Wednesday, October 22, 2014

ችግር ፈጣሪ በተባሉ የግንባታ ግብዓት አቅራቢዎች ላይ ዕርምጃ እንደሚወሰድ ማስጠንቀቂያ ተሰጠ


  • 73
     
    Share
addis-ababa-realethiopia-141የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለመኖሪያ ቤት ግንባታ ደካማ የሥራ አፈጻጸም ከፍተኛ አስተዋጽኦ አላቸው ያላቸውን ጠጠር አምራቾች አስጠነቀቀ፡፡ አስተዳደሩ ጠጠር አምራቾቹ በሕጋዊ መንገድ ሥራቸውን የማያካሂዱ ከሆነ ዕርምጃ እወስዳለሁ ብሏል፡፡
አስተዳደሩ ይህንን ማስጠንቀቂያ የሰጠው በጠጠር አቅርቦት ላይ የተከሰቱ ችግሮችን ለመፍታት፣ ጥቅምት 11 ቀን 2007 ዓ.ም. በጠራው ስብሰባ ላይ ነው፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ አባተ ስጦታው በስብሰባው ላይ እንዳሉት፣ በጠጠር አቅርቦት ላይ እየተፈጠሩ ባሉ ችግሮች እጃቸው ያለበት አካላት ወደ ሕጋዊ መስመር መግባት አለባቸው፡፡ አቶ አባተ አስተዳደሩ የማጣራት ሥራ ሠርቶ አፋጣኝ ዕርምጃ እንደሚወስድ አስገንዝበው፣ በዚህ ተግባር የተሰማሩ የአስተዳደሩም ሆነ አቅራቢ ኩባንያዎች ወደ ሕጋዊ መስመር እንዲገቡ አሳስበዋል፡፡
‹‹በእኛ ሠራተኞች ጭምር ማጭበርበርና ሌብነት አለ›› በማለት አቶ አባተ የጉዳዩን አደገኝነት አስታውቀዋል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 200 ኩባንያዎች የማዕድን ፈቃድ በማውጣት 370 ሔክታር መሬት ለጠጠር ማምረቻ ወስደዋል፡፡ አስተዳደሩ ለእነዚህ ኩባንያዎች በቂ መሬትና የኮንስትራክሽን ማሽኖችን ጨምሮ ለተለያዩ ሥራዎች ብድር አመቻችቶ መስጠቱን ገልጿል፡፡
አስተዳደሩ እነዚህን ድጋፎች ለአምራቾቹ ያቀረበው በከተማው እየተካሄዱ ላሉት ሦስት የመኖሪያ ቤት ፕሮግራሞች የሚያስፈልገውን ጠጠር ለማግኘት መሆኑን ገልጾ፣ ነገር ግን ይህ ዕቅድ በሕገወጦች ምክንያት እየተስተጓጎለ መሆኑን አስረድቷል፡፡
ስብሰባውን የመሩት አቶ አባተ እንደገለጹት፣ ከእነዚህ ኩባንያዎች ውስጥ አብዛኛዎቹ የወሰዱትን የማምረቻ ቦታ ለሦስተኛ ወገን አሳልፈው ሰጥተዋል፡፡ አምራቾቹ ለቤቶች ግንባታ ጠጠር ማቅረብ ሲገባቸው ለሌሎች ፕሮጀክቶች ቅድሚያ እንደሰጡና ‹‹በተለይም ሰው ሠራሽ ዋጋ በመፍጠር የዋጋ ንረት እንዲከሰት አድርገዋል፤›› ሲሉ ወቅሰዋል፡፡
