያ ጥያቄ ሳታቀርብ እስከዛሬ የተበደረችዉንና ለወደፊትም የምትበደረዉን የዉጭና የአገር ዉስጥ ብድር የመክፈል ሃላፊነቷን ጤናማ በሆነ መልኩ መወጣት የምትል አገር አይደለችም። እንደዚህ የምንለዉ ደግሞ ወያኔንና ዘረኛ ስርዐቱን ስለምንጠላ ሳይሆን በሚከተሉት ማስረጃዎች ላይ ተንተርስሰን ነዉ። 1ኛ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ዕዳና አጠቃላይ አገራዊ ምርት (GDP) መጧኔ ቁጥሩ ከፍተኛ ነዉ።
ይህ ማለት ኢትዮጵያ የተቆለለባት ዕዳና ቤሄራዊ ገቢዋ ይቀራረባሉ፤ እኩል ናቸዉ ወይም ዕዳዋ ከገቢዋ ይበልጣል ማለት ነዉ። 2ኛ የአገራችን የዉጭ ብድርና የዉጭ ንግድ ገቢ መጣኔ እጅግ በጣም ከፍተኛ ነዉ። ይህ ማለት ደግሞ ምርታችንን ለአለም ገበያ አቅርበን የምናገኘዉ የዉጭ ምንዛሪ ከዉጭ አገር ዕቃ ሊገዛልን ቀርቶ የተበደርነዉን ብድር ወለዱንም መክፈል አይችልም ማለት ነዉ። 3ኛ የወያኔ አገዛዝ የብድር ዕዳና አገዛዙ አገር ዉስጥ በግብር መልክ የሚሰበስበዉ ገቢ መጣኔ እጅግ በጣም ከፍተኛ ነዉ። ቀለል ባለ አማርኛ የወያኔ አገዛዝ ሁሉንም ነገር ትቶ በሚሰበስበዉ ገንዘብ ዕዳዉን ብቻ ቢከፍል ከእዳዉ ለመላቀቅ ብዙ አመታት ይፈጅበታል።


    ለእናት አገራቸዉ ለኢትዮጵያ የሚጨነቁ ኢትዮጵጵያዉያን የወያኔ ፓርላማ በቅርቡ ያፀደቀዉን የሉዐላዊ ቦንድ ሽያጭ ህግ አጥብቀዉ የሚቃወሙት እነዚህን ሁሉ ገሃድ የወጡ የአገራችንን ችግሮች በሚገባ ስለሚያዉቁ ነዉ። ለኢትዮጵያና ለህዝቧ እንጨነቃለን ስንል ደግሞ እንደ ወያኔ “እኔ ከሞትኩ ሠርዶ አይብቀል” በሚል የንፉጎች አባባል ተዉጠን አይደለም። ለትናንትናዋ ኢትዮጵያ እንደተጨነቅን ሁሉ ለዛሬዋ፤ ለነገዋና እኛ ካለፍን በኋላ ለሚመጣዉ ኢትዮጵያዊ ትዉልድም እኩል እንጨነቃለን። ለዚህም ነዉ የሉዓላዊ ቦንድ ሽያጩን ብቻ ሳይሆን ወያኔ ያመጣብንን መዐት ሁሉ ለማስቆምና አገራችንን በትክከለኛ የእድገትና የዲሞክራሲ መሠረቶች ላይ ለማስቀመጥ ወያኔ መወገድ አለበት ብለን የሞት የሽረት ትግል የጀመርነዉ።