በዘርፉ ወደ ሦስተኛ ወገን ማስተላለፍ፣ ከወሰዱበት ዓላማ ውጪ ለሆነ ተግባር ማዋል አስተዳደሩ ያነሳቸው ችግሮች ሲሆኑ፣ ከተሰብሳቢዎች ውስጥ ‹‹መሬትን ከነግዳጁ ለሦስተኛ ወገን ማስተላለፍ ችግሩ ምንድነው?›› የሚል ጥያቄ ቀርቧል፡፡
አቶ አባተ እንዳሉት መሬት እየያዙ ወደ ሦስተኛ ወገን ማስተላለፍ በፍፁም አይቻልም፡፡ ‹‹እኛ የምንፈልገው ኪራይ ሰብሳቢ ሳይሆን ልማታዊ ባለሀብት ነው፤›› በማለት ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ የአስተዳደሩ መሥሪያ ቤቶች በመቀናጀት የወሰዱትን መሬት ላልተገባ ተግባር ያዋሉ አምራቾች ላይ ዕርምጃ እንዲወሰዱ አቶ አባተ መመርያ ሰጥተዋል፡፡
በተሰብሳቢዎቹ ሥራቸውን ለማካሄድ የመሠረተ ልማት አለመሟላት ችግር እንደሆነ ተነስቷል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም አስተዳደሩ ግዥ የሚፈጽምበት ዋጋ ከማምረቻ ዋጋ ንረት ጋር እንደማይገናኝ የሚጠቅሱም አሉ፡፡ ይህንን የዋጋ ንረት ለመቀነስ የትራንስፖርት ሥራ ውስጥ ለመግባት እንዲፈቀድላቸው ጥያቄ አቅርበዋል፡፡ የመሠረተ ልማት ችግሮች ተብለው ከቀረቡት ውስጥ የመንገድ አውታር፣ የኤሌክትሪክና የውኃ መስመር አለመኖር ተጠቅሰዋል፡፡
በተለይ በኤሌክትሪክ በኩል ያለው ችግር ጎልቶ የወጣ ሲሆን፣ ባለሀብቶቹ ከሁለት ዓመት በፊት ክፍያ ፈጽመው የኤሌክትሪክ ኃይል ይለቀቃል ብለው ቢጠብቁም አለመለቀቁን ተናግረዋል፡፡
አስተዳደሩ በኤሌክትሪክ ኃይል በኩል ያለውን ችግር ለመፍታት ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር እየሠራ መሆኑን ጠቅሶ፣ ውኃና መንገድ ግን በተቻለ መጠን ባለሀብቶቹ ራሳቸው መሥራት እንደሚኖርባቸው አስገንዝቧል፡፡
የአዲስ አበባ አስተዳደር በተያዘው የበጀት ዓመት 125 ሺሕ ቤቶችን እየገነባ መሆኑን ገልጾ፣ ለእነዚህ ግንባታዎች 1.3 ሚሊዮን ሜትር ኩብ ጠጠር እንደሚያስፈልግ አስታውቋል፡፡
ባለሀብቶቹ ይህንን ጠጠር ማቅረብ የማይችሉበት አሠራር ከቀጠለ፣ የራሱን ማሽኖች በመግዛት ወደ ሥራ ሊገባ እንደሚችል አስተዳደሩ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል፡፡ የአዲስ አበባ ኮንስትራክሽንና ቤቶች ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌታቸው ኃይለ ማርያም እንደገለጹት፣ አስተዳደሩ ወደ ጠጠር ምርት የሚገባው የባለሀብቶች የሥራ አፈጻጸም ደካማ ከሆነ ብቻ ነው፡፡
Source:: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/35617

Rotary announces US$2 million in grants to fight polio in Ethiopia

By Rotary International
240x_mg_bfv2ylk88s_rotaryADDIS ABABA, Ethiopia, October 22, 2014/African Press Organization (APO)/ — In advance of the Oct. 24 observance of World Polio Day 2014, Rotary (http://www.rotary.org) announces US$2 million in grants to combat polio in Ethiopia. The funds – part of Rotary’s broader contribution of $44.7 million to end the paralyzing disease worldwide – will be used by UNICEF to support high quality polio immunization campaigns.
Logo: http://www.photos.apo-opa.com/plog-content/images/apo/logos/rotary.png
For the second year in a row, Rotary will mark World Polio Day with a livestream event featuring a global status update on the fight to end polio as well as an array of guest speakers and performers. The event, which will stream live from Chicago, Ill., can be viewed at endpolio.org.
In Ethiopia, Rotary’s PolioPlus program will celebrate World Polio Day by hosting a commemoration ceremony in conjunction with the World Health Organization, UNICEF and the Ethiopian Ministry of Health. The PolioPlus program will also host a World Polio Day march to mark the occasion and raise awareness of the disease.
Polio is set to become the second human disease ever to be eliminated from the world (smallpox is the first). To date, Rotary has helped 193 countries stop the transmission of polio through the mass immunization of children. Rotary’s new funding commitment targets countries where children remain at risk of contracting this incurable, but totally vaccine-preventable disease.
There are only three countries in the world where the wild poliovirus has never been stopped: Nigeria, Pakistan and Afghanistan. However, the virus from these countries can travel and lead to outbreaks in other parts of the world. In fact, last year the majority of the world’s polio cases stemmed from outbreaks in countries that had previously been polio-free. In particular, an outbreak in the Horn of Africa resulted in 217 cases in 2013, including nine in Ethiopia.
“We are pleased it appears we have halted the polio outbreak in Ethiopia,” said Tadesse Alemu, Rotary’s National PolioPlus Chair for Ethiopia, referencing the country’s only case this year, recorded more than nine months ago on 14 January. “However, given the mobility of our global society, until polio is gone from Africa – and the world – Ethiopian children will remain at risk for this disease.”
Rotary provides grant funding to polio eradication initiative partners UNICEF and the World Health Organization, which work with the governments and Rotary club members of polio-affected countries to plan and carry out immunization activities. Mass immunizations of children via the oral polio vaccine mustcontinue until global eradication is achieved.
Approximately $18.5 million will go to the three remaining polio-endemic countries: Afghanistan, Nigeria and Pakistan. An endemic country is one where the wild poliovirus has never been stopped. Another $9.5 million is marked for previously polio-free countries currently reporting cases “imported” from the endemic countries: Cameroon, Ethiopia, and Somalia. And $10.4 million will go to polio-free countries that remain at risk of reinfection: Democratic Republic of Congo, India, Niger, South Sudan, and Sudan.
The remaining $6.3 million will go toward polio eradication research.
Funds for these countries will be used to fight existing polio outbreaks, or to conduct campaigns to protect against the high risk for reinfection. Countries experiencing conflict, like Ethiopia’s neighbor Somalia, are at particular risk for polio outbreaks.
To date, Rotary has contributed more than $1.3 billion to fight polio. Through 2018, the Bill & Melinda Gates Foundation will match two-to-one every dollar Rotary commits to polio eradication (up to $35 million a year). As of 2013, there were only 416 confirmed polio cases in the world, down from about 350,000 a year when the initiative launched in 1988.
Distributed by APO (African Press Organization) on behalf of Rotary International.
Contact:
Stephanie Tobler Mucznik
+41 (0)44 387 7116
Stephanie.ToblerMucznik@rotary.org
About Rotary
Rotary (http://www.rotary.org) brings together a global network of volunteer leaders dedicated to tackling the world’s most pressing humanitarian challenges. Rotary connects 1.2 million members of more than 34,000 Rotary clubs in over 200 countries and geographical areas. Their work improves lives at both the local and international levels, from helping families in need in their own communities to working toward a polio-free world. In 1988, Rotary was joined by the WHO, UNICEF and the CDC to launch the Global Polio Eradication Initiative. Visit http://www.rotary.org and http://www.endpolio.org for more about Rotary and its efforts to eradicate polio. Video and still images will be available on the Rotary Media Center (http://goo.gl/DS86iD).
http://www.zehabesha.com/rotary-announces-us2-million-in-grants-to-fight-polio-in-ethiopia/