    Friday, December 5, 2014

    Prof. Mesfin Woldemariam: THE TPLF PROJECT FOR ETHIOPIA AND THE WORLD

    THE ACME OF EVIL IGNORANCE

    Editor’s Note: The word “Weyyane” (Tigre language) stand for the current Ethiopian dictatorial regime Tigrayan People’s Liberation Front (TPLF).
    by Mesfin Woldemariam*
    Thirty to fifty years ago the TWINS, the Shabia and the Weyyane discovered that one of their formidable and impregnable enemies was RECORDED HISTORY. In their boundless ignorance they believed they could wipe out RECORDED HISTORY by destroying the books on Ethiopia. They started their destructive campaign in London and Washington DC. The University of London and the Library of Congress were, I believe, their first targets. This is a consequence mainly attributable to IGNORANCE.THE ACME OF EVIL IGNORANCE
    Now that the TWINS are presumably incontestably in power they have resumed their campaign of destruction of accumulated knowledge. In Ethiopia the campaign started with the libraries in the Catholic Churches, The Municipality of Addis Abeba and perhaps in less known other organizations. Priceless books in these institutions and organizations were sold dirt-cheap by weight! Fortunately for Ethiopia their ignorance when combined with their greed led to a consequence partially opposite to their desired purpose of total destruction. Although some books were bought by those who would destroy them, some were also bought by those would preserve them.
    Now the weyyane possessed by ignorance and greed attacked the most important treasure of the country: THE ETHIOPIAN NATIONAL LIBRARY. The ancient books in this library were sold at a price of ten Birr (US $0.50) per kilo. Is this not a crime against humanity? Are the Western Powers free from this crime? Does this not demonstrate the TOTALITARIAN TYRANNY under which the Ethiopian people live? Is this not a war against knowledge, against science? Is this not a war against human progress? Is this not a childish attempt to start Ethiopian, indeed Human, history like animals from zero? Is this not a solid proof for the fact that there are no universities in Ethiopia?
    Jean Paul Sartre emphatically explains that every generation of all animals starts from zero with no accumulated experience to guide it. The weyyane project is to reduce all Ethiopians to their level of ignorance; however they fail to realize the universality of knowledge and science. Therefore, while they have American dollars, European Euros and English Pounds as well as Western war machines, they may believe they will succeed in keeping Ethiopians ignorant. Add to this the stifling of freedom of expression, internet, newspapers and other free and independent media there is surely a tremendous weight of ignorance on them; but they are not giving up the pursuit of knowledge. In fact the Project-Ignorance of the weyyane has become a challenge for Ethiopians to know more about themselves and the world. Today, thanks to the weyyane and the Derg there is inhabited continent where Ethiopians are not found.
    Most of all the Weyyane Project forgets or ignores the fact that Ethiopia was a symbol of FREEDOM AND INDEPENDENCE and a BEACON OF HOPE as well as an INSPIRATION OF COURAGE. A proud history of a proud people standing solidly for thousands of years has been reduced to a mere collection of tribes who were forcefully united by Minilik. The Weyyane Project ignores or forgets the tumultuous Sixteen Century that brought challenges which the Ethiopian people converted into opportunities. It is these challenges and opportunities that shaped present-day Ethiopia. The Weyyane Project has no notion about the resilience of the Ethiopian people. If the weyyane live to regret their ignorance and their stupidity, they will witness the rise of Ethiopia with vengeance!
    The following photographs of the covers of some of these priceless books are only a small sample of the consequence of the Weyyane Project making money by selling cheaply these books by weight.
    *****************
    Professor Mesfin Woldemariam is an Ethiopian peace activist and philosopher, who has been actively engaged in a peaceful movement to bring justice, equality and peace for all the people in his country.
    http://ecadforum.com/2014/12/03/the-tplf-project-for-ethiopia-and-the-world/

    የጣሊያን ፖሊስ ሰዉ አስተላላፊዎችን ያዘ

    አስሩ የኤርትራ ተወላጆች ከነመሪያቸው ለበርካታ ስደተኞች ሞት ተጠያቂዎች ናቸው

    Migrants arriving in Sicily where the people trafficking investigation was launched in May Photo Giovanni Isolino AFP