Friday, October 17, 2014

Gunmen kill three Ethiopian peacekeepers in Sudan’s Darfur

(Reuters) – Gunmen killed three Ethiopian peacekeepers who were guarding a water hole in Sudan’s strife-torn Darfur region on Thursday, their force said.
Two of the soldiers died at the scene in Korma, north Darfur, and a third died later from his wounds in Khartoum, said the joint U.N./African Union UNAMID peacekeeping mission. The attackers stole the Ethiopians’ patrol vehicle, it added.
news
“This has been a bloody October for UN Peacekeeping,” UN Secretary-General Ban Ki Moon told reporters in New York.
“In Darfur, Mali and the Central African Republic, we have lost 14 peacekeepers in hostile acts – nearly one per day.”
A total of 61 UNAMID peacekeepers have been killed in action since their force was set up in 2007 to stem violence in Sudan’s western region.
Darfur was plunged into turmoil in 2003 when mostly non-Arab rebels took up arms against the government, accusing it of neglecting the arid region, and Khartoum mobilised mostly Arab militias to crush the uprising.
The situation has since subsided into chaos with skirmishes involving bandits, rival insurgent splinter groups, warring tribes and lawless militias.
UNAMID’s joint U.N./African Union Special Representative Abidoun Bashua called on Khartoum to bring Thursday’s attackers to justice.
“An attack on peacekeepers constitutes a war crime and is punishable under international criminal law,” Bashua said.
(Reporting By Khalid Abdelaziz; Writing by Shadi Bushra; Editing by Andrew Heavens and Ken Wills)http://www.zehabesha.com/gunmen-kill-three-ethiopian-peacekeepers-in-sudans-darfur/