    የጣሊያን ፖሊስ በሕገ-ወጥ መንግድ ወደ አዉሮጳ ያሸጋግራሉ በማለት የተጠረጠሩ 10 የኤርትራ ተወላጆችን በቁጥጥር ሥር አዋለ። የካታኒያ-ሲሲሊ ፖሊስ እንዳስታወቀዉ ተጠርጣሪዎቹ የተያዙት ስደተኞችን ወደ አዉሮጳ የሚያሸጋግር ሕብረ-ሐገራት መረብ መኖሩን የሚጠቁም መረጃ ከደረሰዉ በኋላ ባደረገዉ አሰሳ ነዉ። በፖሊስ መግለጫ መሠረት ስደተኞቹን የሚያሻግረዉ መረብ ኤርትራ፤ ሊቢያ፤ ሌሎች ሰሜን አፍሪቃ ሐገራት እና ኢጣሊያ ድረስ የተዘረጋ ነዉ። ለአሸገጋሪዎቹ ገንዘብ እየከፈሉ ወደ አዉሮጳ ለመግባት  ሲሞክሩ በርካታ ስደተኞች ሜድትራንያን ባሕር ዉስጥ እየሰመጡ ሞተዋል።
    ፖሊስ ሰሞኑን የያዛቸዉን ተጠርጣሪ አሸጋጋሪዎች ካለፈዉ ግንቦት እስከ መስከረም ድረስ  23 የባሕር ላይ ጉዞዎችን አቀነባብረዋል በማለት ከሷቸዋል። ከተጓዦቹ ቢያንስ 240 ስደተኞች ሞተዋል። ከአስሩ ተጠርጣሪዎች ዘጠኙ ኅዳር 16 ቀን ኢጣሊያ ውስጥ የተያዙ ሲሆን አስረኛውና የቡድኑ መሪ ነው ተብሎ የሚጠረጠረው መዓሾ ተስፋማርያም ማክሰኞ ዕለት ጀርመን ውስጥ በቁጥጥር ሥር ውሏል፡፡ በተለይ ባለፈው ሰኔ ወር ከሊቢያ የሰሜን አፍሪካ ወደብ በበርካታ ተጓዦች ተጨናንቆ የተነሳውንና በኋላ በመስጠሙ ለ224 ስደተኞች ሞት ምክንያት የሆነውን ጀልባ የባህር ላይ ጉዞውን ሲጀምር መዓሾ ተስፋማርያም በአካል በመገኘት ሲቆጣጠር እንደነበር ፖሊስ አስታውቋል፡፡
    የካንታኒያ ሲሲሊ ፖሊስ ዘጠኝ ሶማሌዎችን በሕገወጥ መንገድ በማስተላለፍ ሥራ ላይ የነበረ 11ኛ የኤርትራ ተወላጅ ከዚሁ ጋር በቁጥጥር ሥር አውሏል፡፡ ሶማሌዎቹ በአንድ ቤት ውስጥ በአንድ የተቆለፈ ቤት የነበሩ ሲሆን ስምንቱ ለአቅመአዳም/ሔዋን ያልደረሱ መሆናቸውን የዜናው ዘገባ ጨምሮ ገልጾዋል፡፡ (ዜናው የተገኘው ከዶቸቨለ እና በእንግሊዝኛ ከሚታተም The Local የተሰኘ የጣሊያን የዜና መረብ ነው – Photo-Giovanni-Isolino-AFP)
    http://www.goolgule.com/italiy-police-arrested-10-eritreans-suspected-of-human-trafficking/

    ለለውጥ ፈላጊ ኢትዮጵያውያን በሙሉ

    የ9ኙ ፓርቲዎች የ24 ሰዓት ትዕይንተ ሕዝብ

    9 parties 1


    9 parties
    መልዕክቱን አባዝቶ ለሌሎች በማዳረስ ለ24 ሰዓቱ ሰልፍ ቅስቀሳ የበኩላችሁን እገዛ እንድታደርጉ ጥሪ እናስተላልፋለን!
    ያለመስዋዕትነት ድል የለም!
    http://www.goolgule.com/9-parties-24-hours-demonstration/

    በጦማርያን እና ጋዜጠኞች ላይ ተሻሽሎ ቀርቧል የተባለው ክስ ተሰማ

    zon e 9


    በእነ ሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ ተመስርቶባቸው ጉዳያቸው እየታየ ያሉት ጦማርያን እና ወዳጅ ጋዜጠኞች ላይ የተመሰረተው ክስ ተሻሽሎ ቀርቧል የተባለው የክስ ዝርዝር ከትላንት በስቲያ በልደታ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ተሰምቷል፡፡
    ዛሬ ህዳር 24/2007 ጠዋት በዋለው ችሎት፣ በጦማርያኑ እና ጋዜጠኞች ላይ ተሻሽሎ የቀረበው የክስ ዝርዝር በንባብ የተሰማ ሲሆን በክስ ወረቀቱ ላይ ከተመለከቱት ነጥቦች መካከል ግልጽ ያልሆኑ ነጥቦችን አካትቶ እንዲሰጥ ለአቃቤ ህግ ትዕዛዝ ተሰጥቶታል፡፡ ስለሆነም ሙሉ የክስ ወረቀቱ አርብ ለጠበቆቹ እንደሚደርስ ይጠበቃል፡፡
    በጠበቆቹ በኩል ክሱ ቀደም ብሎ ፍርድ ቤቱ በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት መሻሻሉን ለማረጋገጥ ያለፈው የፍርድ ቤቱ ብይን ግልባጭ እስካሁን እንዳልደረሳቸው በመግለጽ፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲደርሳቸው ጠይቀዋል፡፡ በዚህም የተነሳ የብይኑ ግልባጭ ሳይደርሰን ተሻሻለ የተባለው ክስ መሰማት የለበትም ብለው የነበር ቢሆንም፣ ክሱን አይታችሁ መቃወሚያ ካላችሁ አስተያየት እንድትሰጡበት እድል እንሰጣለን ያለው ፍርድ ቤቱ ክሱ እንዲሰማ አድርጓል፡፡
    ፍርድ ቤቱ ጠበቆቹ ያላቸውን አስተያየት ይዘው እንዲቀርቡ ለታህሳስ 7 ቀን 2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱ ታውቋል፡፡ (በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር)
    http://www.goolgule.com/the-improved-charges-on-the-bloggers-and-journalists-was-heard/

    “ሙሽራን ያላችሁ እስቲ እንያችሁ…”፤ [“የቲፎዞነት” ዘመን]

    (ኤፍሬም እንዳለ)