ሰማያዊ፣ መኢዴፓና ኢብአፓ የምርጫ ቦርድን ስብሰባ ረግጠው ወጡ

eth election

ምርጫ ቦርድ በጊዜ ሰሌዳ ላይ ለመወያየት በጊዮን ሆቴል የጠራውን ስብሰባ “ጥያቄዎቻችን የሚመልስ አይደለም” በሚል የሰማያዊ ፓርቲ ተወካዮች ስብሰባውን ረግጠው መውጣታቸውን መዘገባችን ይታወሳል፡፡ ከሰማያዊ ፓርቲ በተጨማሪም የመላው ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (መኢዴፓ) እና የኢትዮጵያ ብሄራዊ አንድነት ፓርቲ (ኢብአፓ) ተወካዮች ስብሰባውን ረግጠው ወጥተዋል፡፡ ፓርቲዎቹ በትናንትናው ዕለት ከምርጫ 2007 ዓ.ም በፊት ውይይት ሊደረግባቸውና ሊፈቱ ይገባል ያሏቸውን ጥያቄዎች ለምርጫ ቦርድ ያስገቡ ቢሆንም በዛሬው ስብሰባ በደብዳቤ ካሳወቋቸው ችግሮች ይልቅ የጊዜ ሰሌዳ ቅድሚያ የተሰጠው በመሆኑ የምርጫ ምህዳሩን ላይ የሚያመጣው ለውጥ የለም ብለው ስብሰባውን ረግጠው መውጣታቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
ስብሰባውን ረግጠው ከወጡት መካከል የኢትዮጵያ ብሄራዊ አንድነት ፓርቲ (ኢብአፓ) ዋና ጸኃፊ ወ/ት መሊሃ ጀሃድ “ትናንትና 12 ፓርቲዎች ሆነን ፈርመን ያስገባነው ደብዳቤ ነበር፡፡ በዚህ ደብዳቤ ባነሳናቸው ጥያቄዎች ላይ መልስ ካልተሰጠን በረቂቅ የጊዜ ሰሌዳው ላይ እንደማንነጋገር ገልጸን ነበር፡፡ ቦርዱ ደግሞ ትናንትና ባስገባነው ደብዳቤ ላይ ከመነጋገርና ለጥያቄዎቹ መልስ ከመስጠት ይልቅ በጊዜ ሰሌዳው ላይ ነው የምንነጋገረው አለን፡፡ ምርጫ ቦርድ ኃላፊዎች ስለ ጊዜ ሰሌዳው እንድንነጋገር ሲያደርጉ እኛ በአካሄድ ጥያቄዎቻችን መልስ እንዲሰጥ ጠየቅን፡፡ የቦርዱ ተወካዮች እሱን በሌላ ጊዜ ስብሰባዎች ላይ እንፈታዋለን፣ ዛሬ ስለ ጊዜ ሰሌዳው እንነጋገር በማለታቸው ስብሰባውን ረግጠን ወጥተናል” ስትል ረግጠው የወጡበትን መነሻ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጻለች፡፡
eth electionበተመሳሳይ የመኢዴፓ ሊቀመንበር አቶ ኑሪ ሙደሂር “ምርጫ ቦርድ ነጻና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ አደርጋለሁ የሚለው አባባሉ ተግባራዊ እንዲሆን ጥያቄዎችን አቅርበን ነበር፡፡ ይህን ጥያቄ የዛሬ 5 አመትም ጠይቀናል፡፡ ትናንትም በጋራ በደብዳቤ አስገብተናል፡፡ ገዥው ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ ከጀመረ 5 አመቱ ነው፡፡ ይህን ቅስቀሳ የሚያደርገው በመንግስት ገንዘብ ነው፡፡ የእኛ ጥያቄ የምርጫ ምህዳሩ መስፋት አለበት ነው፡፡ ትርጉም ያለው ምርጫ መደረግ አለበት ነው የእኛ እምነት፡፡ ይህን ለማድረግ የሚያስችሉ ጥያቄዎችን ለመመለስ ፈቃደኛ ስላልሆኑ ነው እኛ ስብሰባውን ረግጠን የወጣነው” ብለዋል፡፡
ሌላኛው የመኢዴፓ ተወካይና የፓርቲው ዋና ጸኃፊ አቶ ዘመኑ ሞላ በበኩላቸው “እነሱ ካቀረቡት የጊዜ ሰሌዳ ይልቅ የሚቀድመው ሜዳውን ማስፋት ነው፡፡ ትናንትና 12 ፓርቲዎች ተፈራርመን ያስገባነው ደብዳቤ ነበር፡፡ እኛም ቀድመን በተነጋገርነው መሰረት የጊዜ ሰሌዳው ጉዳይ ቀዳሚ አጀንዳ መሆን የለበትን የሚል አቋም ይዘናል” ሲሉ ስብሰባውን ካዘጋጀው ምርጫ ቦርድ ጋር ያላቸውን ልዩነት ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
ምርጫ ቦርድ በሚቀጥለው ስለ ችግሮቻችሁ ቁጭ ብለን እንወያያለን በሚል የማባበል ስራ እንደያዘ የገለጹት አቶ ዘመኑ “የ2002ትን ምርጫን ገምግመናል፡፡ ፓርቲዎች ያስገባነው ደብዳቤ አለ፡፡ አሁንም ገዥው ፓርቲ ከመቼውም ጊዜ በባሰ ሜዳውን እያጠበበና ራሱ ብቻ እየተጫወተበት ይገኛል፡፡ ትክክለኛ ምርጫ ለማድረግ ከታሰበ እናንተም ከገዥው ፓርቲ ጋር ያላችሁን ግንኙነት ቆም ብላችሁ አስቡበት ብለናቸዋል፡፡ ያቀረብናቸው ጥያቄዎች ቅድሚያ ስላልተሰጣቸው ስብሰባውን ረግጠን ለመውጣት ተገደናል” ብለዋል፡፡
ዘግይቶ በደረሰን መረጃ የኢትዮጵያ ማህረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህብረት አንድነት ፓርቲ ተወካይ ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስም ስብሰባውን ረግጠው መውጣታቸው ተግልጾአል፡፡
በትናንትናው ዕለት 12 የፖለቲካ ፓርቲዎች በጋራ ከምርጫ ከጊዜ ሰሌዳው በፊት በውይይት መፈታት አለባቸው ብለው ያመኑባቸውን ጥያቄዎች ለምርጫ ቦርድ በደብዳቤ መጠየቃቸው ይታወሳል፡፡ (ምንጭ፤ ነገረ ኢትዮጵያ)http://www.goolgule.com/ethiopian-parties-walked-out-of-election-board-meeting/


Wednesday, October 15, 2014

በግል ፕሬሶች ላይ የተከፈተው ዘመቻ ለነፃነት የቆሙ ዜጎችን አንገት የሚያስደፋ አይሆንም !!!



ከአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የተሰጠ መግለጫ

******************
በግል ፕሬስ ጋዜጠኞች ላይ እየደረሰ ያለው እስር ሀገር ለቀው እንዲሰደዱ የሚደረገው አሰተዳደሪዊ ጫና እንዲሁም የግል ሚዲያው ዘርፍ ላይ እየተፈፀመ ያለው ሴራ ገዢው ፓርቲ በህገ ወጥ መንገድ በስልጣን ለመቆየት ከሚወሰዳቸው እርምጃዎች አንዱ እንደሆነ እንረዳለን፡፡ ገዥው ፓርቲ በሚከተለው ከዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብ ያፈነገጠና ሴራን ማዕከል ያደረገው ፖለቲካ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ ከመሄዱም ባሻገር በአደባባይ የሚከወን አሳፋሪ ድርጊት ሆኗል፡፡ ይህም የሚያሳየው ገዢው ፓርቲ በስልጣን የሚቆየው በሃሳብ የበላይነት ሳይሆን ለጊዜው በቁጥጥሬ ስር ናቸው በሚላቸው የመንግሰት መዋቅሮችን በመጠቀም መሆኑ ይታወቃል፡፡
ፓርቲያችን የኢህአዴግ የ2007 ዓ.ም ሀገር አቀፍ ምርጫ ዘመቻ አካል እንደሆነ የሚያምነው ማሳደድና ማሰር በጋዜጠኞች ላይ ተጠናክሮ መቀጠሉ ገዢው ቡድን አሁንም መግባባት የተሞላበት ምርጫ እንዲከናወን ፍላጎት እንደሌለው ያረጋግጣል፡፡ የዚህ ዓይነት ድርጊትን የኢትዮጵያ ህዝብ ብሶት ከማባባስ ውጭ የሚጨምረው ፋይዳ ይኖራል ብለን አናምንም፡፡ በዚህ የተነሳ ለነፃነት የቆሙ ዜጎች አንገት ያሰደፋል ብለንም አናምንም፡፡
በዓለማቀፍ ደረጃ አንገታችንን እንድንደፋና እንደ ዜጋ እንድንሸማቀቅ በሚያደርግ መልኩ በተወሰደው አማራጭ የግል ፕሬስ የማጥፋት እርምጃ በርካታ ጋዜጠኞች ለሚወዷት ሀገራቸው ጀርባቸውን ሰጥተው ስደትን ምርጫቸው አድርገዋል፡፡ በቅርቡ ያለወገን ድጋፍና ያላስታማሚም የስደት ሰለባ የሆነው የግል ፕሬስ ባልደረባ ጋዜጠኛ ሚሊዮን ሹሩቤ በተሰደደ በጥቂት ጊዜያት ውስጥ ህይወቱ ማለፉ አሳዛኝ ክሰተት በመሆኑ ፓርቲያችን ለቤተሰቦቹና ወዳጆቹ አዘኑን ይገልፃል፡፡ ለዚህም ሃላፊነት በጎደለው ሁኔታ ጋዜጠኞች በሀገራቸው ላይ የመስራት መብታቸው ተገፍፎ በሚደርስባቸው ወከባ ከሀገር እንዲሰደዱ ያደረገው መንግስት ሃላፊነቱን መውሰድ አለበት፡፡ ገዢው ቡድን የሚሊዮንን ሞተ አስመልክቶ ለሚነሳ የህዝብ ጥያቄ መልስ እንዲሰጥ እንፈልጋለን፡፡
በተሰደዱ ጋዜጠኞች ላይ የሚደርሰውን እንግልት ሰምተን ሳናበቃም አልሰደድም ባሉ ጋዜጠኞች ላይ የሚደርሰው ጥቃት ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ የገዥውን ፓርቲ አምባገነንነት ሳይታክት በግልፅ የሚተቸው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በሀገራችን ህገ መንግሰት አንቀፅ 29 በተደነገገው መስረት ሃሳቡን በነፃነት ስለገለፀ ብቻ ህግን ተገን ተደርጎ በተከፈተበትና ለአመታት ፍርድ ቤት ሲመላለስ በኖረበት ክስ ወቅቱን ጠብቆ እንደሚፈነዳ ፈንጂ የምርጫ ወቅቱን ጠብቀው ጥፋተኛ በማለት ወደ ወህኒ ቤት ማውረድ ፖለቲካዊ እርምጃ መሆኑን አንጠራጠርም፡፡ ፓርቲያችን ይህን በህግ ሽፋን የሚፈፀም የፖለቲካ ሸፍጥ በቁርጠኝነት መታገሉን እንደሚቀጥልና እንደዚህ አይነቱ ግፍ ሊቆም የሚችለው ህዝቡን በማስተባበር በሰላማዊ ትግል አምባገነኑን ስርኣት መቀየር ሲቻል እንደሆነ ያምናል፡፡ ስለዚህ የኢትዮጵያ ህዝብ ከጎናችን በመቆም የዜጎች የመከራ ዘመን እንዲያጥርና ፍትሃዊነት እንዲሰፍን እንድናደርግ ሃገራዊ ጥሪ እናስተላልፋለን፡፡
በግፍ የታሰሩ ጋዜጠኞች፤ ጦማሪያንና ፖለቲከኞች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱም እንጠይቃለን፤ ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ከገዥዎች በችሮታ የሚሰጥ እንዳለሆነ ህዝቡ የሚገነዝብና መንግስት በሚወሰደው እርምጃ የተነሳም አንገቱን የሚደፋ አንድም ነፃነት ወዳድ ዜጋ እንደማይኖር እናረጋግጣለን፡፡
በመተባበር የኢትዮጵያውያንን መከራ ዘመን እናሳጥር!!
UDJ