    Birds


    እንዴት ሰነበታችሁሳ!
    ሀሳብ አለን … ስብስባዎች ሁሉ … አለ አይደል… “እንዴት ሰነበታችሁ…” በሚል ብቻ ይከፈትና ወደ ጉዳዩ ይገባ! አሀ … “ክቡር እከሌ እከሌ፣” “ክብርት እከሊት እከሌ፣” “የተከበሩ እከሌ እከሌ” … ምናምን ሲባል የስብሰባው ሲሦ እያለቀ ነዋ! ለነገሩ … (“ለምን ይዋሻል!” የሚሉት ነገር ነበረ አይደል!) ብዙ ስብሰባዎች ላይ “እንትንህን እንደ ዳናኪል እንፋሎት እንዳላቦንልህ!” አይነት “የጉልበት ግማሹ ምላስ ነው…” ነገር በዝቷላ! (እኔ የምለው … አንዳንዱ መድረክ ላይ ወጥቶ እንዴት ነው እንዲህ ‘ልክ ልክ ማጠጣት’ የሚዋጣለት!)
    አንድ ወዳጃችን ሲነግረን አለቅየው ‘መጠመቁን’ ለበላዮቹ ለማስመስከር የማይሞክረው ነገር የለም፡፡ በተለይ ስብሰባዎች ላይ የሚናገረው ‘ቦተሊካ’ ነክ ንግግር ካርል ማርክስን ጢሙንና ጸጉሩን አርግፎለት ‘አይ ሮቦት’ ነገር ያስመስለው ነበር፡፡ እናላችሁ…በቅርብ ጊዜ ሚጢጢና የሰማይ ስባሪ አለቆችና አለቆች ነገሮችን ይሰበስብና … “እዚህ ክፍል ውስጥ የግንዛቤ ችግር ያለባችሁ ሰዎች እንዳላችሁ ይታወቃል፡፡ የኒኦ ሊበራሊዝም አስተሳሰብ መሥሪያ ቤታችን ውስጥ እንዲገባ መፍቀድ የለብንም…” ምናምን እያለ እሱ ራሱ ባልገባው ነገር ግራ እንዳጋባቸው ሲነግረን ነበር፡፡ ወዳጃችን በሆዳችን ግን ሁላችንም ቂ…ቂ… ብለናል…” ብሎናል፡፡
    እንግዲህ ጨዋታን ጨዋታ ያነሳው የለ…ለነገሩ በሆዳችን ቂ…ቂ… የሚያሰኙ ነገሮች መአት ናቸው፡፡ ጮክ ብለን ቂ…ቂ…ብንል አበሳ ነው፣ ዝም እንዳንል  እንዴት አስችሎን — በሆድ እንኳን እንሳቅ እንጂ!
    እኔ የምለው…እንግዲህ ጨዋታም አይደል…ይቺን ስሙኝማ፡፡ ሰውየው ንግግር እያደረገ ነው አሉ… እናላችሁ …ሦስት አራቱ አንድ ላይ በመናገር በየመሀሉ ያቋርጡታል፡፡ ብሽቅ ይላል፡፡ ተራ በተራ እንዲናገሩ ለማድረግም ምን ይላል… “ዛሬ እዚህ አዳራሽ ውስጥ ብዙ ደደቦች አሉ፡፡ በአንድ ጊዜ አንድ ደደብ ብቻ ቢናገር አይሻልም…” ይላል፡፡
    ተሰብሳቢዎቹ ምን ቢሉት ጥሩ ነው  “…እኮ ቀጥላ!” አሪፍ አይደል! ዘንድሮ በየቦታው “…እኮ ቀጥላ!” መባል የሚገባንን ቤቱ ይቁጠረን፡፡
    ስሙኝማ…“ክቡራንና ክቡራት፣ ደህና  ሁኑ፣ አትሁኑ የእኔ ጉዳይ አይደለም… ምን አግብቶኝ ነው እንደምን አደራችሁ የምለው? አሁን ወደ ስበሰባችን እንገባ፣” የሚል የክብር እንግዳ የመጣ ቀን… ያኔ የምር ዘመኑ እየገባን ነው ማለት ነው፡፡ እንደምን ብንውል ብናድር ማንም ግዴለውማ! አይደለም የእኛ ቤጤ የዓለም ሰዎችን ቀርቶ አባቶች እና ምዕመናን እንደምን አደራችሁ!… እንደምን ዋላችሁ!… እንደምን አመሻችሁ…” ሲለን እንኳን አንዳንዴ እንደው ግድ ሆኖባቸው ነው እንላለን፡፡
    እኔ የምለው…አርቲስቶች (እና ‘ሴሌብሪቲዎች’…) ምናምን … አለ አይደል…በሬድዮ፣ በቲቪ ምናምን ሲቀርቡ… “እወዳችኋለሁ…” የሚሏት ነገር አሁን፣ አሁን ቂ…ቂ…ቂ… ታሰኘን ጀምራለች፡፡ ልክ ነዋ… ከዘመድ፣ አዝማድ ጋር ሁሉ ተጠማምዶ “ሸንኮራ ጠበል ቢጠመቅ ይሻላል ወይስ አርሴማ ገዳም ቢገባ…” እየተባለ ምክክር እየተደረገበት… እኛን “እወዳችኋለሁ…” ሲለን አሪፍ አይደለም፡፡ እኔ የምለው…እግረ መንገዴን የሆነ ነገር ትዝ አለኝማ…አሁን አንድ አንድ ‘ቶክ ሾው’ ምናምን የሚባሉ ዝግጅቶች ላይ እየተለመደች የመጣች አባባል አለች፡፡ “እንዲህ ያሳመረኝ እንትን እንትን ቡቲክ ነው…” አይነት ነገር ይባላል፡፡ ደስ የሚል ዘመን ነው፡፡ ድሮ አፍ አውጥቶ “አምራለሁ…” ቢል የሰፈር ዕድር ሁሉ ባያድምበት ነው! ሀሳብ አለን…አንዳንድ ጊዜ… አለ አይደል… “ይህን የሚያምር ልብስ ያለበሰኝ…” ይባልልንማ! አሀ…እንደዛ ስናስብስ!  ቂ…ቂ…ቂ…
    ስሙኝማ…ጨዋታን ጨዋታ ያነሳው የለ…ዘንድሮ የ‘ቲፎዞ ነገር’ አልበዛባችሁም! የምር አስቸጋሪ ነው…ጥሩ ነገር መሥራት ብቻውን በቂ ያልሆነበት ዘመን ላይ ደርሰናል፡፡ “ስማ እንትን ኤፍ ኤም የምታውቀው ሰው የለህም!” መባባል ለመደብን፡፡ ምን ይደረግ!…‘ቲፎዞ’ ከሌለን ነገርዬው…አለ አይደል…“ከሌለህ የለህም…” አይነት ይሆናል፡፡
    እናላችሁ…አሪፍ መጽሐፍ መጻፍ ብቻ፣ አሪፍ ዘፈን መዝፈን ብቻ፣ ብዙ የግጥም መድበል ማውጣት ብቻ፣ ጥሩ መተወን ብቻ ወዘተ. በቂ አይሆንም፡፡ በምላሳቸው “ወንድምና እህትን ማጋባት ይቻላል…” የሚባሉ አይነት ‘ሎቢይስቶች’ ያስፈልጋሉ፡፡
    የምር ግን…አንዳንድ ሥራዎች ቆይተርው እናንተ ዘንድ ይደርሱና… አለ አይደል… “ይሄን ነገር እንዴት እስከ ዛሬ ድረስ አላየሁትም…” አይነት ነገር ትላላችሁ፡፡ መልሱ አጭር ነው… ‘ኖንቼ ቲፎዞ!’
    ስሙኝማ… ብዙ ሠርግ ምናምን ላይ አይታችሁልኛል…ጠጁ ምናምኑ በ‘መሬት በታች መተላለፊያዎች’ (ቂ…ቂ…ቂ….) የሚሄደው ወደሚታወቁ ሰዎች፣ ወደ ሰፈር ሰዎች፣ ወደ መሥሪያ ቤት ባልደረቦች፡ ምናምን ነው፡፡ ዘመኑ የ‘ቲፎዞ’ ነዋ!
    ደግሞላችሁ…አንዳንድ ቦታ የደረጃም ሆነ የደሞዝ እድገት የሚገኘውም በ‘ቲፎዞ’ ነው ይባላል፡፡ ዘንድሮ ደግሞ ለ‘ቲፎዞነት’ የሚያመቹ መመዘኛዎች በዝተዋል፡፡ ከሁሉ በላይ ግን ‘የአገር ልጅነት’ ዋናው ነው፡፡ እኔ እኮ አንዳንዶቹማ ከሰፊው ‘የአገር ልጅነት’ ወደ ሰፈርነት ሲወርዱ ስታዩ ነገ ደግሞ ‘በግቢ’ እንዳይሆን ትላላችሁ፡፡
    ስሙኝማ…ዘንድሮ መንደሮች ‘መደብ’ የሚለይባቸው እየሆኑ አይደል… እዛም ለየት ያሉ ‘ቲፎዞነቶች’ ይኖራሉ ማለት ነው፡፡ ለመደብና! “ዘመድ ከዘመዱ…” ምናምን የሚባል ነገረ አለ አይደል፡፡ ይቺን ስሙኝማ… ሰውየው አንዱን ጎብኚ እያዟዟረ ኒው ዮርክን ያስጎበኘው ነበር፡፡ እናላችሁ… አንድ ቤተ መንግሥት የሚያክል መኖሪያ ቤት ይደርሳሉ፡፡