http://www.zehabesha.com/amharic/archives/35435








Kenya: Embu Court Sends 11 Illegal Ethiopian Immigrants to Jail for Three Months

ELEVEN Ethiopians who were arrested in Mbeere South recently leading to protests which led to the shooting of two residents were yesterday jailed for three months.
After their arrest at Kiritiri market on October 8, locals wanted them to be released so they could lynch them as they suspected they were robbers.
Acting chief magistrate Alfred Kibiru said the 11, who pleaded guilty to being in Kenya illegally, will be jailed at the Embu GK Prison.
He said once they finish their sentence they should be deported. Kibiru summoned the owner of the car on which the Ethiopians were being ferried to explain why the court should not take it away. He issued a warrant of arrest for Ahmed Mur Amir who was driving the car. Amir failed to appear in court yesterday.
Since the Ethiopians were arrested the court has been looking for an interpreter who understands Amharic and English or Kiswahili.
The interpreter was available yesterday. The Ethiopians told the court that they were going to Nairobi where they had been promised good jobs after suffering in their country for many years. Kibiru said they should have followed the law if they wanted to work in Kenya.
http://www.the-star.co.ke/
http://www.zehabesha.com/kenya-embu-court-sends-11-illegal-ethiopian-immigrants-to-jail-for-three-months/

Monday, October 13, 2014

Breaking News – Independent Ethiopian Journalist Temesgen Desalegn Arrested

Breaking News – Independent Ethiopian Journalist Temesgen Desalegn Arrested


ተመስገን ደሳለኝ
ተመስገን ደሳለኝ
Ethiopian journalist Temesgen Desalegn has been arrested by Ethiopian police today, October 13, 2014 for articles he wrote before 2013.
Temesgen was the editor in chief of the critical newspaper, Feteh, which was closed by government order. The Ethiopian government filed over 100 lawsuits against him, some of which he is still fighting. He has also been arrested briefly in 2013. He worked as the editor in chief of another critical magazine, Addis Times before it also got closed by the government. 
Temesgen becomes raises the number of Ethiopian journalists and publishers charged and detained over 11 this year alone.
His next appointment is on October 27, 2014; the date he will be sentenced.
Source:: Debirhan