    አስጎብኚውም እንዲህ ይላል… “ይህ በኒው ዮርክ እጅግ ሀብታም የሆነው ሰው መኖሪያ ቤት ነው፡፡ አብሳዩ ጀርመናዊት ነች፣ የቤት ሠራተኛዋ ፈረንሳዊት ነች፣ ዕቃ አመላላሹ ጃፓናዊ ነው፣ ሜካኒኩ ስኮትላንዳዊ ነው፣ የቤት ጽዳት ሠራተኛዋ ስዊድናዊት ነች፣  ፀሀፊው ደግሞ አሜሪካዊት ነች፡፡”ጎብኚው ሲመልስ ምን አለ መሰላችሁ… “ይሀ መኖሪያ ቤት ሳይሆን የዓለም ፍርድ ቤት ነው፡፡” ኧረ እዚህ በመጣ፣ ቤተ መንግሥት ሊያስንቁ ምንም የማይቀራቸው ቤቶች ባይኖሩ ነው! እንደውም አንዳንዶቹ እንዲህ አይነት ቤቶች ባሉባቸው አካባቢዎች ሲያልፉ የመኪና ጥሩምባ ማሰማት ክልክል እንደሆነ በቀደም ወዳጄ እየነገረኝ ነበር፡፡ “ገና ምን አይተሽ!” አለ ባል ሚስት ላይ ሲፎክር!
    እኔ የምለው…እግረ መንገዴን…ደግሞ የት አካባቢ ነው…“ከጥራት በታች የተሠራ መንገድ እየፈረሰ ነው…” ምናምን ሲባል ሰማን ልበል! …‘ማፍረስ’ ቀላል የሆነባት አገር! ሀሳብ አለን… ለማፍረስ ጥቅም ላይ የሚውሉ ዲጂኖ ምናምን አይነት መሣሪያዎች ከውጪ ይገቡ እንደሆነም፣ እዚሁ ይመረቱ እንደሆነም ብዛታቸው ይቀነስልንማ! አሀ…ችግር የሚፈጥርው እኮ ‘እንደ ልብ’ የሚገኝ ነገር ነው፡፡ ለነገሩ ዲጂኖውም ቢጠፋ… አለ አይደል… “በጥፍሬ እየቧጠጥሁ ካላፈረስኵ ሞቼ እገኛለሁ…” የምንል አንጠፋም፡፡ ዘመኑ እንዲህ ነዋ!
    እናላችሁ… ‘የቲፎዞነት’ ዘመን ነው፡፡ እኛ “የለም…” የተባልነው የለስላሳ መጠጥ አይነት እዛው በዛው ለ‘ቲፎዞ’ ሲሰጥ ያየንበት ሬስቶራንት ነገር አለ፡፡
    ታዲያላችሁ…በየስብሰባውም የሚገጥማችሁ ነገር ‘የቲፎዞ’ ነገር ነው፡፡ ያው ያቺ ከድሮ ጀምሮ የተለመደች ‘በተንተን ብሎ የመቀመጥ’ ስትራቴጂ አለች አይደል… ሰበሳቢውም “አንድ ከዚህ ጫፍ፣ አንድ ከመሀል፣ አንድ ከወዲያኛው ጫፍ…” ምናምን ይልና ስትራቴጂያዊ ቦታቸውን የያዙ ‘የቲፎዞ ስብስቦች’ ….ይቆጣጠሩታል፡፡
    እናላችሁ… ሰዉ ከሁሉ አስቀድሞ “እንትን መሥሪያ ቤት ሰው ታውቃለህ…” ምናምን የሚባለው ዘመኑ ‘የቲፎዞ’ ስለሆነ ነው፡፡
    አሁን፣ አሁን የሆነ ነገር፣ በተለይ የጥበብ ሥራ፣ ሲያደንቁልን ከሥራው ይልቅ “ሰውዬዋ ፕሮፓጋንዳ እየነሰነሰች ነው እንዴ!” እንላለን፡፡
    እናማ… “ሙሽራን ያላችሁ እስቲ እንያችሁ…” አይነት የመጠቃቀስ፣ በምስጢር የመጠራራት ‘ቲፎዞነት’… አለ አይደል… ‘በጨው ደንደስ በርበሬውን እያስወደሰ’ ስለሆነ ጦሳችንን ይዞ ይሂድልንማ!
    ደህና ሰንብቱልኝማ!
    http://www.goolgule.com/age-of-favoritism/